Lithuanian

Amharic: New Testament

Acts

8

1Saulius pritarė Stepono nužudymui. Tomis dienomis prasidėjo didelis Jeruzalės bažnyčios persekiojimas. Visi, išskyrus apaštalus, išsisklaidė po Judėjos ir Samarijos apylinkes.
1በዚያን ቀንም በኢየሩሳሌም ባለች ቤተ ክርስቲያን ላይ ታላቅ ስደት ሆነ፤ ሁሉም ከሐዋርያትም በቀር ወደ ይሁዳና ወደ ሰማርያ አገሮች ተበተኑ።
2Dievobaimingi vyrai palaidojo Steponą ir labai jį apraudojo.
2በጸሎትም የተጉ ሰዎች እስጢፋኖስን ቀበሩት ታላቅ ልቅሶም አለቀሱለት።
3O Saulius niokojo bažnyčią, naršydamas po namus, tempdamas iš jų vyrus ir moteris ir siųsdamas juos į kalėjimą.
3ሳውል ግን ቤተ ክርስቲያንን ያፈርስ ነበር፤ ወደ ሁሉም ቤት እየገባ ወንዶችንም ሴቶችንም እየጐተተ ወደ ወኅኒ አሳልፎ ይሰጥ ነበር።
4Tuo tarpu išblaškytieji keliaudami skelbė žodį.
4የተበተኑትም ቃሉን እየሰበኩ ዞሩ።
5Pilypas, nuvykęs į Samarijos miestą, ėmė skelbti gyventojams Kristų.
5ፊልጶስም ወደ ሰማርያ ከተማ ወርዶ ክርስቶስን ሰበከላቸው።
6Minios vieningai klausėsi Pilypo žodžių, girdėdamos ir matydamos, kokius jis darė stebuklus.
6ሕዝቡም የፊልጶስን ቃል በሰሙ ጊዜ ያደርጋት የነበረውንም ምልክት ባዩ ጊዜ፥ የተናገረውን በአንድ ልብ አደመጡ።
7Iš daugelio apsėstųjų, baisiai šaukdamos, išeidavo netyrosios dvasios, išgydavo daug paralyžiuotųjų ir luošų.
7ርኵሳን መናፍስት በታላቅ ድምፅ እየጮኹ ከብዙ ሰዎች ይወጡ ነበርና፤ ብዙም ሽባዎችና አንካሶች ተፈወሱ፤
8Ir didelis džiaugsmas pasklido po tą miestą.
8በዚያችም ከተማ ታላቅ ደስታ ሆነ።
9Mieste buvo vienas vyras, vardu Simonas, kuris nuo seno užsiiminėjo magija, stebindamas Samarijos gyventojus ir sakydamas esąs nepaprastas.
9ሲሞን የሚሉት አንድ ሰው ግን። እኔ ታላቅ ነኝ ብሎ፥ እየጠነቈለ የሰማርያንም ወገን እያስገረመ ቀድሞ በከተማ ነበረ።
10Visi­nuo mažo iki didelio­jį gerbė ir sakė: “Jis yra didelė Dievo jėga”.
10ከታናናሾችም ጀምሮ እስከ ታላላቆቹ ድረስ። ታላቁ የእግዚአብሔር ኃይል ይህ ነው እያሉ ሁሉ ያደምጡት ነበር።
11Gerbė jį todėl, kad ilgą laiką šis stebino juos savo kerais.
11ከብዙ ዘመንም ጀምሮ በጥንቈላ ስላስገረማቸው ያደምጡት ነበር።
12Bet patikėję Pilypu, kuris skelbė Dievo karalystę ir Jėzaus Kristaus vardą, ėmė krikštytis vyrai ir moterys.
12ነገር ግን ስለ እግዚአብሔር መንግሥትና ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም እየሰበከላቸው ፊልጶስን ባመኑት ጊዜ፥ ወንዶችም ሴቶችም ተጠመቁ።
13Ir pats Simonas įtikėjo ir pasikrikštijęs nesitraukė nuo Pilypo. Jis buvo apstulbintas, matydamas daromus ženklus ir stebuklus.
13ሲሞንም ደግሞ ራሱ አመነ፤ ተጠምቆም ከፊልጶስ ጋር ይተባበር ነበር፤ የሚደረገውንም ምልክትና ታላቅ ተአምራት ባየ ጊዜ ተገረመ።
14Apaštalai Jeruzalėje, išgirdę, jog Samarija priėmė Dievo žodį, nusiuntė ten Petrą ir Joną,
14በኢየሩሳሌምም የነበሩት ሐዋርያት የሰማርያ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንደተቀበሉ ሰምተው ጴጥሮስንና ዮሐንስን ሰደዱላቸው።
15kurie atvykę ėmė melstis už samariečius, kad jie priimtų Šventąją Dvasią.
15እነርሱም በወረዱ ጊዜ መንፈስ ቅዱስን ይቀበሉ ዘንድ ጸለዩላቸው፤
16Mat Ji dar nebuvo nė vienam jų nužengusi, ir jie tebuvo pakrikštyti Viešpaties Jėzaus vardu.
16በጌታ በኢየሱስ ስም ብቻ ተጠምቀው ነበር እንጂ ከእነርሱ በአንዱ ላይ ስንኳ ገና አልወረደም ነበርና።
17Tuomet apaštalai dėjo ant jų rankas, ir tie gavo Šventąją Dvasią.
17በዚያን ጊዜ እጃቸውን ጫኑባቸው መንፈስ ቅዱስንም ተቀበሉ።
18Pamatęs, kad apaštalų rankų uždėjimu teikiama Šventoji Dvasia, Simonas pasiūlė jiems pinigų,
18ሲሞንም በሐዋርያት እጅ መጫን መንፈስ ቅዱስ እንዲሰጥ ባየ ጊዜ፥ ገንዘብ አመጣላቸውና።
19sakydamas: “Duokite ir man tą jėgą, kad, kam tik uždėsiu rankas, gautų Šventąją Dvasią”.
19እጄን የምጭንበት ሁሉ መንፈስ ቅዱስን ይቀበል ዘንድ ለእኔ ደግሞ ይህን ሥልጣን ስጡኝ አለ።
20Bet Petras jam tarė: “Kad tu pražūtum kartu su savo pinigais, jei sumanei už pinigus gauti Dievo dovaną!
20ጴጥሮስ ግን እንዲህ አለው። የእግዚአብሔርን ስጦታ በገንዘብ እንድታገኝ አስበሃልና ብርህ ከአንተ ጋር ይጥፋ።
21Šiame dalyke tu negali turėti nė mažiausios dalies, nes tavo širdis neteisi prieš Dievą.
21ልብህ በእግዚአብሔር ፊት የቀና አይደለምና ከዚህ ነገር ዕድል ወይም ፈንታ የለህም።
22Taigi atgailauk dėl šio savo nedorumo ir melsk Dievą­gal Jis atleis tavo širdies sumanymą.
22እንግዲህ ስለዚህ ክፋትህ ንሰሐ ግባ፥ ምናልባትም የልብህን አሳብ ይቅር ይልህ እንደ ሆነ ወደ እግዚአብሔር ለምን፤
23Matau, tu pilnas karčios tulžies ir esi nedorybės pančiuose”.
23በመራራ መርዝና በዓመፅ እስራት እንዳለህ አይሃለሁና።
24Simonas atsakė: “Melskite už mane Viešpatį, kad manęs neištiktų tai, ką jūs sakėte”.
24ሲሞንም መልሶ። ካላችሁት አንዳች እንዳይደርስብኝ እናንተው ወደ ጌታ ለምኑልኝ አላቸው።
25O jie, paliudiję ir apsakę Viešpaties žodį, pasuko atgal į Jeruzalę, skelbdami Evangeliją daugelyje Samarijos kaimų.
25እነርሱም ከመሰከሩና የጌታን ቃል ከተናገሩ በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፤ በሳምራውያን በብዙ መንደሮችም ወንጌልን ሰበኩ።
26Viešpaties angelas prabilo į Pilypą, sakydamas: “Kelkis ir eik pietų link ant kelio, kuris eina iš Jeruzalės į Gazą. Jis visiškai tuščias”.
26የጌታም መልአክ ፊልጶስን። ተነሥተህ በደቡብ በኩል ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ ወደሚያወርደው ምድረ በዳ ወደ ሆነ መንገድ ሂድ አለው።
27Jis pakilo ir iškeliavo. Ir štai važiuoja etiopas eunuchas, aukštas Etiopijos karalienės Kandakės dvariškis, viso jos iždo valdytojas. Jis buvo atvykęs į Jeruzalę pagarbinti,
27ተነሥቶም ሄደ። እነሆም፥ ህንደኬ የተባለች የኢትዮጵያ ንግሥት አዛዥና ጃንደረባ የነበረ በገንዘብዋም ሁሉ የሠለጠነ አንድ የኢትዮጵያ ሰው ሊሰግድ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ነበር፤
28o dabar keliavo namo ir, sėdėdamas savo vežime, skaitė pranašą Izaiją.
28ሲመለስም በሰረገላ ተቀምጦ የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ያነብ ነበር።
29Dvasia pasakė Pilypui: “Prieik ir laikykis greta šito vežimo”.
29መንፈስም ፊልጶስን። ወደዚህ ሰረገላ ቅረብና ተገናኝ አለው።
30Pribėgęs Pilypas išgirdo jį skaitant pranašą Izaiją ir paklausė: “Ar supranti, ką skaitai?”
30ፊልጶስም ሮጦ የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ሲያነብ ሰማና። በውኑ የምታነበውን ታስተውለዋለህን? አለው።
31Šis atsiliepė: “Kaip galiu suprasti, jei man niekas nepaaiškina?!” Ir jis pakvietė Pilypą lipti į vežimą ir sėstis šalia.
31እርሱም። የሚመራኝ ሳይኖር ይህ እንዴት ይቻለኛል? አለው። ወጥቶም ከእርሱ ጋር ይቀመጥ ዘንድ ፊልጶስን ለመነው።
32Rašto vieta, kurią jis skaitė, buvo ši: “Tarsi avį vedė Jį į pjovyklą, ir kaip ėriukas, kuris tyli kerpamas, Jis neatvėrė savo lūpų.
32ያነበውም የነበረ የመጽሐፉ ክፍል ይህ ነበረ፤ እንደ በግ ወደ መታረድ ተነዳ፥ የበግ ጠቦትም በሸላቹ ፊት ዝም እንደሚል፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም።
33Jis buvo pažemintas ir neteisingai nuteistas. Kas apsakys Jo giminę, jeigu Jo gyvenimas žemėje buvo nutrauktas?!”
33በውርደቱ ፍርዱ ተወገደ፤ ሕይወቱ ከምድር ተወግዳለችና ትውልዱንስ ማን ይናገራል?
34Eunuchas paklausė Pilypą: “Prašom paaiškinti, apie ką čia pranašas kalba? Apie save ar apie ką kitą?”
34ጃንደረባውም ለፊልጶስ መልሶ። እባክህ፥ ነቢዩ ይህን ስለ ማን ይናገራል? ስለ ራሱ ነውን ወይስ ስለ ሌላ? አለው።
35Atvėręs lūpas ir pradėjęs nuo tos Rašto vietos, Pilypas jam paskelbė Gerąją naujieną apie Jėzų.
35ፊልጶስም አፉን ከፈተ፥ ከዚህም መጽሐፍ ጀምሮ ስለ ኢየሱስ ወንጌልን ሰበከለት።
36Keliaudami toliau, jie privažiavo vandenį. “Štai vanduo,­tarė eunuchas,­kas gi kliudo man pasikrikštyti?”
36በመንገድም ሲሄዱ ወደ ውኃ ደረሱ፤ ጃንደረባውም። እነሆ ውኃ፤ እንዳልጠመቅ የሚከለክለኝ ምንድር ነው? አለው።
37Pilypas tarė: “Jei tiki iš visos širdies, tai galima”. Tas atsakė: “Tikiu, kad Jėzus Kristus yra Dievo Sūnus”.
37ፊልጶስም። በፍጹም ልብህ ብታምን፥ ተፈቅዶአል አለው። መልሶም። ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ አምናለሁ አለ።
38Jis liepė sustabdyti vežimą, ir jie abu­Pilypas ir eunuchas­išlipę įbrido į vandenį, ir Pilypas jį pakrikštijo.
38ሰረገላውም ይቆም ዘንድ አዘዘ፥ ፊልጶስና ጃንደረባው ሁለቱም ወደ ውኃ ወረዱ፥ አጠመቀውም።
39Išėjus iš vandens, Viešpaties Dvasia pagavo Pilypą. Eunuchas daugiau jo nebematė, tik džiūgaudamas traukė savo keliu.
39ከውኃውም ከወጡ በኋላ የጌታ መንፈስ ፊልጶስን ነጠቀው፤ ጃንደረባውም ሁለተኛ አላየውም፥ ደስ ብሎት መንገዱን ይሄድ ነበርና።
40O Pilypas atsidūrė Azote; iš ten keliaudamas skelbė Evangeliją visuose miestuose ir taip atvyko į Cezarėją.
40ፊልጶስ ግን በአዛጦን ተገኘ፥ ወደ ቂሣርያም እስኪመጣ ድረስ እየዞረ በከተማዎች ሁሉ ወንጌልን ይሰብክ ነበር።