1Be to, pranešame jums, broliai, apie Dievo malonę, suteiktą Makedonijos bažnyčioms.
1ወንድሞች ሆይ፥ ለመቄዶንያ አብያተ ክርስቲያናት የተሰጠውን የእግዚአብሔርን ጸጋ እናስታውቃችኋለን፤
2Nors dideli vargai jas bandė, jos pasirodė kupinos džiaugsmo, ir jų gilus skurdas išsiliejo ypatingo dosnumo turtais.
2በብዙ መከራ ተፈትነው ሳሉ የደስታቸው ብዛትና የድህነታቸው ጥልቅነት የልግስናቸውን ባለ ጠግነት አብዝቶአል፤
3Aš liudiju, kad jie pagal išgales ir viršydami išgales, savo noru,
3እንደ ዓቅማቸው መጠን ከዓቅማቸውም የሚያልፍ እንኳ ወደው እንደ ሰጡ እመሰክርላቸዋለሁና።
4prašyte prašė mus, kad mes priimtume dovaną ir jų dalyvavimą tarnavime šventiesiems.
4ለቅዱሳን በሆነው አገልግሎት እንዲተባበሩ ይህን ቸርነት በብዙ ልመና ከእኛ ይለምኑ ነበር፥
5Ir ne tik taip, kaip mes tikėjomės, bet visų pirma atsidavė Viešpačiui, o paskui Dievo valia ir mums.
5አስቀድመውም በእግዚአብሔር ፈቃድ ራሳቸውን ለጌታ ለእኛም ሰጡ እንጂ እንዳሰብን አይደለም።
6Todėl mes paprašėme Titą, kad taip, kaip pradėjo, taip ir baigtų pas jus šią malonę.
6ስለዚህም ቲቶ አስቀድሞ እንደ ጀመረ እንዲሁ ደግሞ ይህን ቸር ሥራ ደግሞ በእናንተ ዘንድ ሊፈጽም ለመንን።
7Tad, būdami visa ko pertekętikėjimo, žodžio, pažinimo, visokeriopo uolumo ir meilės mums, būkite pertekę ir šios malonės.
7ነገር ግን በነገር ሁሉ፥ በእምነትና በቃል በእውቀትም በትጋትም ሁሉ ለእኛም በፍቅራችሁ እንደ ተረፋችሁ፥ በዚህ ቸር ሥራ ደግሞ ትረፉ።
8Tai sakau ne įsakydamas, bet norėdamas kitų uolumu patikrinti jūsų meilės nuoširdumą.
8ትእዛዝ እንደምሰጥ አልልም፥ ነገር ግን በሌሎች ትጋት በኩል የፍቅራችሁን እውነተኛነት ደግሞ ልመረምር እላለሁ፤
9Nes jūs pažįstate mūsų Viešpaties Jėzaus Kristaus malonę, jog Jis, būdamas turtingas, dėl jūsų tapo vargšu, kad jūs per Jo neturtą taptumėte turtingi.
9የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ቸር ስጦታ አውቃችኋልና፤ ሀብታም ሲሆን፥ እናንተ በእርሱ ድህነት ባለ ጠጎች ትሆኑ ዘንድ ስለ እናንተ ድሀ ሆነ።
10Ir čia aš duodu patarimą, nes tai naudinga jums, kurie ne tik pradėjote daryti tai anksčiau, bet ir troškote jau nuo pernai.
10በዚህም ነገር ምክር እሰጣለሁ፤ ከአምና ጀምራችሁ ለማድረግ ብቻ ያይደለ ነገር ግን ለማሰብ ደግሞ አስቀድማችሁ የጀመራችሁት ይህ ይጠቅማችኋልና፤
11Taigi dabar pabaikite šį darbą, kad jūsų nuovokus troškimas būtų įvykdytas iš to, ką turite.
11አሁንም ለማሰብ በጎ ፈቃድ እንደ ነበረ፥ እንዲሁ እንዳላችሁ መጠን መፈጸም ደግሞ ይሆን ዘንድ፥ ማድረጉን ደግሞ ፈጽሙ።
12Nes jei yra sąmoningas noras, jis priimtinas pagal tai, ką žmogus turi, o ne pagal tai, ko neturi.
12በጎ ፈቃድ ቢኖር፥ እንዳለው መጠን የተወደደ ይሆናል እንጂ እንደሌለው መጠን አይደለም።
13Aš nenoriu, kad kitiems tektų lengvatos, o jums naštos,
13ለሌሎች ዕረፍት ለእናንተም መከራ እንዲሆን አይደለም፥ ትክክል እንዲሆን ነው እንጂ፤
14bet kad būtų lygybė: kad šiuo metu jūsų perteklius patenkintų jų nepriteklių, o vėliau jų perteklius taip pat patenkintų jūsų nepriteklių ir būtų lygybė,
14የእነርሱ ትርፍ ደግሞ የእናንተን ጉድለት እንዲሞላ በአሁኑ ጊዜ የእናንተ ትርፍ የእነርሱን ጉድለት ይሙላ፤ በትክክል እንዲሆን፥ እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ።
15kaip parašyta: “Kas daug surinko, neturėjo atliekamo, o kas mažainekentėjo nepritekliaus”.
15ብዙ ያከማቸ አላተረፈም፥ ጥቂትም ያከማቸ አላጎደለም።
16Dėkui Dievui, įdėjusiam į Tito širdį tą patį uolų rūpestį jumis.
16ነገር ግን በቲቶ ልብ ስለ እናንተ ያንን ትጋት የሰጠ አምላክ ይመስገን፤
17Jis ne tik paklausė mano raginimo, bet, būdamas labai uolus, nuvyko pas jus savo noru.
17ምክራችንን ተቀብሎአልና፥ ትጋት ግን ስለ በዛበት ወዶ ወደ እናንተ ይወጣል።
18Kartu su juo pasiuntėme brolį, giriamą dėl Evangelijos skelbimo visose bažnyčiose.
18ከእርሱም ጋር ስለ ወንጌል ስብከት በአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ የተመሰገነውን ወንድም እንልካለን፤
19Dar daugiau, jis yra bažnyčių paskirtas mūsų kelionių palydovu šiai malonei, kurią mes vykdome paties Viešpaties šlovei ir jūsų paslaugumui parodyti,
19ይህም ብቻ አይደለም ነገር ግን የጌታን የራሱን ክብርና የእኛን በጎ ፈቃድ ለማሳየት በምናገለግለው በዚህ ቸር ሥራ ከእኛ ጋር እንዲጓደድ በአብያተ ክርስቲያናት ደግሞ ተመረጠ።
20sergėdamiesi, kad niekas mūsų nekaltintų dėl šios gausos, kurią mes tvarkome.
20ስለምናገለግለው ስለዚህ ለጋስ ስጦታ ማንም እንዳይነቅፈን እንጠነቀቃለን፤
21Mes rūpinamės tuo, kas gerbtina ne tik Viešpaties, bet ir žmonių akyse.
21በጌታ ፊት ብቻ ያይደለ ነገር ግን በሰው ፊት ደግሞ መልካም የሆነውን እናስባለንና።
22Taigi su jais pasiuntėme savo brolį, kurio uolumą daugel kartų įvairiai esame patikrinę ir kuris dabar yra dar uolesnis labai jumis pasitikėdamas.
22ብዙ ጊዜም በብዙ ነገር መርምረን ትጉ እንደ ሆነ ያገኘነውን፥ አሁንም በእናንተ እጅግ ስለሚታመን ከፊት ይልቅ እጅግ ትጉ የሚሆነውን ወንድማችንን ከእነርሱ ጋር እንልካለን።
23Titas‰tai mano bendražygis ir jūsų pagalbininkas, o tie mūsų broliai‰bažnyčių pasiuntiniai, Kristaus šlovė.
23ስለ ቲቶ የሚጠይቅ ቢኖር ስለ እናንተ አብሮኝ የሚሠራ ባልንጀራዬ ነው፤ ስለ ወንድሞቻችን የሚጠይቅ ቢኖርም የአብያተ ክርስቲያናት መልእክተኞችና የክርስቶስ ክብር ናቸው።
24Todėl jų ir visų bažnyčių akyse įrodykite savo meilę ir mūsų pasigyrimą jumis.
24እንግዲህ የፍቅራችሁንና ስለ እናንተ ያለውን የትምክህታችንን መግለጫ በአብያተ ክርስቲያናት ፊት ለእነርሱ ግለጡ።