1Apaštalai ir broliai, kurie buvo Judėjoje, išgirdo, kad ir pagonys priėmė Dievo žodį.
1ሐዋርያትና በይሁዳም የነበሩት ወንድሞች አሕዛብ ደግሞ የእግዚአብሔርን ቃል እንደ ተቀበሉ ሰሙ።
2Todėl, kai Petras atvyko į Jeruzalę, žydų kilmės tikintieji ėmė ginčytis su juo, sakydami:
2ጴጥሮስም ወደ ኢየሩሳሌም በወጣ ጊዜ ከተገረዙት ወገን የሆኑት ሰዎች ከእርሱ ጋር ተከራክረው።
3“Tu nuėjai pas neapipjaustytus vyrus ir su jais valgei!”
3ወዳልተገረዙ ሰዎች ገብተህ ከእነርሱ ጋር በላህ አሉት።
4Tada Petras pradėjo jiems iš eilės aiškinti:
4ጴጥሮስ ግን ከመጀመሪያው ጀምሮ በተራ ገለጠላቸው እንዲህም አለ።
5“Aš kartą meldžiausi Jopės mieste ir Dvasios pagavoje mačiau regėjimą. Kažkoks indas, tarsi didžiulė marška, už keturių kampų leidžiama iš dangaus, nusileido prie manęs.
5እኔ በኢዮጴ ከተማ ስጸልይ ሳለሁ ተመስጬ ራእይን አየሁ፤ ታላቅ ሸማ የመሰለ ዕቃ በአራት ማዕዘን ተይዞ ከሰማይ ወረደና ወደ እኔ መጣ፤
6Atidžiai įsižiūrėjęs, pamačiau jame keturkojų žemės gyvių, laukinių žvėrių, roplių ir padangės paukščių.
6ይህንም ትኵር ብዬ ስመለከት አራት እግር ያላቸውን የምድር እንስሶች አራዊትንም ተንቀሳቃሾችንም የሰማይ ወፎችንም አየሁ።
7Ir išgirdau balsą, kuris man sakė: ‘Kelkis, Petrai, pjauk ir valgyk!’
7ጴጥሮስ ሆይ፥ ተነሣና አርደህ ብላ የሚለኝንም ድምፅ ሰማሁ።
8Aš atsakiau: ‘Jokiu būdu, Viešpatie! Dar niekada suteptas ir nešvarus maistas nebuvo mano burnoje’.
8እኔም። ጌታ ሆይ፥ አይሆንም፤ ርኵስ ወይም የሚያስጸይፍ ከቶ ወደ አፌ ገብቶ አያውቅምና አልሁ።
9Bet balsas iš dangaus prabilo antrą kartą: ‘Ką Dievas apvalė, tu nevadink suteptu!’
9ሁለተኛም። እግዚአብሔር ያነጻውን አንተ አታርክሰው የሚል ድምፅ ከሰማይ መለሰልኝ።
10Taip atsitiko tris kartus, ir vėl viskas pakilo į dangų.
10ይህም ሦስት ጊዜ ሆነ እንደ ገናም ሁሉ ወደ ሰማይ ተሳበ።
11Ir štai prie namų, kuriuose aš buvau, tuojau atėjo trys vyrai. Jie buvo siųsti pas mane iš Cezarėjos.
11እነሆም፥ ያን ጊዜ ሦስት ሰዎች ከቂሣርያ ወደ እኔ ተልከው ወዳለሁበት ቤት ቀረቡ።
12Dvasia man pasakė nė kiek nedvejojant keliauti su jais. Su manimi ėjo ir šitie šeši broliai, ir mes kartu atvykome į vieno vyro namus.
12መንፈስም ሳልጠራጠር ከእነርሱ ጋር እሄድ ዘንድ ነገረኝ። እነዚህም ስድስቱ ወንድሞች ደግሞ ከእኔ ጋር መጡ ወደዚያ ሰውም ቤት ገባን።
13Jis mums papasakojo savo namuose regėjęs stovintį angelą, kuris jam liepė: ‘Nusiųsk į Jopę žmones ir pasikviesk Simoną, vadinamą Petru.
13እርሱም መልአክ በቤቱ ቆሞ እንዳየና። ወደ ኢዮጴ ሰዎች ልከህ ጴጥሮስ የተባለውን ስምዖንን አስመጣ፤
14Jis pasakys tau žodžius, kuriais išsigelbėsi tu ir visi tavo namai’.
14እርሱም አንተና የቤትህ ሰዎች ሁሉ የምትድኑበትን ነገር ይነግርሃል እንዳለው ነገረን።
15Kai pradėjau kalbėti, Šventoji Dvasia nužengė ant jų, kaip ir pradžioje ant mūsų.
15ለመናገርም በጀመርሁ ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ለእኛ ደግሞ በመጀመሪያ እንደ ወረደ ለእነርሱ ወረደላቸው።
16Tada prisiminiau Viešpaties žodžius: ‘Jonas krikštijo vandeniu, o jūs būsite pakrikštyti Šventąja Dvasia’.
16ዮሐንስ በውኃ አጠመቀ እናንተ ግን በመንፈስ ቅዱስ ትጠመቃላችሁ ያለውም የጌታ ቃል ትዝ አለኝ።
17Jeigu tad Dievas suteikė jiems tokią pačią dovaną, kaip ir mums, įtikėjusiems Viešpatį Jėzų Kristų, tai kas gi aš toks, kad galėčiau trukdyti Dievui?!”
17እንግዲህ እግዚአብሔር በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ላመነው ለእኛ ደግሞ እንደ ሰጠን ያን ስጦታ ለእነርሱ ከሰጠ፥ እግዚአብሔርን ለመከልከል እችል ዘንድ እኔ ማን ነበርሁ?
18Tai išgirdę, jie nusiramino ir šlovino Dievą, sakydami: “Vadinasi, Dievas ir pagonims suteikė atgailą, kad jie gyventų”.
18ይህን በሰሙ ጊዜም ዝም አሉና። እንኪያስ እግዚአብሔር ለአሕዛብ ደግሞ ለሕይወት የሚሆን ንስሐን ሰጣቸው እያሉ እግዚአብሔርን አከበሩ።
19Išblaškytieji persekiojimo, kuris buvo kilęs dėl Stepono, nukeliavo į Finikiją, Kiprą ir Antiochiją. Jie pamokslavo žodį vien tik žydams.
19በእስጢፋኖስም ላይ በተደረገው መከራ የተበተኑት እስከ ፊንቄ እስከ ቆጵሮስም እስከ አንጾኪያም ድረስ ዞሩ፥ ቃሉንም ለአይሁድ ብቻ እንጂ ለአንድ ስንኳ አይናገሩም ነበር።
20Kai kurie iš jų, būtent kipriečiai ir kirėniečiai, atvykę į Antiochiją, kreipėsi ir į graikus, skelbdami Viešpatį Jėzų.
20ከእነርሱ ግን የቆጵሮስና የቀሬና ሰዎች የነበሩት አንዳንዶቹ ወደ አንጾኪያ መጥተው የጌታን የኢየሱስን ወንጌል እየሰበኩ ለግሪክ ሰዎች ተናገሩ።
21Viešpaties ranka buvo su jais: didelis žmonių skaičius įtikėjo ir atsivertė į Viešpatį.
21የጌታም እጅ ከእነርሱ ጋር ነበረ፤ ቍጥራቸውም እጅግ የሚሆን ሰዎች አምነው ወደ ጌታ ዘወር አሉ።
22Žinia apie juos pasiekė Jeruzalės bažnyčios ausis, ir ji išsiuntė Barnabą į Antiochiją.
22ወሬውም በኢየሩሳሌም ባለችው ቤተ ክርስቲያን ስለ እነርሱ ተሰማ፥ በርናባስንም ወደ አንጾኪያ ላኩት፤
23Atvykęs ir pamatęs Dievo malonę, jis apsidžiaugė ir visus ragino ryžtinga širdimi pasilikti su Viešpačiu.
23እርሱም መጥቶ የእግዚአብሔርን ጸጋ ባየ ጊዜ ደስ አለው፥ ሁሉንም በልባቸው ፈቃድ በጌታ ጸንተው ይኖሩ ዘንድ መከራቸው፤
24Mat jis buvo geras vyras, pilnas Šventosios Dvasios ir tikėjimo. Ir Viešpačiui prisidėjo didelis būrys.
24ደግ ሰውና መንፈስ ቅዱስ እምነትም የሞላበት ነበረና። ብዙ ሕዝብም ወደ ጌታ ተጨመሩ።
25Tada Barnabas nukeliavo į Tarsą ieškoti Sauliaus
25በርናባስም ሳውልን ሊፈልግ ወደ ጠርሴስ መጣ፤
26ir, radęs jį, atsivedė į Antiochiją. Jiedu ištisus metus darbavosi bažnyčioje ir mokė gausų būrį. Antiochijoje pirmą kartą imta vadinti mokinius “krikščionimis”.
26ባገኘውም ጊዜ ወደ አንጾኪያ አመጣው። በቤተ ክርስቲያንም አንድ ዓመት ሙሉ ተሰበሰቡ፥ ብዙ ሕዝብንም አስተማሩ፤ ደቀ መዛሙርትም መጀመሪያ በአንጾኪያ ክርስቲያን ተባሉ።
27Tomis dienomis iš Jeruzalės į Antiochiją atvyko pranašų.
27በዚያም ወራት ነቢያት ከኢየሩሳሌም ወደ አንጾኪያ ወረዱ፤
28Vienas iš jų, vardu Agabas, Dvasios įkvėptas, išpranašavo didelį badą, kuris ištiksiąs visą pasaulį. Ir badas atėjo, Klaudijui valdant.
28ከእነርሱም አጋቦስ የሚሉት አንድ ሰው ተነሥቶ በዓለም ሁሉ ታላቅ ራብ ሊሆን እንዳለው በመንፈስ አመለከተ፤ ይህም በቀላውዴዎስ ቄሣር ዘመን ሆነ።
29Tada mokiniai, kiekvienas pagal savo išteklius, nusprendė nusiųsti paramą Jeruzalės broliams.
29ደቀ መዛሙርትም እያንዳንዳቸው እንደ ችሎታቸው መጠን አዋጥተው በይሁዳ ለሚኖሩት ወንድሞች እርዳታን ይልኩ ዘንድ ወሰኑ፤
30Jie taip ir padarė, per Barnabą bei Saulių nusiųsdami tai vyresniesiems.
30እንዲህም ደግሞ አደረጉ፥ በበርናባስና በሳውልም እጅ ወደ ሽማግሌዎቹ ሰደዱት።