Lithuanian

Amharic: New Testament

Acts

27

1Kai buvo nuspręsta, kad mes turime išplaukti į Italiją, Paulių ir kelis kitus kalinius perdavė Augusto kohortos šimtininkui Julijui.
1ወደ ኢጣሊያም በመርከብ እንሄድ ዘንድ በተቈረጠ ጊዜ፥ ጳውሎስንና ሌሎችን እስረኞች ከአውግስጦስ ጭፍራ ለነበረ ዩልዮስ ለሚሉት ለመቶ አለቃ አሳልፈው ሰጡአቸው።
2Mes įlipome į Adramitijos laivą, kuris turėjo plaukti Azijos pakrantėmis, ir leidomės į kelionę. Su mumis buvo makedonietis Aristarchas iš Tesalonikos.
2በእስያም ዳርቻ ወዳሉ ስፍራዎች ይሄድ ዘንድ ባለው በአድራሚጢስ መርከብ ገብተን ተነሣን፤ የመቄዶንያም ሰው የሆነ የተሰሎንቄው አርስጥሮኮስ ከእኛ ጋር ነበረ።
3Kitą dieną atplaukėme į Sidoną. Julijus kilniai elgėsi su Pauliumi ir leido jam aplankyti bičiulius, kad galėtų pasidžiaugti jų globa.
3በነገውም ወደ ሲዶና ስንደርስ ዩልዮስ ለጳውሎስ ቸርነት አድርጎ እርዳታቸውን ይቀበል ዘንድ ወደ ወዳጆቹ እንዲሄድ ፈቀደለት።
4Išvykę iš ten, plaukėme Kipro užuovėja, nes pūtė priešingi vėjai.
4ከዚያም ተነሥተን ነፋሱ ፊት ለፊት ነበረና በቆጵሮስ ተተግነን ሄድን፤
5Perplaukę jūrą ties Kilikija ir Pamfilija, atvykome į Lykijos miestą Myrą.
5በኪልቅያና በጵንፍልያም አጠገብ ያለውን ባሕር ከተሻገርን በኋላ በሉቅያ ወዳለ ወደ ሙራ ደረስን።
6Tenai šimtininkas surado Aleksandrijos laivą, kuris plaukė į Italiją, ir persodino mus į jį.
6የመቶ አለቃውም በዚያ ወደ ኢጣሊያ የሚሄድ የእስክንድርያውን መርከብ አግኝቶ ወደ እርሱ አገባን።
7Daug dienų plaukėme palengva ir vargais negalais atsiradome ties Knidu. Kadangi vėjas kliudė, plaukėme Kretos priedangoje, link Salmonės.
7ብዙ ቀንም እያዘገምን ሄደን በጭንቅ ወደ ቀኒዶስ አንጻር ደረስን፤ ነፋስም ስለ ከለከለን በቀርጤስ ተተግነን በሰልሙና አንጻር ሄድን፤
8Šiaip ne taip ją aplenkę, atvykome į vietovę, kuri vadinosi Dailioji Prieplauka, netoli Lasėjos miesto.
8በጭንቅም ጥግ ጥጉን አልፈን ለላሲያ ከተማ ወደ ቀረበች መልካም ወደብ ወደሚሉአት ስፍራ መጣን።
9Prabėgo daug laiko, ir laivyba tapo pavojinga, nes jau buvo pasibaigęs rudens pasninko metas. Paulius juos įspėjo,
9ብዙ ጊዜም ካለፈ በኋላ፥ የጦም ወራት አሁን አልፎ ስለ ነበረ በመርከብ ለመሄድ አሁን የሚያስፈራ ነበርና ጳውሎስ።
10sakydamas: “Vyrai, numatau, jog šis plaukimas bus grėsmingas ir pražūtingas ne tik kroviniams bei laivui, bet ir mūsų gyvybėms”.
10እናንተ ሰዎች ሆይ፥ ይህ ጕዞ በጥፋትና በብዙ ጕዳት እንዲሆን አያለሁ፤ ጥፋቱም በገዛ ሕይወታችን ነው እንጂ በጭነቱና በመርከቡ ብቻ አይደለም ብሎ መከራቸው።
11Tačiau šimtininkas labiau tikėjo vairininku ir laivo savininku negu tuo, ką kalbėjo Paulius.
11የመቶ አለቃው ግን ጳውሎስ ከተናገረው ይልቅ የመርከብ መሪውንና የመርከቡን ባለቤት ያምን ነበር።
12Kadangi uostas buvo netinkamas žiemoti, dauguma nusprendė iš ten plaukti toliau, kaip nors pasiekti Feniksą, Kretos uostą, atvirą į pietvakarius ir šiaurės vakarus, ir ten žiemoti.
12ያም ወደብ ይከርሙበት ዘንድ የማይመች ስለ ሆነ፥ የሚበዙቱ ቢቻላቸው በሰሜንና በደቡብ ምዕራብ ትይዩ ወዳለው ፍንቄ ወደሚሉት ወደ ቀርጤስ ወደብ ደርሰው ይከርሙ ዘንድ ከዚያ እንዲነሡ መከሩ።
13Kai ėmė pūsti lengvas pietų vėjas, jie tikėjosi įvykdyti savo sumanymą ir, pakėlę inkarą, leidosi pirmyn palei Kretos krantus.
13ልከኛም የደቡብ ነፋስ በነፈሰ ጊዜ፥ እንዳሰቡት የሆነላቸው መስሎአቸው ተነሡ በቀርጤስም አጠገብ ጥግ ጥጉን አለፉ።
14Bet netrukus nuo salos pusės pakilo viesulas, vadinamas Šiauriaryčiu.
14ነገር ግን እጅግ ሳይዘገይ አውራቂስ የሚሉት ዓውሎ ነፋስ ከዚያ ወረደባቸው፤
15Jis pagavo laivą, nepajėgusį jam priešintis, ir mes turėjome jį leisti pavėjui.
15መርከቡም ተነጥቆ ነፋሱን ሲቃወም መሄድ ስላልቻለ ለቀነው ተነዳን።
16Kai mus nešė pro salelę, vardu Klaudą, mes tik vargais negalais išsaugojome gelbėjimo valtį.
16ቄዳ በሚሉአትም ደሴት በተተገንን ጊዜ ታንኳይቱን ለመግዛት በጭንቅ ቻልን፤
17Kai ji buvo užkelta, jūreiviai ėmė stiprinti laivą­apjuosė jį virvėmis. Bijodami pakliūti ant Sirtės seklumų, jie nuleido bures ir taip plaukė toliau.
17ወደ ላይም ካወጡአት በኋላ መርከቡን በገመድ አስታጥቀው አጸኑ፤ ስርቲስም ወደሚሉት ወደ አሸዋ እንዳይወድቁ ፈርተው ሸራውን አውርደው እንዲሁ ተነዱ።
18Mus baisiai vargino audra. Todėl rytojaus dieną teko išmesti į jūrą dalį krovinio.
18ነፋሱም በርትቶ ሲያስጨንቀን በማንግሥቱ ከጭነቱ ወደ ባሕር ይጥሉ ነበር፥
19Trečią dieną savo rankomis išmetėme kai kuriuos laivo įrengimus.
19በሦስተኛውም ቀን የመርከቡን ዕቃ በእጃችን ወረወርን።
20Ilgą laiką nematydami nei saulės, nei žvaigždžių, smarkios audros blaškomi, galiausiai praradome bet kokią viltį išsigelbėti.
20ብዙ ቀንም ፀሐይን ከዋክብትንም ሳናይ ትልቅ ነፋስም ሲበረታብን ጊዜ፥ ወደ ፊት እንድናለን የማለት ተስፋ ሁሉ ተቈረጠ።
21Žmonės jau ilgą laiką nieko nevalgė. Paulius, atsistojęs tarp jų, tarė: “Vyrai! Reikėjo paklausyti manęs ir neplaukti nuo Kretos į jūrą. Būtų išvengta šių pavojų ir nuostolių.
21ሳይበሉም ብዙ ቀን ከቆዩ በኋላ፥ ያን ጊዜ ጳውሎስ በመካከላቸው ቆሞ እንዲህ አለ። እናንተ ሰዎች ሆይ፥ ሰምታችሁኝ በሆነ ኖሮ ከቀርጤስ እንዳትነሡ ይህንም ጥፋትና ጕዳት እንዳታገኙ ይገባችሁ ነበር።
22Tačiau ir dabar raginu laikytis drąsiai. Niekas iš jūsų nežus, vien tik laivas.
22አሁንም። አይዞአችሁ ብዬ እመክራችኋለሁ፤ ይህ መርከብ እንጂ ከእናንተ አንድ ነፍስ እንኳ አይጠፋምና።
23Šią naktį mane aplankė angelas Dievo, kuriam aš priklausau ir tarnauju,
23የእርሱ የምሆንና ደግሞ የማመልከው የእግዚአብሔር መልአክ በዚች ሌሊት በአጠገቤ ቆሞ ነበርና፥ እርሱም።
24ir pasakė: ‘Nebijok, Pauliau! Tu privalai stoti prieš ciesorių. Ir štai Dievas tau dovanoja visus, plaukiančius su tavimi’.
24ጳውሎስ ሆይ፥ አትፍራ፤ በቄሣር ፊት ልትቆም ይገባሃል፤ እነሆም፥ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር የሚሄዱትን ሁሉ ሰጥቶሃል አለኝ።
25Tad, vyrai, drąsiau! Aš tikiu Dievu, kad taip ir įvyks, kaip man pasakyta.
25ስለዚህ እናንተ ሰዎች ሆይ፥ አይዞአችሁ፤ እንደ ተናገረኝ እንዲሁ እንዲሆን እግዚአብሔርን አምናለሁና።
26Mus išmes į kokią nors salą”.
26ነገር ግን ወደ አንዲት ደሴት እንድንወድቅ ያስፈልገናል።
27Kai buvome svaidomi Adrijos jūroje keturioliktą naktį, apie vidurnaktį jūreiviams pasirodė, kad artėjame prie kažkokios sausumos.
27በአሥራ አራተኛውም ሌሊት በአድርያ ባሕር ወዲህና ወዲያ ስንነዳ፥ መርከበኞች በእኩለ ሌሊት ወደ አንድ ምድር የቀረቡ መሰላቸው።
28Jie išmetė grimzlę ir nustatė dvidešimties sieksnių gylį; po kiek laiko išmatavo dar kartą ir berado penkiolika.
28መለኪያ ገመድም ቢጥሉ ሀያ በሰው ቁመት አገኙ ጥቂትም ቆይተው ሁለተኛ ቢጥሉ አሥራ አምስት በሰው ቁመት አገኙ፤
29Bijodami užšokti ant povandeninių uolų, jie išmetė iš paskuigalio keturis inkarus ir laukė aušros.
29ድንጋያማም ወደ ሆነ ስፍራ እንዳይወድቁ ፈርተው፥ ከመርከቡ በስተኋላ አራት መልሕቅ አወረዱ፥ ቀንም እንዲሆን ተመኙ።
30Jūreiviai mėgino pabėgti iš laivo. Jie nuleido į jūrą gelbėjimo valtį, neva norėdami išmesti inkarus laivo priešakyje.
30መርከበኞቹም ከመርከቡ ይሸሹ ዘንድ ፈልገው ከመርከቡ በስተ ፊት መልሕቅ መጣል እንዳላቸው አመካኝተው ታንኳይቱን ወደ ባሕር ባወረዱ ጊዜ፥
31Paulius tarė šimtininkui ir kareiviams: “Jeigu šitie nepasiliks laive, jūs neišsigelbėsite”.
31ጳውሎስ ለመቶ አለቃውና ለወታደሮቹ። እነዚህ በመርከቡ ካልቆዩ እናንተ ትድኑ ዘንድ አትችሉም አላቸው።
32Tada kareiviai nukapojo valties virves ir leido jai nukristi į jūrą.
32ያን ጊዜ ወታደሮቹ የታንኳይቱን ገመድ ቈርጠው ትወድቅ ዘንድ ተዉአት።
33Prieš rytą Paulius paragino visus valgyti, sakydamas: “Šiandien jau keturiolikta diena, kai jūs laukiate nevalgę, nieko burnoje neturėję.
33ቀንም ሲነጋ ጳውሎስ ምግብ ይበሉ ዘንድ ሁሉን ይለምን ነበር፥ እንዲህም አላቸው። እየጠበቃችሁ ምንም ሳትቀበሉ ጦማችሁን ከሰነበታችሁ ዛሬ አሥራ አራተኛ ቀናችሁ ነው።
34Todėl aš jus prašau valgyti. To reikia jūsų išsigelbėjimui. Nė vienam iš jūsų nenukris nė plaukas nuo galvos!”
34ሰለዚህ ምግብ ትበሉ ዘንድ እለምናችኋለሁ፤ ይህ ለደኅንነታችሁ ይሆናልና፤ ከእናንተ ከአንዱ የራስ ጠጕር እንኳ አትጠፋምና።
35Tai pasakęs, jis paėmė duonos, visų akivaizdoje padėkojo Dievui, sulaužė ir pradėjo valgyti.
35ይህንም ብሎ እንጀራን ይዞ በሁሉ ፊት እግዚአብሔርን አመሰገነ ቈርሶም ይበላ ዘንድ ጀመረ።
36Tada visi pralinksmėjo ir ėmėsi valgio.
36ሁለም ተጽናንተው ራሳቸው ደግሞ ምግብ ተቀበሉ።
37Laive iš viso buvome du šimtai septyniasdešimt šeši žmonės.
37በመርከቡም ያለን ሁላችን ሁለት መቶ ሰባ ስድስት ነፍስ ነበርን።
38Pavalgę jie palengvino laivą, išmesdami jūron javus.
38በልተውም በጠገቡ ጊዜ ስንዴውን ወደ ባሕር እየጣሉ መርከቡን አቃለሉት።
39Rytui išaušus, jūreiviai negalėjo pažinti žemės, tiktai pastebėjo nedidelę įlanką lėkštais krantais, į kurią, jei bus įmanoma, jie nutarė pasukti laivą.
39በነጋም ጊዜ ምድሩን አላወቁትም፥ ነገር ግን የአሸዋ ዳር ያለውን የባሕር ስርጥ ተመለከቱ፥ ቢቻላቸውም መርከቡን ወደዚያ ይገፉ ዘንድ ቈረጡ።
40Nupjovė inkarus, paliko juos jūroje, atleido vairo diržus ir, iškėlę prieš vėją priekinę burę, leidosi į krantą.
40መልሕቆቹንም ፈትተው በባሕር ተዉአቸው፥ ያን ጊዜም የመቅዘፊያውን ማሠሪያ ፈቱት፤ ታናሹንም ሸራ ለነፋስ ከፍ አድርገው ወደ ዳር አቅንተው ይሄዱ ዘንድ ጀመሩ።
41Atsidūrę prie seklumos, jie užšokdino ant jos laivą. Priekis liko tvirtai įsmigęs, o paskuigalis ėmė irti nuo smarkios bangų mūšos.
41ነገር ግን ሁለት ባሕር በተገናኙበት ስፍራ ወድቀው መርከቡን በዲብ ላይ ነዱ፤ በስተ ፊቱም ተተክሎ የማይነቃነቅ ሆነ፥ በስተ ኋላው ግን ከማዕበሉ ግፊያ የተነሣ ይሰበር ነበር።
42Kareiviai sumanė išžudyti kalinius, kad kuris išplaukęs nepaspruktų.
42ወታደሮቹም ከእስረኞች አንድ ስንኳ ዋኝቶ እንዳያመልጥ ይገድሉአቸው ዘንድ ተማከሩ።
43Bet šimtininkas, gelbėdamas Paulių, sutrukdė jų sumanymą. Jis įsakė, kad mokantys plaukti pirmi šoktų į jūrą ir plauktų į krantą,
43የመቶ አለቃው ግን ጳውሎስን ያድነው ዘንድ አስቦ ምክራቸውን ከለከለ፤ ዋና የሚያውቁትም ከመርከብ ራሳቸውን እየወረወሩ አስቀድመው ወደ ምድር ይወጡ ዘንድ፥
44o kiti tai padarytų kas ant lentų, kas ant laivo nuolaužų. Šitaip visi išsigelbėjo ir pasiekė žemę.
44የቀሩትም እኵሌቶቹ በሳንቃዎች ላይ እኵሌቶቹም በመርከቡ ስባሪ ይወጡ ዘንድ አዘዘ። እንዲሁም ሁሉ በደኅና ወደ ምድር ደረሱ።