1Išsigelbėję jie sužinojo, kad sala vadinasi Melitė.
1በደኅና ከደረስን በኋላ በዚያን ጊዜ ደሴቲቱ መላጥያ እንድትባል አወቅን።
2Barbarai su mumis elgėsi labai draugiškai. Užkūrė ugnį ir pakvietė mus visus prie jos, nes lijo ir buvo šalta.
2አረማውያንም የሚያስገርም ቸርነት አደረጉልን፤ ዝናብ ስለ ሆነም ስለ ብርዱም እሳት አንድደው ሁላችንን ተቀበሉን።
3Paulius pririnko glėbį sausų šakų ir metė į ugnį. Čia nuo kaitros iš laužo iššoko gyvatė ir įsikirto jam į ranką.
3ጳውሎስ ግን ብዙ ጭራሮ አከማችቶ ወደ እሳት ሲጨምር እፉኝት ከሙቀት የተነሣ ወጥታ እጁን ነደፈችው።
4Pamatę prie rankos prikibusią gyvatę, barbarai ėmė vienas kitam kalbėti: “Tas žmogus tikriausiai žmogžudys: išsigelbėjo iš jūros, o keršto deivė vis tiek neduoda jam gyventi”.
4አረማውያንም እባብ በእጁ ተንጠልጥላ ባዩ ጊዜ፥ እርስ በርሳቸው። ይህ ሰው በእርግጥ ነፍሰ ገዳይ ነው፥ ከባሕርም ስንኳ በደኅና ቢወጣ የእግዚአብሔር ፍርድ በሕይወት ይኖር ዘንድ አልተወውም አሉ።
5Tačiau jis nupurtė šliužą į ugnį, nepatirdamas nieko blogo.
5እርሱ ግን እባቢቱን ወደ እሳት አራገፋት አንዳችም አልጐዳችውም፤
6Barbarai laukė, kada jis ištins ar staiga kris negyvas. Laukę nesulaukę ir pamatę, kad jam nesidaro nieko blogo, jie pakeitė nuomonę ir ėmė kalbėti, jog jis esąs dievas.
6እነርሱም። ሊያብጥ ወይም ወዲያው ሞቶ ሊወድቅ ነው ብለው ይጠባበቁት ነበር ብዙ ጊዜ ግን ሲጠባበቁ በእርሱ ላይ የሚያስገርም ነገር ምንም ባላዩ ጊዜ። ይህስ አምላክ ነው ብለው አሳባቸውን ለወጡ።
7Netoli tos vietos buvo vyriausiojo salos valdininko, vardu Publijus, valdos. Jis mus priėmė ir tris dienas bičiuliškai globojo.
7በዚያም ስፍራ አጠገብ ፑፕልዮስ የሚሉት የደሴት አለቃ መሬት ነበረ፥ እርሱም እንግድነት ተቀብሎን ሦስት ቀን በፍቅር አሳደረን።
8Tuo metu Publijaus tėvas susirgo karštine ir viduriavimu. Paulius užėjo pas jį, pasimeldė, uždėjęs ant jo rankas, ir išgydė.
8የፑፕልዮስም አባት በንዳድና በተቅማጥ ታሞ ተኝቶ ነበር፤ ጳውሎስም ወደ እርሱ ገብቶ ጸለየለት እጁንም በላዩ ጭኖ ፈወሰው።
9Po šito įvykio ir kiti salos gyventojai, turėję ligų, ėjo pas Paulių ir buvo pagydomi.
9ይህም በሆነ ጊዜ የቀሩት ደግሞ በደሴቲቱ ደዌ የነበረባቸው እየመጡ ተፈወሱ፤
10Už tai jie mus didžiai gerbė, o išvykstant aprūpino viskuo, ko mums reikėjo.
10በብዙ ክብርም ደግሞ አከበሩን፥ በተነሣንም ጊዜ በመርከብ ላይ የሚያስፈልገንን ነገር አኖሩልን።
11Po trijų mėnesių mes išplaukėme žiemojusiu saloje Aleksandrijos laivu, kuris turėjo Dvynių ženklą.
11ከሦስት ወርም በኋላ በደሴቲቱ ከርሞ በነበረው በእስክንድርያው መርከብ ተነሣን፥ በእርሱም የዲዮስቆሮስ አላማ ነበረበት።
12Atplaukę į Sirakūzus, prastovėjome tris dienas.
12ወደ ሰራኩስም በገባን ጊዜ ሦስት ቀን ተቀመጥን፤
13Iš ten plaukdami, esant nepalankiam vėjui, pasiekėme Regijų ir dar po dienos, ėmus pūsti pietų vėjui, kitą dieną atvykome į Puteolus.
13ከዚያም እየተዛወርን ወደ ሬጊዩም ደረስን። ከአንድ ቀን በኋላም የደቡብ ነፋስ በነፈሰ ጊዜ በሁለተኛው ቀን ወደ ፑቲዮሉስ መጣን።
14Ten susitikome su broliais; jie pakvietė mus septynioms dienoms paviešėti. Taip mes atvykome į Romą.
14በዚያም ወንድሞችን አግኝተን በእነርሱ ዘንድ ሰባት ቀን እንድንቀመጥ ለመኑን፤ እንዲሁም ወደ ሮሜ መጣን።
15Tenykščiai broliai, išgirdę apie mus, atėjo pasitikti iki Apijaus aikštės ir Trijų tavernų. Juos išvydęs, Paulius dėkojo Dievui ir įgavo naujo pasitikėjimo.
15ከዚያም ወንድሞች ስለ እኛ ሰምተው እስከ አፍዩስ ፋሩስና ሦስት ማደሪያ እስከሚባለው ሊቀበሉን ወጡ፥ ጳውሎስም ባያቸው ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገነ ልቡም ተጽናና።
16Kai atvykome į Romą, šimtininkas perdavė kalinius sargybos viršininkui, o Pauliui buvo leista apsigyventi vienam su saugojančiu jį kareiviu.
16ወደ ሮሜም በገባን ጊዜ ጳውሎስ ከሚጠብቀው ወታደር ጋር ለብቻው ይቀመጥ ዘንድ ተፈቀደለት።
17Po trijų dienų Paulius pakvietė pas save žydų vadovus. Jiems susirinkus, jis prabilo: “Vyrai broliai! Nors aš nieku nesu nusikaltęs nei tautai, nei mūsų tėvų papročiams, buvau Jeruzalėje suimtas ir atiduotas į romėnų rankas.
17ከሦስት ቀንም በኋላ ጳውሎስ የአይሁድን ታላላቆች ወደ እርሱ ጠራ፤ በተሰበሰቡም ጊዜ እንዲህ አላቸው። ወንድሞች ሆይ፥ እኔ ሕዝቡን ወይም የአባቶችን ሥርዓት የሚቃወም አንዳች ሳላደርግ፥ ከኢየሩሳሌም እንደ ታሰርሁ በሮማውያን እጅ አሳልፈው ሰጡኝ።
18Tie ištardę, norėjo mane paleisti, nes nerado jokio mirties verto nusižengimo.
18እነርሱም መርምረው ለሞት የሚገባ ምክንያት ስላልነበረብኝ ሊፈቱኝ አሰቡ፤
19Kadangi žydai prieštaravo, turėjau šauktis ciesoriaus, tiktai ne tam, kad apkaltinčiau savo tautą.
19አይሁድ ግን በተቃወሙ ጊዜ፥ ወደ ቄሣር ይግባኝ እንድል ግድ ሆነብኝ እንጂ ሕዝቤን የምከስበት ነገር ኖሮኝ አይደለም።
20Dėl šios priežasties ir pakviečiau jus, kad su jumis pasimatyčiau ir pasikalbėčiau; nes dėl Izraelio vilties esu surakintas šita grandine!”
20ስለዚህም ምክንያት አያችሁና እነግራችሁ ዘንድ ጠራኋችሁ፤ ስለ እስራኤል ተስፋ ይህን ሰንሰለት ለብሻለሁና።
21Jie atsakė jam: “Mes nesame gavę apie tave iš Judėjos laiškų, ir nė vienas iš atvykusių brolių nepranešė ir nekalbėjo nieko blogo apie tave.
21እነርሱም። እኛ ከይሁዳ ስለ አንተ ደብዳቤ አልተቀበልንም፥ ከወንድሞችም አንድ ስንኳ መጥቶ ስለ አንተ ክፉ ነገር አላወራልንም ወይም አልተናገረብህም።
22Vis dėlto norėtume išgirsti tavo pažiūras. Mat apie šitą sektą tiek težinome, jog jai visur prieštaraujama”.
22ነገር ግን ስለዚህ ወገን በየስፍራው ሁሉ እንዲቃወሙ በእኛ ዘንድ ታውቆአልና የምታስበውን ከአንተ እንሰማ ዘንድ እንፈቅዳለን አሉት።
23Paskyrę jam dieną, jie gausiai susirinko pas jį svečių kambaryje. Nuo ryto iki vakaro jis aiškino jiems ir liudijo apie Dievo karalystę, įrodinėdamas jiems Jėzų iš Mozės Įstatymo ir Pranašų.
23ቀንም ቀጥረውለት ብዙ ሆነው ወደ መኖሪያው ወደ እርሱ መጡ፤ ስለ እግዚአብሔር መንግሥትም እየመሰከረ ስለ ኢየሱስም ከሙሴ ሕግና ከነቢያት ጠቅሶ እያስረዳቸው፥ ከጥዋት ጀምሮ እስከ ማታ ድረስ ይገልጥላቸው ነበር።
24Vieni jo žodžiais patikėjo, kiti ne.
24እኵሌቶቹም የተናገረውን አመኑ፥ እኵሌቶቹ ግን አላመኑም፤
25Nesutardami tarpusavyje, jie ėmė skirstytis, o Paulius tepasakė jiems viena: “Teisingai Šventoji Dvasia yra mūsų tėvams pasakiusi per pranašą Izaiją:
25እርስ በርሳቸውም ባልተስማሙ ጊዜ፥ ጳውሎስ አንዲት ቃል ከተናገረ በኋላ ሄዱ፤ እንዲህም አለ። መንፈስ ቅዱስ በነቢዩ በኢሳይያስ ለአባቶቻችን።
26‘Eik pas šitą tautą ir sakyk: girdėti girdėsite, bet nesuprasite, žiūrėti žiūrėsite, bet nematysite.
26ወደዚህ ሕዝብ ሂድና። መስማትን ትሰማላችሁና አታስተውሉም፥ ማየትንም ታያላችሁና አትመለከቱም፤
27Šitų žmonių širdis aptuko, jie prastai girdėjo ausimis ir užmerkė akis, kad kartais nepamatytų akimis, neišgirstų ausimis, nesuprastų širdimi ir neatsiverstų, ir Aš jų nepagydyčiau’.
27በዓይናቸው እንዳያዩ በጆሮአቸው እንዳይሰሙ በልባቸውም እንዳያስተውሉ ተመልሰውም እንዳልፈውሳቸው፥ የዚህ ሕዝብ ልብ ደንድኖአል ጆሮአቸውም ደንቁሮአል ዓይናቸውንም ጨፍነዋል በላቸው
28Tebūnie tad jums žinoma: šis Dievo išgelbėjimas yra pasiųstas pagonims, ir jie išgirs”.
28ሲል መልካም ተናገረ። እንግዲህ ይህ የእግዚአብሔር ደኅንነት ለአሕዛብ እንደ ተላከ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን፤ እነርሱ ደግሞ ይሰሙታል።
29Jam tai pasakius, žydai išėjo, smarkiai ginčydamiesi tarpusavyje.
29ይህንም በተናገረ ጊዜ አይሁድ እርስ በርሳቸው እጅግ እየተከራከሩ ሄዱ።
30Paulius gyveno savo išsinuomotame name ištisus dvejus metus ir priiminėdavo visus, kurie pas jį ateidavo.
30ጳውሎስም በተከራየው ቤት ሁለት ዓመት ሙሉ ተቀመጠ፥ ወደ እርሱም የሚመጡትን ሁሉ ይቀበል ነበር፤
31Jis skelbė Dievo karalystę ir labai drąsiai, netrukdomas mokė apie Viešpatį Jėzų Kristų.
31ማንም ሳይከለክለው የእግዚአብሔርን መንግሥት እየሰበከ ስለ ጌታ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እጅግ ገልጦ ያስተምር ነበር።