1“Vyrai broliai ir tėvai! Paklausykite, ką dabar pasakysiu sau apginti”.
1እናንተ ወንድሞች አባቶችም፥ አሁን ለእናንተ ነገሬን ስገልጥ ስሙኝ።
2Išgirdę jį kreipiantis į juos hebrajiškai, jie dar labiau nurimo. O jis kalbėjo toliau:
2በዕብራይስጥም ቋንቋ ሲናገር በሰሙ ጊዜ ከፊት ይልቅ ዝም አሉ። እርሱም አለ።
3“Aš esu žydas, gimęs Tarse, Kilikijoje, bet išauklėtas šitame mieste, prie Gamalielio kojų, tobulai išmokytas pagal mūsų protėvių Įstatymą, ir buvau ypatingai uolus dėl Dievo, kaip ir jūs visi šiandien.
3እኔ የኪልቅያ በምትሆን በጠርሴስ የተወለድሁ፥ በዚችም ከተማ በገማልያል እግር አጠገብ ያደግሁ፥ የአባቶችንም ሕግ ጠንቅቄ የተማርሁ፥ ዛሬውንም እናንተ ሁሉ እንድትሆኑ ለእግዚአብሔር ቀናተኛ የሆንሁ አይሁዳዊ ሰው ነኝ
4Todėl iki mirties persekiojau šį Kelią, pančiodamas ir mesdamas į kalėjimą vyrus ir moteris.
4ወንዶችንም ሴቶችንም እያሰርሁ ወደ ወኅኒም አሳልፌ እየሰጠሁ ይህን መንገድ እስከ ሞት ድረስ አሳደድሁ።
5Tai gali paliudyti ir vyriausiasis kunigas, ir visa vyresniųjų taryba. Iš jų buvau gavęs laiškus broliams ir keliavau į Damaską, kad tenykščius surištus atgabenčiau į Jeruzalę nubausti.
5እንዲህም ሊቀ ካህናቱ ደግሞ ሽማግሌዎቹም ሁሉ ይመሰክሩልኛል፤ ከእነርሱ ደግሞ መልእክትን ለወንድሞቻቸው ተቀብዬ፥ በደማስቆ ያሉትን ደግሞ ታስረው እንዲቀጡ ወደ ኢየሩሳሌም ላመጣ ወደዚያ እሄድ ነበር።
6Man keliaujant ir artinantis prie Damasko, apie vidurdienį staiga mane apšvietė ryški šviesa iš dangaus.
6ስሄድም ወደ ደማስቆ በቀረብሁ ጊዜ፥ ቀትር ሲሆን ድንገት ከሰማይ ታላቅ ብርሃን በዙሪያዬ አንጸባረቀ፤
7Aš kritau ant žemės ir išgirdau balsą, man sakantį: ‘Sauliau, Sauliau, kam mane persekioji?’
7በምድርም ላይ ወድቄ። ሳውል ሳውል፥ ስለ ምን ታሳድደኛለህ? የሚለኝን ድምፅ ሰማሁ።
8Aš paklausiau: ‘Kas Tu esi, Viešpatie?’ Jis man atsakė: ‘Aš esu Jėzus iš Nazareto, kurį tu persekioji’.
8እኔም መልሼ። ጌታ ሆይ፥ አንተ ማን ነህ? አልሁ። እርሱም። አንተ የምታሳድደኝ የናዝሬቱ ኢየሱስ እኔ ነኝ አለኝ።
9Buvusieji su manimi matė šviesą ir išsigando, bet negirdėjo man kalbančiojo balso.
9ከእኔ ጋር የነበሩትም ብርሃኑን አይተው ፈሩ፥ የሚናገረኝን የእርሱን ድምፅ ግን አልሰሙም።
10Aš dar paklausiau: ‘Ką man daryti, Viešpatie?’ O Viešpats man tarė: ‘Kelkis, eik į Damaską, tenai tau bus pasakyta visa, ką tau reikia daryti’.
10ጌታ ሆይ፥ ምን ላድርግ? አልሁት። ጌታም። ተነሥተህ ወደ ደማስቆ ሂድና ታደርገው ዘንድ ስለ ታዘዘው ሁሉን በዚያ ይነግሩሃል አለኝ።
11Kadangi tos šviesos šlovės apakintas nieko nebemačiau, palydovų už rankos vedamas pasiekiau Damaską.
11ከዚያ ብርሃንም ክብር የተነሣ ማየት ባይሆንልኝ ከእኔ ጋር የነበሩት ሰዎች እጄን ይዘው እየመሩኝ ወደ ደማስቆ ደረስሁ።
12Toksai Ananijas, Įstatymo požiūriu dievotas vyras, apie kurį gerai liudijo visi aplinkiniai žydai,
12በዚያም የኖሩት አይሁድ ሁሉ የመሰከሩለት እንደ ሕጉም በጸሎት የተጋ ሐናንያ የሚሉት አንድ ሰው ነበረ።
13atėjęs stojo prieš mane ir tarė: ‘Broli Sauliau, praregėk!’ Ir tą pačią akimirką aš jį pamačiau.
13እርሱም ወደ እኔ መጥቶ በአጠገቤም ቆሞ። ወንድሜ ሳውል ሆይ፥ እይ አለኝ። እኔም ያን ጊዜውን ወደ እርሱ አየሁ።
14O jis kalbėjo: ‘Mūsų protėvių Dievas išsirinko tave, kad pažintum Jo valią, išvystum Teisųjį ir išgirstum balsą iš Jo lūpų,
14እርሱም አለኝ። የአባቶቻችን አምላክ ፈቃዱን ታውቅ ዘንድና ጻድቁን ታይ ዘንድ ከአፉም ድምፅን ትሰማ ዘንድ አስቀድሞ መርጦሃል
15nes tu būsi Jo liudytojas visiems žmonėms, skelbdamas, ką girdėjai ir regėjai.
15ባየኸውና በሰማኸው በሰው ሁሉ ፊት ምስክር ትሆንለታለህና።
16Tad ko lauki? Kelkis, pasikrikštyk ir nusiplauk nuodėmes, šaukdamasis Viešpaties vardo!’
16አሁንስ ለምን ትዘገያለህ? ተነሣና ስሙን እየጠራህ ተጠመቅ ከኃጢአትህም ታጠብ።
17Vėliau, sugrįžęs į Jeruzalę ir melsdamasis šventykloje, patyriau Dvasios pagavą
17ወደ ኢየሩሳሌምም ከተመለሱ በኋላ በመቅደስ ስጸልይ ተመስጦ መጣብኝ፥
18ir išvydau Jėzų. Jis pasakė: ‘Skubiai pasitrauk iš Jeruzalės, nes jie nepriims tavo liudijimo apie mane’.
18እርሱም። ፍጠን ከኢየሩሳሌምም ቶሎ ውጣ፥ ስለ እኔ የምትመሰክረውን አይቀበሉህምና ሲለኝ አየሁት።
19Aš atsiliepiau: ‘Viešpatie, juk jie žino, kad Tavo tikinčiuosius iš visų sinagogų mesdavau į kalėjimą ir plakdavau.
19እኔም። ጌታ ሆይ፥ በአንተ የሚያምኑትን በምኵራብ ሁሉ እኔ በወኅኒ አገባና እደበድብ እንደ ነበርሁ እነርሱ ያውቃሉ፤
20O kai buvo pralietas tavo liudytojo Stepono kraujas, aš ten stovėjau pritardamas jo nužudymui ir saugodamas žudikų drabužius’.
20የሰማዕትህንም የእስጢፋኖስን ደም ባፈሰሱ ጊዜ፥ ራሴ ደግሞ በአጠገባቸው ስቆም ተስማምቼ የገዳዮችን ልብስ እጠብቅ ነበር አልሁ።
21Bet Jis tarė man: ‘Eik, nes Aš siųsiu tave toli, pas pagonis’ ”.
21እርሱም። ሂድ፥ እኔ ወደ አሕዛብ ከዚህ ወደ ሩቅ እልክሃለሁና አለኝ።
22Jie klausėsi jo iki šitų žodžių, o čia ėmė garsiai šaukti: “Nušluoti nuo žemės jį! Tokiam nevalia gyventi!”
22እስከዚህም ቃል ድረስ ይሰሙት ነበር፥ ድምፃቸውንም ከፍ አድርገው። እንደዚህ ያለውን ሰው ከምድር አስወግደው፥ በሕይወት ይኖር ዘንድ አይገባውምና አሉ።
23Jie klykė, mosavo drabužiais ir svaidė į orą smėlį.
23ሲጮኹና ልብሳቸውን ሲወረውሩ ትቢያንም ወደ ላይ ሲበትኑ፥
24Tribūnas įsakė nuvesti Paulių į kareivines ir liepė tardyti plakant, kad išsiaiškintų, kodėl žmonės prieš jį taip rėkė.
24የሻለቃው ወደ ሰፈሩ እንዲያገቡት አዘዘ፥ እንደዚህም የጮኹበትን ምክንያት ያውቅ ዘንድ። እየገረፋችሁ መርምሩት አላቸው።
25Kai jau buvo pririštas diržais, Paulius kreipėsi į šalia stovintį šimtininką: “Ar jums leista plakti Romos pilietį, ir dar nenuteistą?”
25በጠፍርም በገተሩት ጊዜ ጳውሎስ በአጠገቡ የቆመውን የመቶ አለቃ። የሮሜን ሰው ያለ ፍርድ ትገርፉ ዘንድ ተፈቅዶላችኋልን? አለው።
26Tai išgirdęs, šimtininkas priėjo prie tribūno ir pasakė: “Žiūrėk, ką darai! Tas žmogus yra Romos pilietis”.
26የመቶ አለቃውም በሰማ ጊዜ ወደ ሻለቃው ቀርቦ። ይህ ሰው ሮማዊ ነውና ታደርገው ዘንድ ካለህ ተጠበቅ ብሎ ነገረው።
27Tribūnas atėjęs paklausė: “Pasakyk man, ar tu Romos pilietis?” Paulius atsakė: “Taip”.
27የሻለቃውም ቀርቦ። አንተ ሮማዊ ነህን? ንገረኝ አለው፤ እርሱም። አዎን አለ።
28Tribūnas tarė: “Aš šitą pilietybę įsigijau už didelius pinigus”. Paulius atsiliepė: “O aš turiu ją nuo gimimo”.
28የሻለቃውም መልሶ። እኔ ይህን ዜግነት በብዙ ገንዘብ አገኘሁት አለ። ጳውሎስም። እኔ ግን በእርስዋ ተወለድሁ አለ።
29Bematant pasitraukė nuo jo tie, kurie turėjo jį tardyti. Tribūnas išsigando, sužinojęs, kad Paulius yra Romos pilietis, ir kad jį surišo.
29ስለዚህም ሊመረምሩት ያሰቡት ከእርሱ ወዲያው ተለዩ፤ የሻለቃውም ደግሞ ሮማዊ መሆኑን ባወቀ ጊዜ ፈራ፥ አሳስሮት ነበርና።
30Rytojaus dieną, norėdamas tiksliau išsiaiškinti, kuo jis žydų kaltinamas, tribūnas išlaisvino jį iš grandinių, liepė sušaukti aukštuosius kunigus bei visą sinedrioną ir, atvedęs Paulių, pastatė jų akivaizdoje.
30በማግሥቱም አይሁድ የከሰሱት በምን ምክንያት እንደ ሆነ እርግጡን ያውቅ ዘንድ አስቦ ፈታው፥ የካህናት አለቆችና ሸንጎውም ሁሉ ይሰበሰቡ ዘንድ አዘዘ፥ ጳውሎስንም አውርዶ በፊታቸው አቆመው።