Lithuanian

Amharic: New Testament

2 Corinthians

5

1Mes žinome, kad, mūsų žemiškajam namui, šiai palapinei, suirus, turime pastatą iš Dievo, ne rankomis statytus amžinus namus danguje.
1ድንኳን የሚሆነው ምድራዊ መኖሪያችን ቢፈርስ፥ በሰማይ ያለ በእጅ ያልተሠራ የዘላለም ቤት የሚሆን ከእግዚአብሔር የተሠራ ሕንጻ እንዳለን እናውቃለንና።
2Todėl mes dejuojame, karštai trokšdami apsivilkti savo buveinę iš dangaus,
2በዚህ ውስጥ በእውነት እንቃትታለንና፥
3nes aprengti nebūsime nuogi.
3ከሰማይም የሚሆነውን መኖሪያችንን እንድንለብስ እንናፍቃለንና ለብሰን ራቁታችንን አንገኝም።
4Juk mes, esantys šioje palapinėje, dejuojame prislėgti, norėdami ne nusirengti, bet apsirengti, kad tai, kas maru, būtų gyvenimo praryta.
4በእውነትም የሚሞተው በሕይወት ይዋጥ ዘንድ ልንለብስ እንጂ ልንገፈፍ የማንወድ ስለ ሆነ፥ በድንኳኑ ያለን እኛ ከብዶን እንቃትታለን።
5Tam mus paruošęs yra Dievas, kuris davė mums Dvasią kaip užstatą.
5ነገር ግን ለዚሁ የሠራን እግዚአብሔር ነው እርሱም የመንፈሱን መያዣ ሰጠን።
6Todėl mes visada užtikrinti, žinodami, kad, kol gyvename namuose­kūne, mes nesame su Viešpačiu,—
6እንግዲህ ሁልጊዜ ታምነን፥ በእምነት እንጂ በማየት አንመላለስምና በሥጋ ስናድር ከጌታ ተለይተን በስደት እንዳለን የምናውቅ ከሆንን፥
7mes gyvename tikėjimu, o ne regėjimu,—
8ታምነናል ይልቁንም ከሥጋ ተለይተን በስደት መኖር በጌታም ዘንድ ማደር ደስ ይለናል።
8tačiau esame užtikrinti ir norėtume verčiau palikti kūną ir būti kartu su Viešpačiu.
9ስለዚህ ደግሞ ብናድር ወይም ተለይተን ብንሆን እርሱን ደስ የምናሰኝ ልንሆን እንቀናለን።
9Todėl mes siekiame,­tiek nebūdami, tiek būdami su Juo,­Jam patikti.
10መልካም ቢሆን ወይም ክፉ እንዳደረገ፥ እያንዳንዱ በሥጋው የተሠራውን በብድራት ይቀበል ዘንድ ሁላችን በክርስቶስ በፍርድ ወንበር ፊት ልንገለጥ ይገባናልና።
10Nes mums visiems reikės stoti prieš Kristaus teismo krasę, kad kiekvienas atsiimtų pagal tai, ką jis, gyvendamas kūne, darė­gera ar bloga.
11እንግዲህ የጌታን ፍርሃት አውቀን ሰዎችን እናስረዳለን ለእግዚአብሔር ግን የተገለጥን ነን፤ በሕሊናችሁም ደግሞ የተገለጥን እንደ ሆንን ተስፋ አደርጋለሁ።
11Todėl, pažindami Viešpaties baimę, mes stengiamės įtikinti žmones. Dievui mes esame atviri, tikiuosi, kad esame atviri ir jūsų sąžinėms.
12በመልክ እንጂ በልብ ለማይመኩ የምትመልሱላቸው መልስ እንዲኖራችሁ፥ በእኛ ልትመኩ ምክንያት እንሰጣችኋለን እንጂ ራሳችንን ደግሞ ለእናንተ የምናመሰግን አይደለንም።
12Neprisistatome jums iš naujo, bet duodame progą pasigirti mumis, kad turėtumėte, ką sakyti žmonėms, besigiriantiems savo išore, o ne širdimi.
13እብዶች ብንሆን፥ ለእግዚአብሔር ነው፤ ባለ አእምሮዎች ብንሆን፥ ለእናንተ ነው።
13Jei mes išprotėję­tai Dievui; jei esame sveiko proto­tai dėl jūsų.
14ይህን ስለቆረጥን የክርስቶስ ፍቅር ግድ ይለናልና፤ አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ፤ እንግዲያስ ሁሉ ሞቱ፤
14Nes Kristaus meilė valdo mus, įsitikinusius, kad jei vienas mirė už visus, tai ir visi yra mirę.
15በሕይወትም ያሉት ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ።
15O Jis mirė už visus, kad gyvieji nebe sau gyventų, bet Tam, kuris už juos mirė ir prisikėlė.
16ስለዚህ እኛ ከአሁን ጀምሮ ማንንም በሥጋ እንደሚሆን አናውቅም፤ ክርስቶስንም በሥጋ እንደ ሆነ ያወቅነው ብንሆን እንኳ፥ አሁን ግን ከእንግዲህ ወዲህ እንደዚህ አናውቀውም።
16Todėl nuo šiol mes nė vieno nebepažįstame pagal kūną. Jei mes ir pažinome Kristų pagal kūną, tai dabar taip Jo nebepažįstame.
17ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል።
17Taigi, jei kas yra Kristuje, tas yra naujas kūrinys. Kas sena­ praėjo, štai visa tapo nauja.
18ነገር ግን የሆነው ሁሉ፥ በክርስቶስ ከራሱ ጋር ካስታረቀን የማስታረቅም አገልግሎት ከሰጠን፥ ከእግዚአብሔር ነው፤
18O visa tai iš Dievo, kuris per Jėzų Kristų sutaikino mus su savimi ir davė mums sutaikinimo tarnavimą.
19እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና፥ በደላቸውን አይቆጥርባቸውም ነበር፤ በእኛም የማስታረቅ ቃል አኖረ።
19Tai Dievas Kristuje sutaikino su savimi pasaulį, nebeįskaitydamas žmonėms jų nusikaltimų, ir davė mums sutaikinimo žodį.
20እንግዲህ እግዚአብሔር በእኛ እንደሚማልድ ስለ ክርስቶስ መልክተኞች ነን፤ ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ ብለን ስለ ክርስቶስ እንለምናለን።
20Taigi mes esame Kristaus pasiuntiniai, tarsi pats Dievas prašytų per mus. Kristaus vardu maldaujame: “Susitaikinkite su Dievu!”
21እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው።
21Nes Tą, kuris nepažino nuodėmės, Jis padarė nuodėme dėl mūsų, kad mes Jame taptume Dievo teisumu.