Lithuanian

Amharic: New Testament

Acts

3

1Kartą Petras ir Jonas devintą maldos valandą ėjo drauge į šventyklą.
1ጴጥሮስና ዮሐንስም በጸሎት ጊዜ በዘጠኝ ሰዓት ወደ መቅደስ ይወጡ ነበር።
2Ten buvo nešamas ir vienas žmogus, luošas nuo motinos įsčių. Jį kasdien sodindavo prie šventyklos vartų, vadinamų Gražiaisiais, kad prašytų išmaldos iš ateinančių į šventyklą.
2ወደ መቅደስም ከሚገቡት ምጽዋት ይለምን ዘንድ፥ ሰዎች ተሸክመው መልካም በሚሉአት በመቅደስ ደጅ በየቀኑ ያስቀምጡት የነበሩ ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ አንካሳ የሆነ አንድ ሰው ነበረ።
3Pastebėjęs beįeinančius į šventyklą Petrą ir Joną, jis paprašė išmaldos.
3እርሱም ጴጥሮስና ዮሐንስ ወደ መቅደስ ሊገቡ እንዳላቸው ባየ ጊዜ፥ ምጽዋትን ለመናቸው።
4Petras, įdėmiai pažvelgęs į jį drauge su Jonu, tarė:
4ጴጥሮስም ከዮሐንስ ጋር ትኵር ብሎ ወደ እርሱ ተመልክቶ። ወደ እኛ ተመልከት አለው።
5“Pažiūrėk į mudu”. Jis pažvelgė į juos, tikėdamasis ką nors iš jų gauti.
5እርሱም አንድ ነገር ከእነርሱ እንዲቀበል ሲጠብቅ ወደ እነርሱ ተመለከተ።
6Bet Petras pasakė: “Sidabro nei aukso neturiu, bet ką turiu, tą duodu. Jėzaus Kristaus iš Nazareto vardu kelkis ir vaikščiok!”
6ጴጥሮስ ግን። ብርና ወርቅ የለኝም፤ ይህን ያለኝን ግን እሰጥሃለሁ፤ በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሣና ተመላለስ አለው።
7Ir, paėmęs už dešinės rankos, pakėlė jį. Jo pėdos ir keliai bematant sustiprėjo.
7በቀኝ እጁም ይዞ አስነሣው፤ በዚያን ጊዜም እግሩና ቍርጭምጭምቱ ጸና፥
8Jis pašokęs atsistojo, pradėjo vaikščioti ir kartu su apaštalais įėjo į šventyklą. Ten vaikščiodamas ir pasišokinėdamas šlovino Dievą.
8ወደ ላይ ዘሎም ቆመ፥ ይመላለስም ጀመር፤ እየተመላለሰም እየዘለለም እግዚአብሔርንም እያመሰገነ ከእነርሱ ጋር ወደ መቅደስ ገባ።
9Visi žmonės pamatė jį vaikščiojant ir šlovinant Dievą.
9ሕዝቡም ሁሉ እግዚአብሔርን እያመሰገነ ሲመላለስ አዩት፤
10Jie pažino, kad tai tas pats, kuris sėdėdavo elgetaudamas prie Gražiųjų vartų. Visi nustėro ir nustebo dėl to, kas buvo jam atsitikę.
10መልካምም በሚሉአት በመቅደስ ደጅ ስለ ምጽዋት ተቀምጦ የነበረው እርሱ እንደ ሆነ አወቁት፤ በእርሱም ከሆነው የተነሣ መደነቅና መገረም ሞላባቸው።
11Kadangi išgydytas luošys laikėsi Petro ir Jono, prie jų į vadinamąją Saliamono stoginę didžiai nustebinti susibėgo visi žmonės.
11እርሱም ጴጥሮስንና ዮሐንስን ይዞ ሳለ፥ ሕዝቡ ሁሉ እየተደነቁ የሰሎሞን ደጅ መመላለሻ በሚባለው አብረው ወደ እነርሱ ሮጡ።
12Tai matydamas, Petras kreipėsi į žmones: “Izraelio vyrai! Ko stebitės tuo ir ko taip žiūrite į mudu, tarsi mes savo jėga ar savo šventumu būtume padarę, kad šis vaikščiotų?!
12ጴጥሮስም አይቶ ለሕዝቡ እንዲህ ሲል መለሰ። የእስራኤል ሰዎች ሆይ፥ በዚህ ስለ ምን ትደነቃላችሁ? ወይስ በገዛ ኃይላችን ወይስ እግዚአብሔርን በመፍራታችን ይህ ይመላለስ ዘንድ እንዳደረግነው ስለ ምን ትኵር ብላችሁ ታዩናላችሁ?
13Abraomo, Izaoko ir Jokūbo Dievas, mūsų tėvų Dievas, pašlovino savo tarną Jėzų, kurį jūs išdavėte ir kurio išsižadėjote Piloto akivaizdoje, kai tas buvo nusprendęs Jį paleisti.
13የአብርሀምና የይስሐቅ የያዕቆብም አምላክ፥ የአባቶቻችን አምላክ፥ እናንተ አሳልፋችሁ የሰጣችሁትንና ሊፈታው ቈርጦ ሳለ በጲላጦስ ፊት የካዳችሁትን ብላቴናውን ኢየሱስን አከበረው።
14Jūs išsižadėjote Šventojo ir Teisiojo, o pareikalavote atiduoti jums žmogžudį.
14እናንተ ግን ቅዱሱን ጻድቁንም ክዳችሁ ነፍሰ ገዳዩን ሰው ይሰጣችሁ ዘንድ ለመናችሁ፥
15Jūs nužudėte gyvybės Kūrėją, kurį Dievas prikėlė iš numirusių, ir mes esame to liudytojai.
15የሕይወትንም ራስ ገደላችሁት፤ እርሱን ግን እግዚአብሔር ከሙታን አስነሣው፥ ለዚህም ነገር እኛ ምስክሮች ነን።
16Jėzaus vardas­dėl tikėjimo Jo vardu­tvirtą padarė tą, kurį jūs matote ir pažįstate. Iš Jėzaus kylantis tikėjimas suteikė jam visišką sveikatą jūsų visų akyse.
16በስሙም በማመን ይህን የምታዩትንና የምታውቁትን የእርሱ ስም አጸናው፥ በእርሱም በኩል የሆነው እምነት በሁላችሁ ፊት ይህን ፍጹም ጤና ሰጠው።
17O dabar, broliai, aš žinau, kad jūs taip padarėte iš nežinojimo, kaip ir jūsų vadai.
17አሁንም፥ ወንድሞቼ ሆይ፥ እናንተ እንደ አለቆቻችሁ ደግሞ ባለማወቅ እንዳደረጋችሁት አውቄአለሁ፤
18Taip Dievas įvykdė, ką iš anksto buvo paskelbęs visų savo pranašų lūpomis, būtent, kad Kristus kentėsiąs.
18እግዚአብሔር ግን ክርስቶስ መከራ እንዲቀበል አስቀድሞ በነቢያት ሁሉ አፍ የተናገረውን እንዲሁ ፈጸመው።
19Tad atgailaukite ir atsiverskite, kad būtų panaikintos jūsų nuodėmės, kad nuo Viešpaties veido ateitų atgaivos laikai
19እንግዲህ ከጌታ ፊት የመጽናናት ዘመን እንድትመጣላችሁ አስቀድሞም ለእናንተ የመረጠውን ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲልክላችሁ፥ ኃጢአታችሁ ይደመሰስ ዘንድ ንስሐ ግቡ ተመለሱም።
20ir Jis atsiųstų jums iš anksto paskelbtąjį Jėzų Kristų.
21እግዚአብሔር ከጥንት ጀምሮ በቅዱሳን ነቢያቱ አፍ የተናገረው፥ ነገር ሁሉ እስከሚታደስበት ዘመን ድረስ ሰማይ ይቀበለው ዘንድ ይገባልና።
21Jį turi priimti dangus iki visų dalykų atnaujinimo meto. Dievas tai nuo amžių paskelbė visų savo šventųjų pranašų lūpomis.
22ሙሴም ለአባቶች። ጌታ አምላክ እኔን እንዳስነሣኝ ነቢይን ከወንድሞቻችሁ ያስነሣላችኋል፤ በሚነግራችሁ ሁሉ እርሱን ስሙት።
22Juk Mozė tėvams pasakė: ‘Viešpats, mūsų Dievas, iš jūsų brolių pažadins jums Pranašą kaip mane. Klausykite Jo visame kame, ką tik Jis jums sakys.
23ያንም ነቢይ የማትሰማው ነፍስ ሁሉ ከሕዝብ ተለይታ ትጠፋለች አለ።
23O kiekviena siela, kuri to Pranašo neklausys, bus išnaikinta iš tautos’.
24ሁለተኛም ከሳሙኤል ጀምሮ ከእርሱም በኋላ የተናገሩት ነቢያት ሁሉ ደግሞ ስለዚህ ወራት ተናገሩ።
24Ir visi pranašai, kurie tik kalbėjo nuo Samuelio laikų, vienas po kito skelbė šias dienas.
25እናንተ የነቢያት ልጆችና እግዚአብሔር ለአብርሃም። በዘርህ የምድር ወገኖች ሁሉ ይባረካሉ ብሎ፥ ከአባቶቻችን ጋር ያደረገው የኪዳን ልጆች ናችሁ።
25Jūs esate vaikai pranašų ir tos sandoros, kurią Dievas sudarė su jūsų tėvais, tardamas Abraomui: ‘Tavo palikuonyse bus palaimintos visos žemės giminės’.
26ለእናንተ አስቀድሞ እግዚአብሔር ብላቴናውን አስነሥቶ፥ እያንዳንዳችሁን ከክፋታችሁ እየመለሰ ይባርካችሁ ዘንድ፥ ሰደደው።
26Dievas pirmiausia jums prikėlęs pasiuntė savo tarną Jėzų, kad Jis atneštų jums palaiminimą, nukreipdamas kiekvieną nuo jo nusikaltimų”.