Lithuanian

Amharic: New Testament

Colossians

3

1Jeigu esate su Kristumi prikelti, siekite to, kas aukštybėse, kur Kristus sėdi Dievo dešinėje.
1እንግዲህ ከክርስቶስ ጋር ከተነሣችሁ፥ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ ባለበት በላይ ያለውን እሹ።
2Mąstykite apie tai, kas aukštybėse, o ne apie tai, kas žemėje.
2በላይ ያለውን አስቡ እንጂ በምድር ያለውን አይደለም።
3Jūs juk esate mirę, ir jūsų gyvenimas su Kristumi yra paslėptas Dieve.
3ሞታችኋልና፥ ሕይወታችሁም በእግዚአብሔር ከክርስቶስ ጋር ተሰውሮአልና።
4Kai pasirodys Kristus­mūsų gyvenimas, tada su Juo ir jūs pasirodysite šlovėje.
4ሕይወታችሁ የሆነ ክርስቶስ በሚገለጥበት ጊዜ፥ በዚያን ጊዜ እናንተ ደግሞ ከእርሱ ጋር በክብር ትገለጣላችሁ።
5Todėl marinkite tuos savo narius, kurie yra žemėje: ištvirkavimą, netyrumą, aistringumą, piktą pageidimą, taip pat godumą, kuris yra stabmeldystė.
5እንግዲህ በምድር ያሉቱን ብልቶቻችሁን ግደሉ፥ እነዚህም ዝሙትና ርኵሰት ፍትወትም ክፉ ምኞትም ጣኦትንም ማምለክ የሆነ መጎምጀት ነው።
6Dėl šių dalykų ateina Dievo rūstybė neklusnumo vaikams.
6በእነዚህም ጠንቅ የእግዚአብሔር ቍጣ በማይታዘዙ ልጆች ላይ ይመጣል።
7Jūs irgi kadaise taip elgėtės, gyvendami tarp jų.
7እናንተም ደግሞ ትኖሩባቸው በነበራችሁ ጊዜ፥ በፊት በእነዚህ ተመላለሳችሁ።
8Bet dabar jūs visa tai nusivilkite: rūstybę, nirtulį, nelabumą, pyktį, piktžodžiavimą, nešvarias kalbas nuo savo lūpų.
8አሁን ግን እናንተ ደግሞ ቍጣንና ንዴትን ክፋትንም፥ ከአፋችሁም ስድብን የሚያሳፍርንም ንግግር እነዚህን ሁሉ አስወግዱ።
9Nebemeluokite vienas kitam, nusivilkę senąjį žmogų su jo darbais
9እርስ በርሳችሁ ውሸት አትነጋገሩ፥ አሮጌውን ሰው ከሥራው ጋር ገፋችሁታልና፥
10ir apsivilkę nauju, kuris atnaujinamas pažinimu pagal atvaizdą To, kuris jį sukūrė.
10የፈጠረውንም ምሳሌ እንዲመስል እውቀትን ለማግኘት የሚታደሰውን አዲሱን ሰው ለብሳችሁታል።
11Čia jau nebėra nei graiko, nei žydo, nei apipjaustyto, nei neapipjaustyto, nei barbaro, nei skito, nei vergo, nei laisvojo, bet visa ir visuose­Kristus.
11በዚያም የግሪክ ሰው አይሁዳዊም የተገረዘም ያልተገረዘም አረማዊም እስኩቴስም ባሪያም ጨዋ ሰውም መሆን አልተቻለም፥ ነገር ግን ክርስቶስ ሁሉ ነው፥ በሁሉም ነው።
12Todėl, kaip Dievo išrinktieji, šventieji ir numylėtiniai, apsivilkite nuoširdžiu gailestingumu, gerumu, nuolankumu, romumu ir ištverme.
12እንግዲህ እንደ እግዚአብሔር ምርጦች ቅዱሳን ሆናችሁ የተወደዳችሁም ሆናችሁ፥ ምሕረትን፥ ርኅራኄን፥ ቸርነትን፥ ትህትናን፥ የዋህነትን፥ ትዕግሥትን ልበሱ።
13Būkite vieni kitiems pakantūs ir atleiskite vieni kitiems, jei vienas prieš kitą turite skundą. Kaip Kristus atleido, taip ir jūs atleiskite.
13እርስ በርሳችሁ ትዕግሥትን አድርጉ፥ ማንም በባልንጀራው ላይ የሚነቅፈው ነገር ካለው፥ ይቅር ተባባሉ። ክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉ።
14O virš viso šito apsivilkite meile, kuri yra tobulumo raištis.
14በእነዚህም ሁሉ ላይ የፍጻሜ ማሰሪያ የሆነውን ፍቅርን ልበሱት።
15Jūsų širdyse teviešpatauja Dievo ramybė, į kurią esate pašaukti viename kūne. Ir būkite dėkingi.
15በአንድ አካልም የተጠራችሁለት ደግሞ የክርስቶስ ሰላም በልባችሁ ይግዛ። የምታመሰግኑም ሁኑ።
16Kristaus žodis tegul tarpsta jumyse. Mokykite ir įspėkite vieni kitus visokeriopa išmintimi, su dėkinga širdimi giedokite Viešpačiui psalmes, himnus ir dvasines giesmes.
16የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ። በጥበብ ሁሉ እርስ በርሳችሁ አስተምሩና ገሥጹ። በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ በጸጋው በልባችሁ ለእግዚአብሔር ዘምሩ።
17Ir visa, ką bedarytumėte žodžiu ar darbu, visa darykite Viešpaties Jėzaus vardu, per Jį dėkodami Dievui Tėvui.
17እግዚአብሔር አብን በእርሱ እያመሰገናችሁ፥ በቃል ቢሆን ወይም በሥራ የምታደርጉትን ሁሉ በጌታ በኢየሱስ ስም አድርጉት።
18Jūs, žmonos, būkite atsidavusios savo vyrams, kaip dera Viešpatyje.
18ሚስቶች ሆይ፥ በጌታ እንደሚገባ ለባሎቻችሁ ተገዙ።
19O jūs, vyrai, mylėkite savo žmonas ir nebūkite joms šiurkštūs.
19ባሎች ሆይ፥ ሚስቶቻችሁን ውደዱ መራራም አትሁኑባቸው።
20Jūs, vaikai, visuose dalykuose klausykite savo tėvų, nes tai patinka Viešpačiui.
20ልጆች ሆይ፥ ይህ ለጌታ ደስ የሚያሰኝ ነውና በሁሉ ለወላጆቻችሁ ታዘዙ።
21O jūs, tėvai, neerzinkite savo vaikų, kad jie nepasidarytų baukštūs.
21አባቶች ሆይ፥ ልባቸው እንዳይዝል ልጆቻችሁን አታበሳጩአቸው።
22Jūs, vergai, visame kame pakluskite savo šeimininkams pagal kūną, ne dėl akių tarnaudami, kaip žmonėms patikti norėdami, bet iš tyros širdies, bijodami Dievo.
22ባሪያዎች ሆይ፥ በቅን ልብ ጌታን እየፈራችሁ እንጂ፥ ለሰው ደስ እንደምታሰኙ ለታይታ የምትገዙ ሳትሆኑ፥ በሥጋ ጌቶቻችሁ ለሆኑ በሁሉ ታዘዙ።
23Ir ką tik darytumėte, darykite iš širdies, kaip Viešpačiui, o ne žmonėms,
23ለሰው ሳይሆን ለጌታ እንደምታደርጉ፥ የምታደርጉትን ሁሉ በትጋት አድርጉት፥
24žinodami, kad iš Viešpaties gausite palikimą kaip atlyginimą,­ nes jūs tarnaujate Viešpačiui Kristui.
24ከጌታ የርስትን ብድራት እንድትቀበሉ ታውቃላችሁና። የምታገለግሉት ጌታ ክርስቶስ ነውና።
25O kas daro neteisybę, susilauks atlygio už tai, ką padarė, ir nebus žiūrima asmens.
25የሚበድልም የበደለውን በብድራት ይቀበላል፥ ለሰው ፊትም አድልዎ የለም።