Lithuanian

Amharic: New Testament

2 Corinthians

7

1Taigi, mylimieji, turėdami tokius pažadus, apsivalykime nuo visos kūno ir dvasios nešvaros, tobulindami šventumą Dievo baimėje.
1እንግዲህ፥ ወዳጆች ሆይ፥ የዚህ ተስፋ ቃል ካለን፥ በእግዚአብሔር ፍርሃት ቅድስናን ፍጹም እያደረግን ሥጋንና መንፈስን ከሚያረክስ ሁሉ ራሳችንን እናንጻ።
2Priimkite mus. Mes nė vieno nenuskriaudėme, nė vienam nepakenkėm, nė vieno neapgavome.
2በልባችሁ ስፍራ አስፉልን፤ ማንንም አልበደልንም፥ ማንንም አላጠፋንም፥ ማንንም አላታለልንም።
3Tai sakau, ne norėdamas jus smerkti. Nes jau esu sakęs, jog esate mūsų širdyse, kad kartu mirtume ir kartu gyventume.
3ለኵነኔ አልልም፤ በአንድነት ለመሞትና በአንድነት ለመኖር በልባችን እንዳላችሁ አስቀድሜ ብዬአለሁና።
4Aš labai pasitikiu jumis ir labai jumis didžiuojuosi. Esu kupinas paguodos ir džiaugsmo visuose mūsų sunkumuose.
4ስለ እናንተ እምነቴ ታላቅ ነው፥ በእናንተ ምክንያት ትምክህቴ ታላቅ ነው፤ መጽናናት ሞልቶብኛል፤ በመከራችን ሁሉ ደስታዬ ከመጠን ይልቅ ይበዛል።
5Kai atvykome į Makedoniją, mūsų kūnui neteko patirti nė kiek ramybės; mes buvome visokeriopai varginami: iš išorės­kovos, viduje­baimė.
5ወደ መቄዶንያም በመጣን ጊዜ፥ በሁሉ ነገር መከራን ተቀበልን እንጂ ሥጋችን ዕረፍት አልነበረውም፤ በውጭ ጠብ ነበረ፥ በውስጥ ፍርሃት ነበረ።
6Bet Dievas, pažemintųjų guodėjas, paguodė mus Tito atvykimu.
6ነገር ግን ኀዘንተኞችን የሚያጽናና አምላክ በቲቶ መምጣት አጽናናን፤
7Ir ne vien jo atvykimu, bet ir ta paguoda, kuria jis buvo paguostas pas jus. Jis pranešė mums apie jūsų karštą troškimą, dejones, jūsų uolumą man. Taigi aš pradžiugau dar labiau.
7በመምጣቱም ብቻ አይደለም ነገር ግን ናፍቆታችሁንና ልቅሶአችሁን ስለ እኔም ቅንዓታችሁን ሲናገረን በእናንተ ላይ በተጽናናበት መጽናናት ደግሞ ነው፤ ስለዚህም ከፊት ይልቅ ደስ አለን።
8Todėl jeigu nuliūdinau jus laišku, tai šito nesigailiu, nors ir apgailestavau. Nes matau, kad tas laiškas jus nuliūdino, bet tik kuriam laikui.
8በመልእክቴ ያሳዘንኋችሁ ብሆን እንኳ አልጸጸትም፤ የተጸጸትሁ ብሆን እንኳ፥ ያ መልእክት ጥቂት ጊዜ ብቻ እንዳሳዘናችሁ አያለሁና አሁን ለንስሐ ስላዘናችሁ ደስ ብሎኛል እንጂ ስላዘናችሁ አይደለም፤
9Dabar aš džiaugiuosi, žinoma, ne todėl, kad jums teko nuliūsti, bet kad jūsų nuliūdimas atvedė jus į atgailą. Jūs buvote nuliūdę dievišku liūdesiu, todėl iš mūsų pusės nebuvo jums jokios skriaudos.
9በምንም ከእኛ የተነሣ እንዳትጎዱ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ አዝናችኋልና።
10Dieviškas liūdesys gimdo atgailą išgelbėjimui, dėl kurio nereikia gailėtis; o pasaulio liūdesys gimdo mirtį.
10እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሆነ ኀዘን ጸጸት የሌለበትን፥ ወደ መዳንም የሚያደርሰውን ንስሐ ያደርጋልና፤ የዓለም ኀዘን ግን ሞትን ያመጣል።
11Ir štai kaip tik tas dieviškas nuliūdimas pagimdė jumyse tokį susirūpinimą, tokį teisinimąsi, apmaudą, baimę, tokį stiprų troškimą, uolumą, tokį atpildą! Jūs visais atžvilgiais pasirodėte švarūs šiame reikale.
11እነሆ፥ ይህ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሆነ ኀዘን እንዴት ያለ ትጋት፥ እንዴት ያለ መልስ፥ እንዴት ያለ ቁጣ፥ እንዴት ያለ ፍርሃት፥ እንዴት ያለ ናፍቆት፥ እንዴት ያለ ቅንዓት፥ እንዴት ያለ በቀል በመካከላችሁ አደረገ። በዚህ ነገር ንጹሐን እንደ ሆናችሁ በሁሉ አስረድታችኋል።
12Todėl, jeigu jums parašiau, tai ne dėl įžeidėjo ir ne dėl įžeistojo, bet kad jums paaiškėtų mūsų rūpestis jumis Dievo akivaizdoje.
12እንግዲያስ የጻፍሁላችሁ ብሆን እንኳ፥ ስለ እኛ ያላችሁ ትጋታችሁ ከእናንተ ዘንድ በእግዚአብሔር ፊት እንዲገለጥ እንጂ፥ ስለ በዳዩ ወይም ስለ ተበዳዩ አልጻፍሁም። ስለዚህ ተጽናንተናል።
13Todėl mes pasiguodėme jūsų paguoda ir dar labiau nudžiugome dėl Tito džiaugsmo, nes jo dvasia buvo jūsų visų atgaivinta.
13በመጽናናታችንም ስለ ቲቶ ደስታ አብልጦ ደስ አለን፥ መንፈሱ በሁላችሁ ዐርፎአልና፤
14Taigi nelikau sugėdintas, kad jam buvau pasigyręs jumis, bet kaip ir viską jums teisingai kalbėjome, taip ir mūsų pasigyrimas Titui pasirodė teisingas.
14ለእርሱ በምንም ስለ እናንተ የተመካሁ እንደ ሆነ አላፈርሁምና፥ ነገር ግን ሁሉን ለእናንተ በእውነት እንደ ተናገርን፥ እንደዚህ ደግሞ ትምክህታችን በቲቶ ፊት እውነት ሆነ።
15Ir jo širdis dar labiau prisirišusi prie jūsų, nes jis prisimena jūsų paklusnumą ir kaip priėmėte jį su baime ir drebėdami.
15ስለዚህም በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ እንዴት እንደተቀበላችሁት፥ የሁላችሁን መታዘዝ እያሰበ ፍቅሩ በእናንተ ላይ እጅግ በዝቶአል።
16Todėl džiaugiuosi, kad visais atžvilgiais galiu jumis pasitikėti.
16በነገር ሁሉ ተማምኜባችኋለሁና ደስ ይለኛል።