Lithuanian

Amharic: New Testament

Acts

9

1Tuo tarpu Saulius, tebealsuodamas grasinimais ir žudynėmis prieš Viešpaties mokinius, nuėjo pas vyriausiąjį kunigą
1ሳውል ግን የጌታን ደቀ መዛሙርት እንዲገድላቸው ገና እየዛተ ወደ ሊቀ ካህናት ሄደ፥
2ir išgavo raštus Damasko sinagogoms, kad, užtikęs to Kelio sekėjus, vyrus ir moteris, galėtų juos suiminėti ir gabenti į Jeruzalę.
2በዚህ መንገድ ያሉትንም ሰዎች ወንዶችንም ሴቶችንም ቢያገኝ፥ እያሰረ ወደ ኢየሩሳሌም ያመጣቸው ዘንድ በደማስቆ ላሉት ምኵራቦች ደብዳቤ ከእርሱ ለመነ።
3Kai keliaudamas priartėjo prie Damasko, staiga jį apšvietė iš dangaus šviesa.
3ሲሄድም ወደ ደማስቆ በቀረበ ጊዜ ድንገት በእርሱ ዙሪያ ከሰማይ ብርሃን አንጸባረቀ፤
4Jis krito ant žemės ir išgirdo balsą, sakantį jam: “Sauliau, Sauliau, kam mane persekioji?”
4በምድርም ላይ ወድቆ ሳለ። ሳውል ሳውል፥ ስለ ምን ታሳድደኛለህ? የሚለውን ድምፅ ሰማ።
5Jis tarė: “Kas Tu esi, Viešpatie?” Viešpats atsakė: “Aš esu Jėzus, kurį tu persekioji. Sunku tau spyriotis prieš akstiną!
5ጌታ ሆይ፥ ማን ነህ? አለው። እርሱም። አንተ የምታሳድደኝ እኔ ኢየሱስ ነኝ፤ የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብሃል አለው።
6Kelkis, eik į miestą, ir tau bus pasakyta, ką turi daryti”.
6እየተንቀጠቀጠና እየተደነቀ። ጌታ ሆይ፥ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ? አለው። ጌታም። ተነሥተህ ወደ ከተማ ግባና ታደርገው ዘንድ የሚያስፈልግህን ይነግሩሃል አለው።
7Su juo keliavę vyrai stovėjo be žado: jie girdėjo balsą, tačiau nieko nematė.
7ከእርሱም ጋር በመንገድ የሄዱ ሰዎች ድምፁን እየሰሙ ማንን ግን ሳያዩ እንደ ዲዳዎች ቁሙ።
8Saulius atsikėlė nuo žemės, bet, atmerkęs akis, nieko nebematė. Laikydami už rankos, jie nuvedė jį į Damaską.
8ሳውልም ከምድር ተነሣ፥ አይኖቹም በተከፈቱ ጊዜ ምንም አላየም፤ እጁንም ይዘው እየመሩ ወደ ደማስቆ አገቡት።
9Jis tris dienas išbuvo neregintis, nieko nevalgė ir negėrė.
9ሳያይም ሦስት ቀን ኖረ፤ አልበላምም አልጠጣምም።
10Damaske buvo vienas mokinys, vardu Ananijas. Viešpats tarė jam regėjime: “Ananijau!” Šis atsakė: “Štai aš, Viešpatie”.
10በደማስቆም ሐናንያ የሚሉት አንድ ደቀ መዝሙር ነበረ፥ ጌታም በራእይ። ሐናንያ ሆይ፥ አለው። እርሱም። ጌታ ሆይ፥ እነሆኝ አለ።
11Viešpats tęsė: “Kelkis, eik į gatvę, vadinamą Tiesiąja, ir Judo namuose teiraukis tarsiečio, vardu Sauliaus. Štai, jis meldžiasi
11ጌታም። ተነሥተህ ቅን ወደ ሚባለው መንገድ ሂድ፥ በይሁዳ ቤትም ሳውል የሚሉትን አንድ የጠርሴስ ሰው ፈልግ፤
12ir regėjime pamatė vyrą, vardu Ananiją, ateinantį ir uždedantį ant jo rankas, kad praregėtų”.
12እነሆ፥ እርሱ ይጸልያልና፤ ሐናንያ የሚሉትም ሰው ገብቶ ደግሞ እንዲያይ እጁን ሲጭንበት አይቶአል አለው።
13Ananijas atsakė: “Viešpatie, iš daugelio esu girdėjęs apie tą vyrą, kiek daug pikto jis yra padaręs Tavo šventiesiems Jeruzalėje.
13ሐናንያም መልሶ። ጌታ ሆይ፥ በኢየሩሳሌም በቅዱሳንህ ላይ ስንት ክፉ እንዳደረገ ስለዚህ ሰው ከብዙዎች ሰምቼአለሁ፤
14Ir čia jis turi aukštųjų kunigų įgaliojimus suiminėti visus, kurie šaukiasi Tavo vardo”.
14በዚህም ስምህን የሚጠሩትን ሁሉ ለማሰር ከካህናት አለቆች ሥልጣን አለው አለ።
15Bet Viešpats jam tarė: “Eik, nes jis yra mano išrinktas indas, kuris neš mano vardą pagonims, karaliams ir Izraelio vaikams.
15ጌታም። ይህ በአሕዛብም በነገሥታትም በእስራኤልም ልጆች ፊት ስሜን ይሸከም ዘንድ ለእኔ የተመረጠ ዕቃ ነውና ሂድ፤
16Aš jam parodysiu, kiek daug jis turės iškentėti dėl mano vardo”.
16ስለ ስሜ ስንት መከራ ሊቀበል እንዲያስፈልገው እኔ አመለክተዋለሁና አለው።
17Ananijas nuėjo į tuos namus, uždėjo ant jo rankas ir tarė: “Broli Sauliau! Viešpats Jėzus, kuris tau pasirodė kelyje, kai keliavai, atsiuntė mane, kad tu vėl regėtum ir taptum pilnas Šventosios Dvasios”.
17ሐናንያም ሄዶ ወደ ቤቱ ገባ፥ እጁንም ጭኖበት። ወንድሜ ሳውል ሆይ፥ ጌታ፥ እርሱም በመጣህበት መንገድ የታየህ ኢየሱስ ነው፥ ደግሞ ታይ ዘንድና መንፈስ ቅዱስ ይሞላብህ ዘንድ ላከኝ አለ።
18Ir bematant jam nuo akių lyg žvynai nukrito. Jis kaipmat atgavo regėjimą ir buvo pakrikštytas.
18ወዲያውም እንደ ቅርፊት ያለ ከዓይኑ ወደቀ፥ ያን ጊዜም ደግሞ አየ፤ ተነሥቶም ተጠመቀ፥
19Paskui užvalgęs sustiprėjo. Pabuvęs kelias dienas su Damasko mokiniais,
19መብልም በልቶ በረታ። በደማስቆም ካሉት ደቀ መዛሙርት ጋር ጥቂት ቀን ኖረ።
20Saulius bematant pradėjo pamokslauti sinagogose, kad Kristus yra Dievo Sūnus.
20ወዲያውም ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ በምኵራቦቹ ሰበከ።
21Visi, kurie tai girdėjo, be galo stebėjosi ir klausinėjo: “Ar čia ne tas pats, kuris Jeruzalėje persekiojo visus, kurie šaukiasi šito vardo?! Argi jis nėra čia atvykęs jų suimti ir gabenti pas aukštuosius kunigus?!”
21የሰሙትም ሁሉ ተገረሙና። ይህ በኢየሩሳሌም ይህን ስም የሚጠሩትን ያጠፋ አይደለምን? ስለዚህስ ታስረው ወደ ካህናት አለቆች ይወስዳቸው ዘንድ ወደዚህ አልመጣምን? አሉ።
22O Saulius vis labiau stiprėjo ir kėlė sąmyšį tarp Damaske gyvenančių žydų, įrodinėdamas, kad Jėzus yra Kristus.
22ሳውል ግን እየበረታ ሄደ፥ በደማስቆም ለተቀመጡት አይሁድ ይህ ክርስቶስ እንደ ሆነ አስረድቶ መልስ ያሳጣቸው ነበር።
23Praslinkus nemažai laiko, žydai nutarė jį nužudyti.
23ብዙ ቀንም ሲሞላ አይሁድ ሊገድሉት ተማከሩ፤
24Tačiau Saulius sužinojo apie jų sąmokslą. Dieną ir naktį jie tykojo prie vartų, norėdami jį užmušti,
24ሳውል ግን አሳባቸውን አወቀ። ይገድሉትም ዘንድ በሌሊትና በቀን የከተማይቱን በር ሁሉ ይጠቀብቁ ነበር፤
25bet mokiniai nakčia nuleido jį per sieną ant virvių pintinėje.
25ደቀ መዛሙርት ግን በሌሊት ወስደው በቅጥር ላይ አሳልፈው በቅርጫት አወረዱት።
26Saulius nuvyko į Jeruzalę ir mėgino prisidėti prie mokinių, tačiau visi jo bijojo, netikėdami jį esant mokinį.
26ሳውልም ወደ ኢየሩሳሌም በደረሰ ጊዜ ከደቀ መዛሙርት ጋር ይተባበር ዘንድ ሞከረ፤ ሁሉም ደቀ መዝሙር እንደ ሆነ ስላላመኑ ፈሩት።
27Bet Barnabas, pasiėmęs jį, nusivedė pas apaštalus ir jiems papasakojo, kaip kelionėje Saulius regėjęs Viešpatį ir šis kalbėjęs su juo, ir kaip Damaske jis drąsiai pamokslavęs Jėzaus vardu.
27በርናባስ ግን ወስዶ ወደ ሐዋርያት አገባውና ጌታን በመንገድ እንዴት እንዳየውና እንደ ተናገረው በደማስቆም በኢየሱስ ስም ደፍሮ እንዴት እንደ ነገረ ተረከላቸው።
28Taip jis liko su jais Jeruzalėje ir drąsiai kalbėjo Viešpaties Jėzaus vardu.
28በጌታም በኢየሱስ ስም ደፍሮ እየተናገረ በኢየሩሳሌም ሲወጣና ሲገባ ከእነርሱ ጋር ነበረ፤
29Jis kalbėdavosi ir ginčydavosi su helenistais, o tie kėsinosi jį nužudyti.
29ከግሪክ አገርም መጥተው ከነበሩት አይሁድ ጋር ይነጋገርና ይከራከር ነበር፤ እነርሱ ግን ሊገድሉት ፈለጉ።
30Tai sužinoję, broliai jį nugabeno į Cezarėją ir iš ten išsiuntė į Tarsą.
30ወንድሞችም ይህን ባወቁ ጊዜ ወደ ቂሣርያ ወሰዱት ወደ ጠርሴስም ሰደዱት።
31Tuo tarpu bažnyčios visoje Judėjoje, Galilėjoje ir Samarijoje džiaugėsi ramybe, statydinosi ir augo, gyvendamos su Viešpaties baime ir guodžiamos Šventosios Dvasios.
31በይሁዳም ሁሉና በገሊላ በሰማርያም የነበሩት አብያተ ክርስቲያናት በሰላም ኖሩ ታነጹም፤ በእግዚአብሔርም ፍርሃትና በመንፈስ ቅዱስ መጽናናት እየሄዱ ይበዙ ነበር።
32Kartą Petras, lankydamas jas visas, atėjo pas šventuosius, gyvenančius Lydoje.
32ጴጥሮስም በየስፍራው ሁሉ ሲዞር በልዳ ወደሚኖሩ ቅዱሳን ደግሞ ወረደ።
33Ten jis užtiko žmogų, vardu Enėją, kuris paralyžiuotas jau aštuoneri metai gulėjo patale.
33በዚያም ከስምንት ዓመት ጀምሮ በአልጋ ላይ ተኝቶ የነበረውን ኤንያ የሚሉትን አንድ ሰው አገኘ፤ እርሱም ሽባ ነበረ።
34Petras jam tarė: “Enėjau, Jėzus Kristus išgydo tave. Kelkis ir užklok savo patalą!” Šis bematant atsikėlė.
34ጴጥሮስም። ኤንያ ሆይ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ይፈውስሃል፤ ተነሣ ለራስህም አንጥፍ አለው።
35Visi Lydos ir Sarono gyventojai pamatė jį ir atsivertė į Viešpatį.
35ወዲያውም ተነሣ። በልዳና በሰሮናም የሚኖሩ ሁሉ እርሱን አይተው ወደ ጌታ ዘወር አሉ።
36Jopėje gyveno viena mokinė, vardu Tabita, išvertus Dorkadė. Ji garsėjo gerais darbais ir gailestingumo aukomis.
36በኢዮጴም ጣቢታ የሚሉአት አንዲት ደቀ መዝሙር ነበረች፥ ትርጓሜውም ዶርቃ ማለት ነው፤ እርስዋም መልካም ነገር የሞላባት ምጽዋትም የምታደርግ ነበረች።
37Tomis dienomis ji susirgo ir mirė. Ją nuprausė ir paguldė aukštutiniame kambaryje.
37በዚያም ወራት ታመመችና ሞተች፤ አጥበውም በሰገነት አኖሩአት።
38Kadangi Lyda netoli Jopės, mokiniai, išgirdę ten esant Petrą, pasiuntė pas jį du vyrus, prašydami, kad jis nedelsdamas pas juos atvyktų.
38ልዳም ለኢዮጴ ቅርብ ናትና ደቀ መዛሙርት ጴጥሮስ በዚያ እንዳለ ሰምተው፥ ወደ እነርሱ ከመምጣት እንዳይዘገይ እየለመኑ ሁለት ሰዎች ወደ እርሱ ላኩ።
39Petras pakilęs iškeliavo su jais. Kai tik atėjo, jį nuvedė į aukštutinį kambarį. Ten jį apstojo visos našlės, verkdamos ir rodydamos jam tunikas bei viršutinius drabužius, kuriuos, tebegyvendama su jomis, buvo pasiuvusi Dorkadė.
39ጴጥሮስም ተነሥቶ ከእነርሱ ጋር መጣ፤ በደረሰም ጊዜ በሰገነት አወጡት መበለቶችም ሁሉ እያለቀሱ ዶርቃ ከእነርሱ ጋር ሳለች ያደረገቻቸውን ቀሚሶችንና ልብሶችን ሁሉ እያሳዩት በፊቱ ቆሙ።
40Petras liepė visiems išeiti. Atsiklaupęs pasimeldė ir, atsisukęs į lavoną, tarė: “Tabita, kelkis!” Ši atmerkė akis ir, išvydusi Petrą, atsisėdo.
40ጴጥሮስም ሁሉን ወደ ውጭ አስወጥቶ ተንበርክኮም ጸለየ፥ ወደ ሬሳውም ዘወር ብሎ። ጣቢታ ሆይ፥ ተነሺ አላት። እርስዋም ዓይኖችዋን ከፈተች ጴጥሮስንም ባየች ጊዜ ተቀመጠች።
41Jis ištiesė jai ranką ir ją pakėlė. Tada, pašaukęs vidun šventuosius ir našles, parodė jiems ją gyvą.
41እጁንም ለእርስዋ ሰጥቶ አስነሣት፤ ቅዱሳንንና መበለቶችንም ጠራ ሕያውም ሆና በፊታቸው አቆማት።
42Žinia apie tai pasklido visoje Jopėje, ir daugelis įtikėjo Viešpatį.
42ይህም በኢዮጴ ሁሉ የታወቀ ሆነ፥ ብዙ ሰዎችም በጌታ አመኑ።
43Jis dar ilgesnį laiką pasiliko Jopėje pas vieną odininką, vardu Simoną.
43በኢዮጴም ስምዖን ከሚሉት ከአንድ ቍርበት ፋቂ ጋር አያሌ ቀን ኖረ።