1Išsiplėšę iš jų glėbio, išplaukėme ir tiesiu keliu atvykome į Kosą, o kitą dieną į Rodą ir iš ten į Patarą.
1ከእነርሱም ተለይተን ተነሣን፤ በቀጥታም ሄደን ወደ ቆስ በነገውም ወደ ሩድ ከዚያም ወደ ጳጥራ መጣን፤
2Radę laivą, plaukiantį į Finikiją, įlipome ir išplaukėme.
2ወደ ፊንቄም የሚሻገር መርከብ አግኝተን ገባንና ተነሣን።
3Išvydę artėjant Kiprą, palikome jį kairėje ir leidomės link Sirijos, kur išlipome Tyre. Ten laivas turėjo iškrauti savo krovinius.
3ቆጵሮስንም ባየናት ጊዜ በስተ ግራችን ተውናት ወደ ሶርያም ሄደን ወደ ጢሮስ ደረስን፥ መርከቡ ሸክሙን በዚያ የሚያራግፍ ነበርና።
4Suradę mokinių, išbuvome su jais septynias dienas. Dvasios paskatinti, jie sakė Pauliui nevykti į Jeruzalę.
4ደቀ መዛሙርትንም ባገኘን ጊዜ በዚያ ሰባት ቀን ተቀመጥን፤ እነርሱም ጳውሎስን ወደ ኢየሩሳሌም እንዳይወጣ በመንፈስ አሉት።
5Praėjus toms dienoms, mes išėjome ir leidomės į kelionę, o jie visi kartu su žmonomis ir vaikais palydėjo mus iki miesto ribos. Pajūryje suklaupę visi pasimeldėme.
5ጊዜውንም በፈጸምን ጊዜ ወጥተን ሄድን፤ ሁላቸውም ከሚስቶቻቸውና ከልጆቻቸው ጋር እስከ ከተማው ውጭ ድረስ ሸኙን፥ በባሕሩም ዳር ተንበርክከን ጸለይን፤
6Vieni su kitais atsisveikinę, sulipome į laivą, o jie sugrįžo namo.
6እርስ በርሳችንም ተሰነባብተን ወደ መርከብ ወጣን፥ እነዚያም ወደ ቤታቸው ተመለሱ።
7Keliaudami toliau iš Tyro atplaukėme į Ptolemaidę. Ten pasveikinome brolius ir pasilikome pas juos vienai dienai.
7እኛም የባሕሩን መንገድ ጨርሰን ከጢሮስ ወደ አካ ደረስን፥ ለወንድሞችም ሰላምታ ሰጥተን ከእነርሱ ዘንድ አንድ ቀን ተቀመጥን።
8Kitą dieną Paulius ir mes, buvę su juo, vėl iškeliavome ir atvykome į Cezarėją. Ten nuėjome į evangelisto Pilypo, vieno iš septynių, namus ir pas jį pasilikome.
8በነገውም ወጥተን ወደ ቂሣርያ መጣን፥ ከሰባቱም አንድ በሚሆን በወንጌላዊው ፊልጶስ ቤት ገብተን በእርሱ ዘንድ ተቀመጥን።
9Jis turėjo keturias netekėjusias dukteris, kurios pranašaudavo.
9ለእርሱም ትንቢት የሚናገሩ አራት ደናግል ሴቶች ልጆች ነበሩት።
10Mums bebūnant ten daugiau dienų, iš Judėjos atėjo vienas pranašas, vardu Agabas.
10አያሌ ቀንም ተቀምጠን ሳለን ነቢይ የነበረ አጋቦስ የሚሉት አንድ ሰው ከይሁዳ ወረደ።
11Atėjęs pas mus, jis paėmė Pauliaus juostą ir, susirišęs ja rankas ir kojas, tarė: “Taip sako Šventoji Dvasia: ‘Vyrą, kuriam priklauso ši juosta, taip Jeruzalėje supančios žydai ir atiduos į pagonių rankas’ ”.
11ወደ እኛም መጣና የጳውሎስን መታጠቂያ ወስዶ የገዛ እጁንና እግሩን አስሮ። እንዲሁ መንፈስ ቅዱስ። ይህ መታጠቂያ ያለውን ሰው አይሁድ በኢየሩሳሌም እንደዚህ ያስሩታል በአሕዛብም እጅ አሳልፈው ይሰጡታል ይላል አለ።
12Tai išgirdę, ir mes, ir tenykščiai prašėme, kad jis neitų į Jeruzalę.
12ይህንም በሰማን ጊዜ እኛም በዚያ የሚኖሩትም ወደ ኢየሩሳሌም እንዳይወጣ ለመንነው።
13Bet Paulius atsakė: “Kodėl raudate ir draskote man širdį? Aš pasirengęs Jeruzalėje dėl Viešpaties Jėzaus ne tik būti supančiotas, bet ir numirti!”
13ጳውሎስ ግን መልሶ። እያለቀሳችሁ ልቤንም እየሰበራችሁ ምን ማድረጋችሁ ነው? እኔ ስለ ጌታ ስለ ኢየሱስ ስም በኢየሩሳሌም ለመሞት እንኳ ተሰናድቼአለሁ እንጂ ለእስራት ብቻ አይደለም አለ።
14Jam nesiduodant perkalbamam, mes nurimome ir tarėme: “Tebūnie Viešpaties valia!”
14ምክርንም ሊቀበል እምቢ ባለ ጊዜ። የጌታ ፈቃድ ይሁን ብለን ዝም አልን።
15Po tų dienų, susiruošę į kelią, išvykome į Jeruzalę.
15ከዚህም ቀን በኋላ ተዘጋጅተን ወደ ኢየሩሳሌም ወጣን።
16Mus lydėjo kai kurie mokiniai iš Cezarėjos ir nuvedė apsistoti pas vieną kiprietį, seną mokinį Mnasoną.
16በቂሣርያም ከነበሩ ደቀ መዛሙርት አንዳንዶች ደግሞ ከእኛ ጋር መጡ፥ እነርሱም ወደምናድርበት ወደ ቀደመው ደቀ መዝሙር ወደ ቆጵሮሱ ምናሶን ወደሚሉት ቤት መሩን።
17Kai atvykome į Jeruzalę, broliai mus džiaugsmingai priėmė.
17ወደ ኢየሩሳሌም በደረስን ጊዜ ወንድሞች በደስታ ተቀበሉን።
18Kitą dieną Paulius kartu su mumis nuėjo pas Jokūbą, kur buvo susirinkę visi vyresnieji.
18በነገውም ጳውሎስ ከእኛ ጋር ወደ ያዕቆብ ዘንድ ገባ ሽማግሌዎችም ሁሉ መጡ።
19Juos pasveikinęs, jis smulkiai išdėstė visa, ką Dievas padarė pagonijoje per jo tarnystę.
19ሰላምታም ካቀረበላቸው በኋላ በእርሱ ማገልገል እግዚአብሔር በአሕዛብ መካከል ያደረገውን በእያንዳንዱ ተረከላቸው።
20Jie išklausę šlovino Viešpatį ir tarė Pauliui: “Tu matai, broli, kiek daug tūkstančių žydų tapo tikinčiaisiais, ir jie visi uoliai laikosi Įstatymo.
20እነርሱም በሰሙ ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገኑ አሉትም። ወንድም ሆይ፥ በአይሁድ መካከል አምነው የነበሩት ስንት አእላፋት እንደ ሆኑ ታያለህ፤ ሁላቸውም ለሕግ የሚቀኑ ናቸው።
21Bet jiems prikalbėta apie tave, kad tu mokai visus žydus, gyvenančius tarp pagonių, atsižadėti Mozės, sakydamas, jog jiems nereikia apipjaustyti vaikų nei laikytis papročių.
21ልጆቻቸውንም እንዳይገርዙ በሥርዓትም እንዳይሄዱ ብለህ በአሕዛብ መካከል ያሉት አይሁድ ሁሉ ሙሴን ይክዱ ዘንድ እንድታስተምር ስለ አንተ ነግረዋቸዋል።
22Ką daryti? Jie būtinai susirinks, išgirdę, kad esi atvykęs.
22እንግዲህ ምን ይሁን? የአንተን መምጣት ይሰማሉና ብዙዎች የግድ ሳይሰበሰቡ አይቀሩም።
23Todėl padaryk, kaip tau sakome. Pas mus yra keturi vyrai, padarę įžadą.
23እንግዲህ ይህን የምንልህን አድርግ፤ ስለት ያለባቸው አራት ሰዎች በእኛ ዘንድ አሉ።
24Pasiimk juos, apsivalyk kartu su jais ir prisiimk jų išlaidas, kad jie galėtų nusikirpti plaukus. Tada visi pamatys, jog gandai apie tave nieko verti ir tu nenukrypdamas laikaisi Įstatymo.
24እነዚህንም ይዘህ ከእነርሱ ጋር ንጻ፥ ራሳቸውንም እንዲላጩ ገንዘብ ክፈልላቸው፤ ሁሉም ስለ አንተ የተማሩት ከንቱ እንደ ሆነና አንተ ራስህ ደግሞ ሕጉን እየጠበቅህ በሥርዓት እንድትመላለስ ያውቃሉ።
25O dėl tikinčiųjų iš pagonių, tai mes išsiuntėme nurodymus, kad jie saugotųsi to, kas paaukota stabams, kraujo, pasmaugtų gyvulių mėsos ir ištvirkavimo”.
25አምነው ስለ ነበሩ አሕዛብ ግን ለጣዖት ከተሠዋ ከደምም ከታነቀም ከዝሙትም ነፍሳቸውን እንዲጠብቁ ፈርደን እኛ ጽፈንላቸዋል።
26Tada Paulius pasiėmė tuos vyrus ir kitą dieną su jais apsivalęs įėjo į šventyklą. Ten jis nurodė apsivalymo dienų pabaigą, kada už kiekvieną iš jų turės būti paaukota auka.
26በዚያን ጊዜ ጳውሎስ ሰዎችን ይዞ በማግሥቱ ከእነርሱ ጋር እየነጻ፥ መንጻታቸውን የሚፈጽሙበትን ቀን አስታውቆ ወደ መቅደስ ገባ። በዚያም ቀን ስለ እያንዳንዳቸው መሥዋዕትን አቀረቡ።
27Toms septynioms dienoms baigiantis, žydai iš Azijos, pastebėję Paulių šventykloje, sukurstė visą minią ir, nutvėrę jį,
27ሰባቱ ቀንም ይፈጸም ዘንድ ሲቀርብ ከእስያ የመጡ አይሁድ በመቅደስ አይተውት ሕዝብን ሁሉ አወኩና። የእስራኤል ሰዎች ሆይ፥ እርዱን ሕዝብን ሕግንም ይህንም ስፍራ ሲቃወም ሰውን ሁሉ በየስፍራው የሚያስተምረው ሰው ይህ ነው፤ ጨምሮም የግሪክን ሰዎች ደግሞ ወደ መቅደስ አግብቶ ይህን የተቀደሰ ስፍራ አርክሶአል ብለው እየጮኹ እጃቸውን ጫኑበት።
28ėmė šaukti: “Izraelio vyrai, padėkite! Šitas žmogus visur visus moko prieš tautą, Įstatymą ir šią vietą. Jis net atsivedė šventyklon graikus ir suteršė šią šventą vietą”.
29በፊት የኤፌሶኑን ጥሮፊሞስን ከእርሱ ጋር በከተማ አይተውት ነበርና ጳውሎስም ወደ መቅደስ ያገባው መስሎአቸው ነው።
29Mat jie prieš tai matė su juo mieste Trofimą iš Efezo ir manė, kad Paulius jį atsivedęs į šventyklą.
30ከተማውም ሁሉ ታወከ ሕዝቡም ሁሉ ተሰበሰቡ ጳውሎስንም ይዘው ከመቅደስ ውጭ ጎተቱት፥ ወዲያውም ደጆች ተዘጉ።
30Sujudo visas miestas, subėgo žmonės, nutvėrė Paulių ir ištempė jį iš šventyklos. Durys bematant buvo uždarytos.
31ሊገድሉትም ሲፈልጉ። ኢየሩሳሌም ፈጽማ ታወከች የሚል ወሬ ወደ ጭፍራው ሻለቃ ወጣ፤
31Jiems ketinant jį užmušti, įgulos viršininkuitribūnui buvo duota žinia, kad visoje Jeruzalėje kyla sąmyšis.
32እርሱም ያን ጊዜ ወታደሮችን ከመቶ አለቆች ጋር ይዞ እየሮጠ ወረደባቸው፤ እነርሱም የሻለቃውንና ወታደሮችን ባዩ ጊዜ ጳውሎስን መምታት ተዉ።
32Jis nedelsdamas su kareiviais ir šimtininkais atskubėjo ten. Jie, pamatę tribūną ir kareivius, liovėsi mušę Paulių.
33በዚያን ጊዜም የሻለቃው ቀርቦ ያዘውና በሁለት ሰንሰለት ይታሰር ዘንድ አዞ ማን እንደ ሆነና ምን እንዳደረገ ጠየቀ።
33Prisiartinęs tribūnas suėmė Paulių ir įsakė surišti dviem grandinėmis. Paskui paklausė, kas jis esąs ir ką padaręs.
34ሕዝቡም እኵሌቶቹ እንዲህ እኵሌቶቹም እንዲያ እያሉ ይጮኹ ነበር፤ ስለ ጫጫታውም እርግጡን ማወቅ ባልተቻለ ጊዜ፥ ወደ ወታደሮች ሰፈር ይወስዱት ዘንድ አዘዘ።
34Tuo tarpu iš minios šaukė tai šį, tai tą. Negalėdamas dėl triukšmo nieko tikro apie jį sužinoti, tribūnas įsakė nuvesti Paulių į kareivines.
35ወደ ደረጃውም በደረሰ ጊዜ ስለ ሕዝቡ ግፊያ ወታደሮች እንዲሸከሙት ሆነ፤
35Atėjus prie laiptų, dėl minios įsisiautėjimo kareiviams teko jį nešte nešti.
36ብዙ ሕዝብ። አስወግደው እያሉና እየጮኹ ይከተሉ ነበርና።
36Nes žmonių minia sekė iš paskos, šaukdama: “Mirtis jam!”
37ወደ ሰፈርም ሊያገቡት በቀረቡ ጊዜ፥ ጳውሎስ የሻለቃውን። አንድ ነገር ብነግርህ ትፈቅዳለህን? አለው። እርሱም። የግሪክ ቋንቋ ታውቃለህን?
37Vedamas į kareivines, Paulius kreipėsi į tribūną: “Ar galiu tau šį tą pasakyti?” Šis atsiliepė: “Tu moki graikiškai?
38አንተ ከዚህ ዘመን አስቀድሞ ከነፍሰ ገዳዮቹ አራቱን ሺህ ሰዎች አሸፍተህ ወደ ምድረ በዳ ያወጣህ የግብፅ ሰው አይደለህምን? አለ።
38Tai tune anas egiptietis, kuris neseniai sukėlė sąmyšį ir išsivedė į dykumą keturis tūkstančius vyrų žudikų?”
39ጳውሎስ ግን። እኔስ አይሁዳዊ በኪልቅያ ያለው የጠርሴስ ሰው ሆኜ ስመ ጥር በሆነ ከተማ የምኖር ነኝ፤ ለሕዝቡ እናገር ዘንድ እንድትፈቅድልኝ እለምንሃለሁ አለ።
39Paulius atsakė: “Aš esu žydas iš Kilikijos Tarso, taigi žymaus miesto pilietis. Prašau tavęs, leisk man prabilti žmonėms”.
40በፈቀደለትም ጊዜ ጳውሎስ በደረጃው ላይ ቆሞ በእጁ ወደ ሕዝቡ ጠቀሰ እጅግም ጸጥታ በሆነ ጊዜ በዕብራይስጥ ቋንቋ እየተናገረ እንዲህ አለ።
40Tribūnas sutiko. Paulius atsistojo ant laiptų ir pamojo ranka miniai. Visiems nutilus, jis prabilo hebrajų kalba: