Lithuanian

Amharic: New Testament

Acts

2

1Atėjus Sekminių dienai, visi mokiniai vieningai buvo vienoje vietoje.
1በዓለ ኀምሳ የተባለውም ቀን በደረሰ ጊዜ፥ ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው አብረው ሳሉ፥
2Staiga iš dangaus pasigirdo ūžesys, tarsi pūstų smarkus vėjas. Jis pripildė visą namą, kur jie sėdėjo.
2ድንገት እንደሚነጥቅ ዓውሎ ነፋስ ከሰማይ ድምፅ መጣ፥ ተቀምጠው የነበሩበትንም ቤት ሁሉ ሞላው።
3Jiems pasirodė tarsi ugnies liežuviai, kurie pasidaliję nusileido ant kiekvieno iš jų.
3እንደ እሳትም የተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩአቸው፤ በያንዳንዳቸውም ላይ ተቀመጡባቸው።
4Visi pasidarė pilni Šventosios Dvasios ir pradėjo kalbėti kitomis kalbomis, kaip Dvasia jiems davė prabilti.
4በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፥ መንፈስም ይናገሩ ዘንድ እንደ ሰጣቸው በሌላ ልሳኖች ይናገሩ ጀመር።
5Jeruzalėje gyveno žydų ir dievobaimingų žmonių iš visų tautų po dangumi.
5ከሰማይም በታች ካሉ ሕዝብ ሁሉ በጸሎት የተጉ አይሁድ በኢየሩሳሌም ይኖሩ ነበር፤
6Kilus tam ūžesiui, subėgo daugybė žmonių. Jie buvo priblokšti, kiekvienas girdėdamas savo kalba juos kalbant.
6ይህም ድምፅ በሆነ ጊዜ ሕዝብ ሁሉ ተሰበሰቡ፥ እያንዳንዱም በገዛ ቋንቋው ሲናገሩ ይሰማ ስለ ነበር የሚሉትን አጡ።
7Lyg nesavi ir nustebę, jie vienas kitam kalbėjo: “Argi štai šitie kalbantys nėra galilėjiečiai?
7ተገርመውም ተደንቀውም እንዲህ አሉ። እነሆ፥ እነዚህ የሚናገሩት ሁሉ የገሊላ ሰዎች አይደሉምን?
8Tai kaipgi mes kiekvienas juos girdime savo gimtąja kalba?!
8እኛም እያንዳንዳችን የተወለድንበትን የገዛ ቋንቋችንን እንዴት እንሰማለን?
9Mes, partai, medai, elamitai, Mesopotamijos, Judėjos ir Kapadokijos, Ponto ir Azijos,
9የጳርቴና የሜድ የኢላሜጤም ሰዎች፥ በሁለት ወንዝም መካከል በይሁዳም በቀጰዶቅያም በጳንጦስም በእስያም፥
10Frygijos ir Pamfilijos, Egipto bei Libijos pakraščio ties Kirėne gyventojai, ateiviai romiečiai, žydai ir prozelitai,
10በፍርግያም በጵንፍልያም በግብፅም በቀሬናም በኩል ባሉት በሊቢያ ወረዳዎች የምንኖር፥ በሮሜም የምንቀመጥ፥ አይሁድም ወደ ይሁዲነትም የገባን፥
11kretiečiai ir arabai,­girdime juos skelbiant didingus Dievo darbus mūsų kalbomis”.
11የቀርጤስና የዓረብ ሰዎች፥ የእግዚአብሔርን ታላቅ ሥራ በልሳኖቻችን ሲናገሩ እንሰማቸዋለን።
12Visi labai stebėjosi ir, nieko nesuprasdami, klausinėjo: “Ką tai reiškia?”
12ሁሉም ተገረሙና አመንትተው እርስ በርሳቸው። እንጃ ይህ ምን ይሆን? አሉ።
13O kiti šaipydamiesi kalbėjo: “Jie prisigėrė jauno vyno”.
13ሌሎች ግን እያፌዙባቸው። ጉሽ የወይን ጠጅ ጠግበዋል አሉ።
14Tada stojo Petras su vienuolika ir, pakėlęs balsą, prabilo į juos: “Jūs, vyrai judėjiečiai bei visi Jeruzalės gyventojai, tebūnie jums žinoma,­įsidėmėkite mano žodžius!
14ነገር ግን ጴጥሮስ ከአሥራ አንዱ ጋር ቆመ፥ ድምፁንም ከፍ አድርጎ እንዲህ ሲል ተናገራቸው። አይሁድ በኢየሩሳሌምም የምትኖሩ ሁላችሁ፥ ይህ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን፥ ቃሎቼንም አድምጡ።
15Šitie nėra, kaip jūs manote, prisigėrę,­juk dabar vos trečia dienos valanda,­
15ለእናንተ እንደ መሰላችሁ እነዚህ የሰከሩ አይደሉም፥ ከቀኑ ሦስተኛ ሰዓት ነውና፤
16bet čia išsipildė, kas buvo pasakyta per pranašą Joelį:
16ነገር ግን ይህ በነቢዩ በኢዩኤል የተባለው ነው።
17‘Paskutinėmis dienomis,­sako Dievas,­Aš išliesiu savo Dvasios kiekvienam kūnui, ir jūsų sūnūs bei dukterys pranašaus, jūsų jaunuoliai matys regėjimus, o senieji sapnuos sapnus.
17እግዚአብሔር ይላል። በመጨረሻው ቀን እንዲህ ይሆናል፤ ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ፥ ጎበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ፥ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልም ያልማሉ፤
18Ir savo tarnams bei tarnaitėms tomis dienomis Aš išliesiu savo Dvasios, ir jie pranašaus.
18ደግሞም በዚያች ወራት በወንዶችና በሴቶች ባሪያዎቼ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ ትንቢትም ይናገራሉ።
19Aš darysiu stebuklų aukštai danguje ir apačioje, žemėje, parodysiu ženklų: kraujo, ugnies bei rūkstančių dūmų.
19ድንቆችን በላይ በሰማይ፥ ምልክቶችንም በታች በምድር እሰጣለሁ፤ ደምም እሳትም የጢስ ጭጋግም ይሆናል፤
20Saulė pavirs tamsybe, o mėnulis­krauju, prieš ateinant didingai ir šlovingai Viešpaties dienai.
20ታላቅ የሆነ የተሰማም የጌታ ቀን ሳይመጣ ፀሐይ ወደ ጨለማ ጨረቃም ወደ ደም ይለወጣሉ።
21Ir kiekvienas, kuris šauksis Viešpaties vardo, bus išgelbėtas’.
21የጌታን ስም የሚጠራም ሁሉ ይድናል።
22Izraelio vyrai! Klausykite šitų žodžių: Jėzų iš Nazareto­vyrą, Dievo jums patvirtintą galingais darbais, stebuklais ir ženklais, kuriuos per Jį nuveikė Dievas tarp jūsų,­kaip ir patys žinote,­
22የእስራኤል ሰዎች ሆይ፥ ይህን ቃል ስሙ፤ ራሳችሁ እንደምታውቁ፥ የናዝሬቱ ኢየሱስ እግዚአብሔር በመካከላችሁ በእርሱ በኩል ባደረገው ተአምራትና በድንቆች በምልክቶችም ከእግዚአብሔር ዘንድ ለእናንተ የተገለጠ ሰው ነበረ፤
23Jį, išankstiniu Dievo sprendimu bei numatymu atiduotą, jūs piktadarių rankomis nužudėte, prikaldami prie kryžiaus.
23እርሱንም በእግዚአብሔር በተወሰነው አሳቡና በቀደመው እውቀቱ ተሰጥቶ በዓመፀኞች እጅ ሰቅላችሁ ገደላችሁት።
24Dievas Jį prikėlė, išvaduodamas iš mirties skausmų, nes buvo neįmanoma, kad Jis liktų jos galioje.
24እግዚአብሔር ግን የሞትን ጣር አጥፍቶ አስነሣው፥ ሞት ይይዘው ዘንድ አልቻለምና።
25Juk Dovydas apie Jį sako: ‘Aš visuomet matau Viešpatį priešais save. Jis mano dešinėje, kad Aš nesusvyruočiau.
25ዳዊት ስለ እርሱ እንዲህ ይላልና። ጌታን ሁልጊዜ በፊቴ አየሁት፥ እንዳልታወክ በቀኜ ነውና።
26Todėl džiūgavo mano širdis, krykštavo mano lūpos, ir mano kūnas ilsėsis viltyje,
26ስለዚህ ልቤን ደስ አለው፥ ልሳኔም ሐሤት አደረገ፥ ደግሞም ሥጋዬ በተስፋ ያድራል፤
27nes Tu nepaliksi mano sielos pragare ir neduosi savo Šventajam matyti supuvimo.
27ነፍሴን በሲኦል አትተዋትምና፥ ቅዱስህንም መበስበስን ያይ ዘንድ አትሰጠውም።
28Tu man atvėrei gyvenimo kelius ir pripildysi mane džiaugsmu prieš savo veidą’.
28የሕይወትን መንገድ አስታወቅኸኝ፤ ከፊትህ ጋር ደስታን ትሞላብኛለህ።
29Vyrai broliai! Noriu jums drąsiai pasakyti apie patriarchą Dovydą. Jis mirė, buvo palaidotas, ir jo kapas tebėra pas mus iki šios dienos.
29ወንድሞች ሆይ፥ ስለ አባቶች አለቃ ስለ ዳዊት እንደ ሞተም እንደ ተቀበረም ለእናንተ በግልጥ እናገር ዘንድ ፍቀዱልኝ፤ መቃብሩም እስከ ዛሬ በእኛ ዘንድ ነው።
30Būdamas pranašas ir žinodamas, jog Dievas jam prisiekdamas pažadėjo, kad iš jo palikuonių pagal kūną pakils Kristus užimti jo sosto,
30ነቢይ ስለ ሆነ፥ ከወገቡም ፍሬ በዙፋኑ ያስቀምጥ ዘንድ እግዚአብሔር መሐላ እንደ ማለለት ስለ አወቀ፥
31Dovydas tai numatė ir kalbėjo apie Kristaus prisikėlimą, kad ‘Jo siela neliks pragare ir Jo kūnas nematys supuvimo’.
31ስለ ክርስቶስ ትንሣኤ አስቀድሞ አይቶ፥ ነፍሱ በሲኦል እንዳልቀረች ሥጋውም መበስበስን እንዳላየ ተናገረ።
32Tą Jėzų Dievas prikėlė, ir mes visi esame šito liudytojai.
32ይህን ኢየሱስን እግዚአብሔር አስነሣው ለዚህም ነገር እኛ ሁላችን ምስክሮች ነን፤
33Dievo dešinės išaukštintas, Jis gavo iš Tėvo Šventosios Dvasios pažadą ir išliejo tai, ką dabar matote ir girdite.
33ስለዚህ በእግዚአብሔር ቀኝ ከፍ ከፍ ብሎና የመንፈስ ቅዱስን የተስፋ ቃል ከአብ ተቀብሎ ይህን እናንተ አሁን የምታዩትንና የምትሰሙትን አፈሰሰው።
34Juk Dovydas neįžengė į dangų. Jis pats kalba: ‘Viešpats tarė mano Viešpačiui: sėskis mano dešinėje,
34ዳዊት ወደ ሰማያት አልወጣምና፥ ነገር ግን እርሱ። ጌታ ጌታዬን። ጠላቶችህን የእግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው
35kol Aš patiesiu Tavo priešus, tarsi pakojį po Tavo kojų’.
36አለ። እንግዲህ ይህን እናንተ የሰቀላችሁትን ኢየሱስን እግዚአብሔር ጌታም ክርስቶስም እንዳደረገው የእስራኤል ወገን ሁሉ በእርግጥ ይወቅ።
36Tad tvirtai žinokite, visi Izraelio namai: Dievas padarė Viešpačiu ir Kristumi tą Jėzų, kurį jūs nukryžiavote”.
37ይህንም በሰሙ ጊዜ ልባቸው ተነካ፥ ጴጥሮስንና ሌሎችንም ሐዋርያት። ወንድሞች ሆይ፥ ምን እናድርግ? አሉአቸው።
37Tie žodžiai vėrė jiems širdį, ir jie klausė Petrą bei kitus apaštalus: “Ką mums daryti, vyrai broliai?”
38ጴጥሮስም። ንስሐ ግቡ፥ ኃጢአታችሁም ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ።
38Petras jiems tarė: “Atgailaukite, ir kiekvienas tepasikrikštija Jėzaus Kristaus vardu, kad būtų atleistos jūsų nuodėmės, ir jūs gausite Šventosios Dvasios dovaną.
39የተስፋው ቃል ለእናንተና ለልጆቻችሁ ጌታ አምላካችንም ወደ እርሱ ለሚጠራቸው በሩቅ ላሉ ሁሉ ነውና አላቸው።
39Juk jums skirtas pažadas, taip pat ir jūsų vaikams ir visiems toli esantiems, kuriuos tik pasišauks Viešpats, mūsų Dievas”.
40በብዙ ሌላ ቃልም መሰከረና። ከዚህ ጠማማ ትውልድ ዳኑ ብሎ መከራቸው።
40Dar daugeliu kitų žodžių jis liudijo ir ragino juos, sakydamas: “Gelbėkitės iš šios iškrypusios kartos!”
41ቃሉንም የተቀበሉ ተጠመቁ፥ በዚያም ቀን ሦስት ሺህ የሚያህል ነፍስ ተጨመሩ፤
41Kurie mielai priėmė jo žodį, buvo pakrikštyti, ir tą dieną prisidėjo prie jų apie tris tūkstančius sielų.
42በሐዋርያትም ትምህርትና በኅብረት እንጀራውንም በመቍረስ በየጸሎቱም ይተጉ ነበር።
42Jie ištvermingai laikėsi apaštalų mokymo, bendravimo, duonos laužymo ir maldų.
43ነገር ግን በሰው ሁሉ ፍርሀት ሆነ፤ በሐዋርያትም እጅ ብዙ ድንቅና ምልክት ተደረገ።
43Baimė apėmė kiekvieną, nes per apaštalus vyko daug stebuklų ir ženklų.
44ያመኑትም ሁሉ አብረው ነበሩ፤
44Visi tikintieji laikėsi drauge ir turėjo visa bendra.
45ያላቸውንም ሁሉ አንድነት አደረጉ። መሬታቸውንና ጥሪታቸውንም እየሸጡ፥ ማንኛውም እንደሚፈልግ ለሁሉ ያካፍሉት ነበር።
45Nuosavybę bei turtą jie parduodavo ir, ką gavę, padalydavo visiems, kiek kam reikėdavo.
46በየቀኑም በአንድ ልብ ሆነው በመቅደስ እየተጉ በቤታቸውም እንጀራ እየቈረሱ፥ በደስታና በጥሩ ልብ ምግባቸውን ይመገቡ ነበር፤
46Jie kasdien vieningai rinkdavosi šventykloje, o savo namuose tai vienur, tai kitur laužydavo duoną, vaišindavosi su džiugia ir tauria širdimi,
47እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ በሕዝብ ሁሉ ፊት ሞገስ ነበራቸው። ጌታም የሚድኑትን ዕለት ዕለት በእነርሱ ላይ ይጨምር ነበር።
47šlovindami Dievą, ir turėjo malonę visų žmonių akyse. O Viešpats kasdien gausino bažnyčią išgelbėtaisiais.