1Būdami Jo bendradarbiai, jūsų taip pat prašome, kad nepriimtumėte Dievo malonės veltui!
1አብረንም እየሠራን የእግዚአብሔርን ጸጋ በከንቱ እንዳትቀበሉ ደግሞ እንለምናለን፤
2Nes Jis sako: “Aš išklausiau tave priimtinu metu ir išgelbėjimo dieną Aš padėjau tau”. Štai dabar yra priimtinas metas, štai dabar išgelbėjimo diena!
2በተወደደ ሰዓት ሰማሁህ በመዳንም ቀን ረዳሁህ ይላልና፤ እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው።
3Mes niekuo neduodame akstino pasipiktinti, kad mūsų tarnavimas nebūtų peiktinas.
3አገልግሎታችንም እንዳይነቀፍ በአንዳች ነገር ማሰናከያ ከቶ አንሰጥም።
4Bet visame kame pasirodome Dievo tarnai: su didele kantrybe, skausmuose, sunkumuose, suspaudimuose,
4ነገር ግን በሁሉ እንደ እግዚአብሔር አገልጋዮች ራሳችንን እናማጥናለን፤
5plakimuose, įkalinimuose, sąmyšiuose, darbuose, budėjimuose, pasninkuose;
5በብዙ መጽናት፥ በመከራ፥ በችግር፥ በጭንቀት፥ በመገረፍ፥ በወኅኒ፥ በሁከት፥ በድካም፥ እንቅልፍ በማጣት፥
6tyrumu, pažinimu, pakantumu, gerumu, Šventąja Dvasia, neveidmainiška meile,
6በመጦም፥ በንጽህና፥ በእውቀት፥ በትዕግሥት፥ በቸርነት፥ በመንፈስ ቅዱስ፥ ግብዝነት በሌለው ፍቅር፥ በእውነት ቃል፥
7tiesos žodžiu, Dievo jėga, teisumo ginklais iš dešinės ir kairės;
7በእግዚአብሔር ኃይል፥ ለቀኝና ለግራ በሚሆን በጽድቅ የጦር ዕቃ፥ በክብርና በውርደት፥
8gerbiami ir negerbiami, šmeižiami ir giriami, laikomi apgavikais ir teisiais,
8በክፉ ወሬና በመልካም ወሬ ራሳችንን እናማጥናለን፤ አሳቾች ስንባል እውነተኞች ነን፤
9nepažįstamais ir gerai žinomais, laikomi mirštančiaisbet štai mes gyvi; esame baudžiami, bet nenužudomi,
9ያልታወቁ ስንባል የታወቅን ነን፤ የምንሞት ስንመስል እነሆ ሕያዋን ነን፤ የተቀጣን ስንሆን አንገደልም፤
10mus liūdina, bet mes visada džiaugiamės, esame skurdžiai, bet daugelį praturtiname, neturime niekoir valdome viską.
10ኀዘንተኞች ስንሆን ዘወትር ደስ ይለናል፤ ድሆች ስንሆን ብዙዎችን ባለ ጠጎች እናደርጋለን፤ አንዳች የሌለን ስንሆን ሁሉ የእኛ ነው።
11O korintiečiai! Mūsų lūpos atvirai jums prabilo, mūsų širdis plačiai atverta.
11እናንተ የቆሮንቶስ ሰዎች ሆይ፥ አፋችን ለእናንተ ተከፍቶአል ልባችንም ሰፍቶላችኋል፤
12Ne mumyse jums ankšta; ankšta jūsų pačių širdyse.
12በእኛ አልጠበባችሁም በሆዳችሁ ግን ጠቦባችኋል፤
13Tad atsimokėkite tuo pačiu, kalbu kaip vaikams,ir taip pat atsiverkite.
13ልጆቼ እንደ መሆናችሁ ግን እላችኋለሁ፥ እናንተ ደግሞ ብድራት መልሳችሁልን ተስፋፉ።
14Nevilkite svetimo jungo su netikinčiais. Kas gi bendro tarp teisumo ir nusikaltimo? Ir kas bendro tarp šviesos ir tamsos?
14ከማያምኑ ጋር በማይመች አካሄድ አትጠመዱ፤ ጽድቅ ከዓመፅ ጋር ምን ተካፋይነት አለውና? ብርሃንም ከጨለማ ጋር ምን ኅብረት አለው?
15Kaipgi galima gretinti Kristų su Beliaru? Arba kokia dalis tikinčio su netikinčiu?
15ክርስቶስስ ከቤልሆር ጋር ምን መስማማት አለው? ወይስ የሚያምን ከማያምን ጋር ምን ክፍል አለው?
16Ir kaip suderinti Dievo šventyklą su stabais? Juk jūs esate gyvojo Dievo šventykla, kaip Dievas yra pasakęs: “Aš gyvensiu juose ir vaikščiosiu tarp jų; būsiu jų Dievas, ir jie bus manoji tauta”.
16ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስም ከጣዖት ጋር ምን መጋጠም አለው? እኛ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ነንና እንዲሁም እግዚአብሔር ተናገረ እንዲህ ሲል። በእነርሱ እኖራለሁ በመካከላቸውም እመላለሳለሁ፥ አምላካቸውም እሆናለሁ እነርሱም ሕዝቤ ይሆናሉ።
17Todėl: “Išeikite iš jų ir atsiskirkite,sako Viešpats,ir nelieskite to, kas netyra, ir Aš jus priimsiu
17ስለዚህም ጌታ። ከመካከላቸው ውጡና የተለያችሁ ሁኑ ርኵስንም አትንኩ ይላል፤ ሁሉንም የሚገዛ ጌታ። እኔም እቀበላችኋለሁ፥ ለእናንተም አባት እሆናለሁ እናንተም ለእኔ ወንድ ልጆችና ሴት ልጆች ትሆናላችሁ ይላል።
18ir būsiu jums Tėvas, o jūs būsite mano sūnūs ir dukterys,sako visagalis Viešpats”.