1Cezarėjoje gyveno vyras, vardu Kornelijus, vadinamosios italų kohortos šimtininkas.
1በቂሣርያም ኢጣሊቄ ለሚሉት ጭፍራ የመቶ አለቃ የሆነ ቆርኔሌዎስ የሚሉት አንድ ሰው ነበረ።
2Jis buvo dievotas ir drauge su savo namiškiais bijojo Dievo, gausiai šelpdavo žmones ir nuolat melsdavosi Dievui.
2እርሱም ከቤተ ሰዎቹ ሁሉ ጋር እግዚአብሔርን የሚያመልክና የሚፈራ ለሕዝብም እጅግ ምጽዋት የሚያደርግ ወደ እግዚአብሔርም ሁልጊዜ የሚጸልይ ነበረ።
3Kartą, apie devintą valandą, jis regėjime aiškiai išvydo pas jį ateinantį Dievo angelą, kuris jam tarė: “Kornelijau!”
3ከቀኑም ዘጠኝ ሰዓት ያህል። ቆርኔሌዎስ ሆይ የሚለው የእግዚአብሔር መልአክ ወደ እርሱ ሲገባ በራእይ በግልጥ አየው።
4Tas, pažvelgęs į jį, išsigando ir paklausė: “Kas yra, viešpatie?” Šis jam atsakė: “Tavo maldos ir gailestingumo aukos pakilo Dievo akivaizdon, ir Jis tave prisiminė.
4እርሱም ትኵር ብሎ ሲመለከተው ደንግጦ። ጌታ ሆይ፥ ምንድር ነው? አለ። መልአኩም አለው። ጸሎትህና ምጽዋትህ በእግዚአብሔር ፊት ለመታሰቢያ እንዲሆን አረገ።
5Dabar siųsk vyrus į Jopę ir pasikviesk Simoną, vadinamą Petru.
5አሁንም ወደ ኢዮጴ ሰዎችን ልከህ ጴጥሮስ የሚባለውን ስምዖንን አስመጣ።
6Jis svečiuojasi pas vieną odininką, Simoną, kurio namai stovi prie jūros. Petras pasakys tau, ką turi daryti”.
6እርሱ ቤቱ በባሕር አጠገብ ባለው በቍርበት ፋቂው በስምዖን ዘንድ እንግድነት ተቀምጦአል፤ ልታደርገው የሚገባህን እርሱ ይነግርሃል።
7Kai su juo kalbėjęs angelas pasitraukė, Kornelijus pasišaukė du tarnus ir vieną pamaldų kareivį iš nuolat šalia esančių valdinių
7የተናገረውም መልአክ በሄደ ጊዜ፥ ከሎሎዎቹ ሁለቱን፥ ከማይለዩትም ጭፍሮቹ እግዚአብሔርን የሚያመልክ አንዱን ወታደር ጠርቶ፥
8ir, viską jiems išaiškinęs, išsiuntė į Jopę.
8ነገሩን ሁሉ ተረከላቸው ወደ ኢዮጴም ላካቸው።
9Rytojaus dieną, kai šitie keliaudami artinosi prie miesto, Petras užlipo ant plokščiastogio melstis. Buvo apie šeštą valandą.
9እነርሱም በነገው ሲሄዱ ወደ ከተማም ሲቀርቡ፥ ጴጥሮስ በስድስት ሰዓት ያህል ይጸልይ ዘንድ ወደ ጣራው ወጣ።
10Jis pasijuto labai išalkęs ir norėjo užkąsti. Kol jam ruošė valgį, jį ištiko dvasios pagava.
10ተርቦም ሊበላ ወደደ፤ ሲያዘጋጁለት ሳሉም ተመስጦ መጣበት፤
11Jis išvydo atsivėrusį dangų, iš kurio jam leidosi žemyn kažkoks padėklas, lyg didelė marška, pririšta už keturių kampų ir nuleidžiama žemėn.
11ሰማይም ተከፍቶ በአራት ማዕዘን የተያዘ ታላቅ ሸማ የሚመስል ዕቃ ወደ ምድር ሲወርድ አየ፤
12Jame buvo įvairiausių žemės keturkojų, laukinių žvėrių, roplių ir padangės paukščių.
12በዚያውም አራት እግር ያላቸው ሁሉ አራዊትም በምድርም የሚንቀሳቀሱት የሰማይ ወፎችም ነበሩበት።
13Ir jam pasigirdo balsas: “Kelkis, Petrai, pjauk ir valgyk!”
13ጴጥሮስ ሆይ፥ ተነሣና አርደህ ብላ የሚልም ድምፅ ወደ እርሱ መጣ።
14Bet Petras atsakė: “Jokiu būdu, Viešpatie! Aš niekuomet nesu valgęs nieko sutepto ar nešvaraus”.
14ጴጥሮስ ግን። ጌታ ሆይ፥ አይሆንም፤ አንዳች ርኵስ የሚያስጸይፍም ከቶ በልቼ አላውቅምና አለ።
15Balsas antrą kartą tarė: “Ką Dievas apvalė, tu nevadink suteptu!”
15ደግሞም ሁለተኛ። እግዚአብሔር ያነጻውን አንተ አታርክሰው የሚል ድምፅ ወደ እርሱ መጣ።
16Taip pasikartojo tris kartus, ir tuojau padėklas vėl pakilo į dangų.
16ይህም ሦስት ጊዜ ሆነ፥ ወዲያውም ዕቃው ወደ ሰማይ ተወሰደ።
17Petrui tebesvarstant, ką galėtų reikšti matytas regėjimas, štai Kornelijaus pasiuntiniai, išklausinėję, kur Simono namai, sustojo prie vartų.
17ጴጥሮስም ስላየው ራእይ። ምን ይሆን? ብሎ በልቡ ሲያመነታ፥ እነሆ፥ ቆርኔሌዎስ የላካቸው ሰዎች ስለ ስምዖን ቤት ጠይቀው ወደ ደጁ ቀረቡ፤
18Jie sušukę paklausė: “Ar čia vieši Simonas, vadinamas Petru?”
18ድምፃቸውንም ከፍ አድርገው። ጴጥሮስ የተባለው ስምዖን በዚህ እንግድነት ተቀምጦአልን? ብለው ይጠይቁ ነበር።
19Petrui, vis tebemąstančiam apie regėjimą, Dvasia tarė: “Štai trys vyrai ieško tavęs.
19ጴጥሮስም ስለ ራእዩ ሲያወጣ ሲያወርድ ሳለ፥ መንፈስ። እነሆ፥ ሦስት ሰዎች ይፈልጉሃል፤
20Kelkis, lipk žemyn ir keliauk su jais nė kiek nedvejodamas, nes Aš juos atsiunčiau”.
20ተነሥተህ ውረድ፥ እኔም ልኬአቸዋለሁና ሳትጠራጠር ከእነርሱ ጋር ሂድ አለው።
21Taigi Petras nulipo žemyn pas Kornelijaus siųstus vyrus ir tarė: “Štai aš, kurio ieškote. Su kokiu reikalu atėjote?”
21ጴጥሮስም ወደ ሰዎቹ ወርዶ። እነሆ፥ የምትፈልጉኝ እኔ ነኝ፤ የመጣችሁበትስ ምክንያት ምንድር ነው? አላቸው።
22Tie atsakė: “Šimtininkas Kornelijus, teisus ir dievobaimingas vyras, turintis gerą vardą visoje žydų tautoje, gavo iš šventojo angelo nurodymą pakviesti tave į savo namus ir išklausyti tavo žodžių”.
22እነርሱም። ጻድቅ ሰው እግዚአብሔርንም የሚፈራ በአይሁድም ሕዝብ ሁሉ የተመሰከረለት የመቶ አለቃ ቆርኔሌዎስ ወደ ቤቱ ያስመጣህ ዘንድ ከአንተም ቃልን ይሰማ ዘንድ ከቅዱስ መልአክ ተረዳ አሉት።
23Tada Petras paprašė juos į vidų ir svetingai priėmė. Kitą rytą iškeliavo su jais. Jį lydėjo keli broliai iš Jopės.
23እርሱም ወደ ውስጥ ጠርቶ እንድግድነት ተቀበላቸው። በነገውም ተነሥቶ ከእነርሱ ጋር ወጣ፥ በኢዮጴም ከነበሩት ወንድሞች አንዳንዶቹ ከእርሱ ጋር አብረው ሄዱ።
24Rytojaus dieną jie atvyko į Cezarėją. Kornelijus jų laukė, susikvietęs savo gimines ir artimiausius draugus.
24በነገውም ወደ ቂሣርያ ገቡ፤ ቆርኔሌዎስም ዘመዶቹንና የቅርብ ወዳጆቹን በአንድነት ጠርቶ ይጠባበቃቸው ነበር።
25Įeinantį Petrą Kornelijus pasitiko ir, puldamas po kojų, išreiškė jam pagarbą.
25ጴጥሮስም በገባ ጊዜ ቆርኔሌዎስ ተገናኝቶ ከእግሩ በታች ወደቀና ሰገደለት።
26Bet Petras pakėlė Kornelijų, tardamas: “Kelkis! Juk ir aš esu žmogus!”
26ጴጥሮስ ግን። ተነሣ፤ እኔ ራሴ ደግሞ ሰው ነኝ ብሎ አስነሣው።
27Paskui, kalbėdamasis su juo, įėjo vidun ir, radęs daug susirinkusių,
27ከእርሱም ጋር እየተነጋገረ ገባ፥ ብዙዎችም ተከማችተው አግኝቶ።
28prabilo: “Jūs žinote, kad žydui nevalia bendrauti ar užeiti pas svetimtautį. Bet Dievas parodė man, jog negalima jokio žmogaus laikyti suteptu ar netyru.
28አይሁዳዊ ሰው ከሌላ ወገን ጋር ይተባበር ወይም ይቃረብ ዘንድ እንዳልተፈቀደ እናንተ ታውቃላችሁ፤ ለእኔ ግን እግዚአብሔር ማንንም ሰው ርኵስና የሚያስጸይፍ ነው እንዳልል አሳየኝ፤
29Štai kodėl pakviestas aš nesipriešindamas atvykau. Taigi klausiu dabar, kokiu reikalu mane pakvietėte?”
29ስለዚህም ደግሞ ብትጠሩኝ ሳልከራከር መጣሁ። አሁንም በምን ምክንያት አስመጣችሁኝ? ብዬ እጠይቃችኋለሁ አላቸው።
30Kornelijus atsakė: “Kaip tik dabar sukanka lygiai keturios dienos, kai aš savo namuose pasninkavau ir meldžiausi devintą valandą. Ir štai prieš mane stojo spindinčiais drabužiais vyras
30ቆርኔሌዎስም እንዲህ አለው። በዚች ሰዓት የዛሬ አራት ቀን የዘጠኝ ሰዓት ጸሎት በቤቴ እጸልይ ነበር፤ እነሆም፥ የሚያንጸባርቅ ልብስ የለበሰ ሰው በፊቴ ቆመና።
31ir prabilo: ‘Kornelijau, tavo maldos išklausytos, ir Dievas prisiminė tavo gailestingumo aukas.
31ቆርኔሌዎስ ሆይ፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸሎትህ ተሰማ ምጽዋትህም ታሰበ።
32Tad siųsk pasiuntinius į Jopę ir pasikviesk Simoną, vadinamą Petru. Jis yra apsistojęs odininko Simono namuose prie jūros. Atėjęs jis tau viską pasakys’.
32እንግዲህ ወደ ኢዮጴ ልከህ ጴጥሮስ የተባለውን ስምዖንን አስጠራ፤ እርሱ በቍርበት ፋቂው በስምዖን ቤት በባሕር አጠገብ እንግድነት ተቀምጦአል አለኝ።
33Taigi aš iš karto pasiunčiau pas tave, o tu gerai padarei, čia atvykdamas. Dabar mes visi esame susirinkę Dievo akivaizdoje, kad išgirstume visa, ką Dievas tau pavedė”.
33ስለዚህ ያን ጊዜ ወደ አንተ ላክሁ፥ አንተም በመምጣትህ መልካም አድርገሃል። እንግዲህ አንተ ከእግዚአብሔር ዘንድ የታዘዝኸውን ሁሉ እንድንሰማ እኛ ሁላችን አሁን በእግዚአብሔር ፊት በዚህ አለን።
34Tada, atvėręs lūpas, Petras pasakė: “Iš tiesų dabar suprantu, kad Dievas neatsižvelgia į asmenis.
34ጴጥሮስም አፉን ከፍቶ እንዲህ አለ። እግዚአብሔር ለሰው ፊት እንዳያደላ ነገር ግን በአሕዛብ ሁሉ እርሱን የሚፈራና ጽድቅን የሚያደርግ በእርሱ የተወደደ እንደ ሆነ በእውነት አስተዋልሁ።
35Jam priimtinas kiekvienos tautos žmogus, kuris Jo bijo ir teisiai gyvena.
36የሁሉ ጌታ በሚሆን በኢየሱስ ክርስቶስ ሰላምን እየሰበከ ይህን ቃል ወደ እስራኤል ልጆች ላከ።
36Jis pasiuntė savo žodį Izraelio vaikams ir per Jėzų Kristų paskelbė taikos Evangeliją. Jis yra visų Viešpats.
37ዮሐንስ ከሰበከው ጥምቀት በኋላ ከገሊላ ጀምሮ በይሁዳ ሁሉ የሆነውን ነገር እናንተ ታውቃላችሁ።
37Jūs žinote, kas yra įvykę visoje Judėjoje, pradedant nuo Galilėjos, po Jono skelbtojo krikšto,
38እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም ቀባው፥ እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበረና፤
38kaip Dievas patepė Šventąja Dvasia ir jėga Jėzų iš Nazareto, ir Jis vaikščiojo, darydamas gera ir gydydamas visus velnio pavergtuosius, nes Dievas buvo su Juo.
39እኛም በአይሁድ አገርና በኢየሩሳሌም ባደረገው ነገር ሁሉ ምስክሮች ነን፤ እርሱንም በእንጨት ላይ ሰቅለው ገደሉት።
39Mes esame liudytojai visko, ką Jis yra padaręs žydų šalyje ir Jeruzalėje. Jį nužudė, pakabindami ant medžio.
40እርሱን እግዚአብሔር በሦስተኛው ቀን አስነሣው ይገለጥም ዘንድ ሰጠው፤
40Tačiau trečią dieną Dievas Jį prikėlė ir leido Jam pasirodyti,
41ይኸውም ለሕዝብ ሁሉ አይደለም ነገር ግን በእግዚአብሔር አስቀድሞ የተመረጡ ምስክሮች ለሆንን ለእኛ ነው እንጂ፤ ከሙታንም ከተነሣ በኋላ ከእርሱ ጋር የበላን የጠጣንም እኛ ነን።
41beje, ne visai tautai, o Dievo iš anksto išrinktiems liudytojams, būtent mums, kurie su Juo valgėme ir gėrėme, Jam prisikėlus iš numirusių.
42ለሕዝብም እንድንሰብክና በሕያዋንና በሙታን ሊፈርድ በእግዚአብሔር የተወሰነ እርሱ እንደ ሆነ እንመሰክር ዘንድ አዘዘን።
42Jis mums įsakė skelbti žmonėms ir liudyti, kad Jis yra Dievo paskirtasis gyvųjų ir mirusiųjų teisėjas.
43በእርሱ የሚያምን ሁሉ በስሙ የኃጢአቱን ስርየት እንዲቀበል ነቢያት ሁሉ ይመሰክሩለታል።
43Apie Jį visi pranašai liudija, kad kiekvienas, kuris Jį tiki, gauna Jo vardu nuodėmių atleidimą”.
44ጴጥሮስ ይህን ነገር ገና ሲናገር ቃሉን በሰሙት ሁሉ ላይ መንፈስ ቅዱስ ወረደ።
44Petrui dar tebekalbant šiuos dalykus, Šventoji Dvasia nužengė ant visų, kurie klausėsi žodžio.
45ከጴጥሮስም ጋር የመጡት ሁሉ ከተገረዙት ወገን የሆኑ ምዕመናን በአሕዛብ ላይ ደግሞ የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ ስለ ፈሰሰ ተገረሙ፤
45Su Petru atvykę žydų kilmės tikintieji labai stebėjosi, kad ir pagonims buvo išlieta Šventosios Dvasios dovana.
46በልሳኖች ሲናገሩ እግዚአብሔርንም ሲያከብሩ ሰምተዋቸዋልና።
46Jie girdėjo juos kalbant kalbomis ir aukštinant Dievą.
47በዚያን ጊዜ ጴጥሮስ መልሶ። እነዚህ እንደ እኛ ደግሞ መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉ እንዳይጠመቁ ውኃን ይከለክላቸው ዘንድ የሚችል ማን ነው? አለ።
47Tuomet Petras tarė: “Ar kas galėtų uždrausti pasikrikštyti jiems vandeniušiems, kurie, kaip ir mes, gavo Šventąją Dvasią?”
48በኢየሱስ ክርስቶስ ስምም ይጠመቁ ዘንድ አዘዛቸው። ከዚህ በኋላ ጥቂት ቀን እንዲቀመጥ ለመኑት።
48Ir jis liepė juos pakrikštyti Viešpaties vardu. Po to jie prašė jį pasilikti dar kelias dienas.