Lithuanian

Amharic: New Testament

Galatians

3

1O neprotingi galatai! Kas jus, kuriems akivaizdžiai buvo nupieštas Jėzus Kristus tarsi pas jus nukryžiuotas, apkerėjo, kad nepaklustumėte tiesai?
1የማታስተውሉ የገላትያ ሰዎች ሆይ፥ በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ተሥሎ ነበር፤ ለእውነት እንዳትታዘዙ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው?
2Noriu jus paklausti tiktai vieno dalyko: ar jūs gavote Dvasią įstatymo darbais, ar klausydami tikėjimo?
2ይህን ብቻ ከእናንተ እንድማር እወዳለሁ፤ በሕግ ሥራ ወይም ከእምነት ጋር በሆነ መስማት መንፈስን ተቀበላችሁን?
3Nejaugi jūs tokie neprotingi, kad, pradėję Dvasia, dabar užbaigsite kūnu?
3እንዲህን የማታስተውሉ ናችሁ? በመንፈስ ጀምራችሁ አሁን በሥጋ ትፈጽማላችሁን?
4Ar tiek daug iškentėjote veltui? Jei iš tiesų būtų veltui!
4በውኑ ከንቱ እንደ ሆነስ እንደዚህ ያለ መከራ በከንቱ ተቀበላችሁን?
5Ar Tas, kuris jums teikia Dvasią ir pas jus daro stebuklus, tai daro per įstatymo darbus, ar dėl tikėjimo klausymo?
5እንግዲህ መንፈስን የሚሰጣችሁ በእናንተም ዘንድ ተአምራት የሚያደርግ፥ በሕግ ሥራ ነውን ወይስ ከእምነት ጋር በሆነ መስማት ነው?
6Taip “Abraomas patikėjo Dievu, ir tai jam buvo įskaityta teisumu”.
6እንዲሁ አብርሃም በእግዚአብሔር አመነና ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት።
7Todėl supraskite, kad Abraomo sūnūs yra tie, kurie tiki.
7እንኪያስ ከእምነት የሆኑት እነዚህ የአብርሃም ልጆች እንደ ሆኑ እወቁ።
8Ir Raštas, numatydamas, kad Dievas tikėjimu išteisins pagonis, iš anksto paskelbė Abraomui Evangeliją: “Tavyje bus palaimintos visos tautos”.
8መጽሐፍም እግዚአብሔር አሕዛብን በእምነት እንዲያጸድቅ አስቀድሞ አይቶ። በአንተ አሕዛብ ሁሉ ይባረካሉ ብሎ ወንጌልን ለአብርሃም አስቀድሞ ሰበከ።
9Taip tikintys susilaukia palaiminimo kartu su tikinčiuoju Abraomu.
9እንደዚህ ከእምነት የሆኑት ካመነው ከአብርሃም ጋር ይባረካሉ።
10Visi, kurie remiasi įstatymo darbais, yra prakeikimo galioje, nes parašyta: “Prakeiktas kiekvienas, kuris nuolatos nesilaiko visko, kas įstatymo knygoje parašyta, ir to nevykdo”.
10ከሕግ ሥራ የሆኑት ሁሉ በእርግማን በታች ናቸውና፤ በሕግ መጽሐፍ በተጻፉት ሁሉ ጸንቶ የማይኖር የማያደርግም ሁሉ የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፎአልና።
11Kad įstatymu niekas neišteisinamas Dievo akyse, aišku, nes “teisusis gyvens tikėjimu”.
11ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎአልና ማንም በእግዚአብሔር ፊት በሕግ እንዳይጸድቅ ግልጥ ነው።
12O įstatymas nėra kilęs iš tikėjimo, bet “kas juos vykdo, tas gyvens jais”.
12ሕግም ከእምነት አይደለም ነገር ግን። የሚያደርገው ይኖርበታል ተብሎአል።
13Kristus mus atpirko iš įstatymo prakeikimo, tapdamas už mus prakeikimu, nes parašyta: “Prakeiktas kiekvienas, kuris kybo ant medžio”,­
13በእንጨት የሚሰቀል ሁሉ የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፎአልና ክርስቶስ ስለ እኛ እርግማን ሆኖ ከሕግ እርግማን ዋጀን፤
14kad Abraomo palaiminimas Jėzuje Kristuje atitektų pagonims ir mes tikėjimu gautume pažadėtąją Dvasią.
14የመንፈስን ተስፋ በእምነት እንድንቀበል፥ የአብርሃም በረከት ወደ አሕዛብ በኢየሱስ ክርስቶስ ይደርስላቸው ዘንድ።
15Broliai, kalbu, kaip įprasta žmonėms: net žmogaus testamento, kuris patvirtintas, niekas neatmeta ir nepapildo.
15ወንድሞች ሆይ፥ እንደ ሰው ልማድ እላለሁ። የሰው ስንኳ ቢሆን እርግጠኛውን ኪዳን ማንም አይንቅም ወይም አይጨምርበትም።
16Pažadai buvo duoti Abraomui ir jo palikuoniui. Jis nesako “ir palikuonims”, ne daugeliui, bet kaip apie vieną: “ir tavo palikuoniui”, kuris yra Kristus.
16ለአብርሃምና ለዘሩም የተስፋው ቃል ተነገረ። ስለ ብዙዎች እንደሚነገር። ለዘሮቹም አይልም፤ ስለ አንድ እንደሚነገር ግን። ለዘርህም ይላል፥ እርሱም ክርስቶስ።
17Noriu pasakyti, kad Dievo Kristuje anksčiau patvirtinto testamento negali panaikinti po keturių šimtų trisdešimties metų atsiradęs įstatymas, ir jis negali pažado paversti negaliojančiu.
17ይህንም እላለሁ፤ ከአራት መቶ ሠላሳ ዓመት በኋላ የተሰጠው ሕግ አስቀድሞ በእግዚአብሔር የተረጋገጠውን ኪዳን የተስፋውን ቃል እስኪሽር ድረስ አያፈርስም።
18Jei paveldėjimas būtų iš įstatymo, tai jau nebe iš pažado, o Dievas davė tai Abraomui pažadu.
18ርስቱ በሕግ ቢሆንስ እንግዲያስ በተስፋ ቃል አይሆንም፤ በተስፋ ቃል ግን እግዚአብሔር ለአብርሃም ሰጥቶአል።
19Tad kam gi reikalingas įstatymas? Jis buvo pridėtas dėl nusižengimų, kol ateis palikuonis, kuriam buvo skirtas pažadas; įstatymas buvo perduotas per angelus, tarpininko ranka.
19እንግዲህ ሕግ ምንድር ነው? ተስፋው የተሰጠው ዘር እስኪመጣ ድረስ በመካከለኛ እጅ በመላእክት በኩል ስለ ሕግ መተላለፍ ተጨመረ።
20Tarpininkas neatstovauja vienai pusei, bet Dievas yra vienas.
20መካከለኛውም ለአንድ ብቻ አይደለም እግዚአብሔር ግን አንድ ነው።
21Tad gal įstatymas priešingas Dievo pažadams? Anaiptol! Jei būtų duotas įstatymas, galintis suteikti gyvenimą, tai iš tikrųjų teisumas būtų iš įstatymo.
21እንግዲህ ሕግ የእግዚአብሔርን የተስፋ ቃል የሚቃወም ነውን? አይደለም። ሕያው ሊያደርግ የሚቻለው ሕግ ተሰጥቶ ቢሆንስ በእውነት ጽድቅ ከሕግ በሆነ ነበር፤
22Bet Raštas viską apjuosė nuodėme, kad pažadas dėl tikėjimo Jėzumi Kristumi tektų tiems, kurie tiki.
22ነገር ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ከማመን የሆነው የተስፋ ቃል ለሚያምኑ ይሰጥ ዘንድ መጽሐፍ ከኃጢአት በታች ሁሉን ዘግቶታል።
23Prieš ateinant tikėjimui, buvome įstatymo įkalinti, kad lauktume apsireiškiant tikėjimo.
23እምነትም ሳይመጣ ሊገለጥ ላለው እምነት ተዘግተን ከሕግ በታች እንጠበቅ ነበር።
24Todėl įstatymas buvo mūsų auklėtojas, vedęs į Kristų, kad būtume tikėjimu išteisinti.
24እንደዚህ በእምነት እንጸድቅ ዘንድ ሕግ ወደ ክርስቶስ የሚያመጣ ሞግዚታችን ሆኖአል፤
25Bet, tikėjimui atėjus, jau nesame auklėtojo globoje.
25እምነት ግን መጥቶአልና ከእንግዲህ ወዲህ ከሞግዚት በታች አይደለንም።
26Juk jūs visi esate Dievo sūnūs per tikėjimą Jėzumi Kristumi.
26በእምነት በኩል ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁና፤
27Ir visi, kurie esate pakrikštyti Kristuje, apsivilkote Kristumi.
27ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋልና።
28Nebėra nei žydo, nei graiko; nebėra nei vergo, nei laisvojo; nebėra nei vyro, nei moters: visi esate viena Kristuje Jėzuje!
28አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም፥ ባሪያ ወይም ጨዋ ሰው የለም፥ ወንድም ሴትም የለም፤ ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁና።
29O jeigu esate Kristaus, tai esate Abraomo palikuonys ir paveldėtojai pagal pažadą.
29እናንተም የክርስቶስ ከሆናችሁ እንኪያስ የአብርሃም ዘር እንደ ተስፋውም ቃል ወራሾች ናችሁ።