1Dabar pasakysiu: kol paveldėtojas vaikas, jis nieku nesiskiria nuo vergo, nors yra visko šeimininkas;
1ነገር ግን እላለሁ፥ ወራሹ ሕፃን ሆኖ ባለበት ዘመን ሁሉ፥ ምንም የሁሉ ጌታ ቢሆን ከቶ ከባሪያ አይለይም፥
2jis esti globėjų ir prižiūrėtojų valdžioje iki tėvo nustatyto meto.
2ነገር ግን አባቱ እስከ ቀጠረለት ቀን ድረስ ከጠባቂዎችና ከመጋቢዎች በታች ነው።
3Taip buvo ir su mumis: kol buvome vaikai, turėjome vergauti pasaulio pradmenims.
3እንዲሁ እኛ ደግሞ ሕፃናት ሆነን ሳለን ከዓለም መጀመሪያ ትምህርት በታች ተገዝተን ባሪያዎች ነበርን፤
4Bet, atėjus laiko pilnatvei, Dievas atsiuntė savo Sūnų, gimusį iš moters, pavaldų įstatymui,
4ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤
5kad atpirktų esančius įstatymo valdžioje ir kad mes įgytume įsūnystę.
5እንደ ልጆች እንሆን ዘንድ፥ ከሕግ በታች ያሉትን ይዋጅ ዘንድ።
6O kadangi esate sūnūs, Dievas atsiuntė į mūsų širdis savo Sūnaus Dvasią, kuri šaukia: “Aba, Tėve!”
6ልጆችም ስለ ሆናችሁ እግዚአብሔር አባ አባት ብሎ የሚጮኽ የልጁን መንፈስ በልባችሁ ውስጥ ላከ።
7Taigi tu jau nebe vergas, bet sūnus; o jeigu sūnus, tai ir Dievo paveldėtojas per Kristų.
7ስለዚህ ከእንግዲህ ወዲህ ልጅ ነህ እንጂ ባሪያ አይደለህም፤ ልጅም ከሆንህ ደግሞ በክርስቶስ የእግዚአብሔር ወራሽ ነህ።
8Kitados, dar nepažindami Dievo, jūs vergavote dievams, kurie iš tikro nėra dievai.
8ነገር ግን በዚያን ጊዜ እግዚአብሔርን ሳታውቁ በባሕርያቸው አማልክት ለማይሆኑ ባሪያዎች ሆናችሁ ተገዛችሁ፤
9Bet dabar, pažinę Dievą arba, geriau sakant, Dievo pažinti, kaipgi galite grįžti prie menkų ir vargingų pradmenų, kuriems ir vėl norite vergauti?!
9አሁን ግን እግዚአብሔርን ስታውቁ ይልቅስ በእግዚአብሔር ስትታወቁ እንደ ገና ወደ ደካማ ወደሚናቅም ወደ መጀመሪያ ትምህርት እንዴት ትመለሳላችሁ? እንደ ገና ባሪያዎች ሆናችሁ ዳግመኛ ለዚያ ልትገዙ ትወዳላችሁን?
10Jūs laikotės dienų, mėnesių, laikotarpių, metų.
10ቀንንና ወርን ዘመንንም ዓመትንም በጥንቃቄ ትጠብቃላችሁ።
11Aš baiminuosi dėl jūsų, kad kartais nebūčiau veltui dirbęs jūsų labui.
11ምናልባት በከንቱ ለእናንተ ደክሜአለሁ ብዬ እፈራችኋለሁ።
12Prašau jus, broliai, tapkite tokie kaip aš, nes ir aš tapau toks kaip jūs. Jūs visai neįžeidėte manęs.
12ወንድሞች ሆይ፥ እኔ ደግሞ እንደ እናንተ ሆኜአለሁና። እንደ እኔ ሁኑ ብዬ እለምናችኋለሁ። አንዳችም አልበደላችሁኝም።
13Jūs žinote, kad jums pirmą kartą paskelbiau Evangeliją negaluodamas kūnu.
13በመጀመሪያ ወንጌልን በሰበክሁላችሁ ጊዜ ከሥጋ ድካም የተነሣ እንደ ነበረ ታውቃላችሁ፥
14Ir jūs nepaniekinote ir nepasipiktinote mano kūne esančiu išbandymu, bet priėmėte mane kaip Dievo angelą, kaip patį Kristų Jėzų.
14በሥጋዬም ፈተና የሆነባችሁን ነገር አልናቃችሁትምና አልተጸየፋችሁትም ነገር ግን እንደ እግዚአብሔር መልአክ አዎን እንደ ክርስቶስ ኢየሱስ ተቀበላችሁኝ።
15Koks tai buvo palaiminimas jums! Aš galiu paliudyti, kad įmanydami būtumėte išlupę savo akis ir atidavę man.
15እንግዲህ ደስ ማሰኘታችሁ ወዴት አለ? ቢቻልስ ዓይኖቻችሁን አውጥታችሁ በሰጣችሁኝ ብዬ እመሰክርላችኋለሁ።
16Nejaugi tapau jūsų priešu, kalbėdamas jums tiesą?
16እንኪያስ እውነቱን ስለ ነገርኋችሁ ጠላት ሆንሁባችሁን?
17Jie uolūs ne jūsų labui, bet norėtų jus atskirti, kad būtumėte uolūs dėl jų.
17በብርቱ ይፈልጉአችኋል፥ ለመልካም አይደለም ነገር ግን በብርቱ ትፈልጉአቸው ዘንድ በውጭ ሊያስቀሩአችሁ ይወዳሉ።
18Bet gerai visada būti uoliems dėl gero, o ne vien kai esu pas jus.
18ነገር ግን ከእናንተ ዘንድ በምኖርበት ጊዜ ብቻ ሳይሆን ሁልጊዜ በመልካም ነገር ተፈላጊ ብትሆኑ መልካም ነው።
19Mano vaikeliai, dėl jūsų aš vėl gimdymo skausmuose, kol jumyse išryškės Kristus!
19ልጆቼ ሆይ፥ ክርስቶስ በእናንተ እስኪሣል ድረስ ዳግመኛ ስለ እናንተ ምጥ ይዞኛል።
20Norėčiau dabar būti pas jus ir prabilti kitaip, nes nežinau, ką man su jumis daryti.
20ስለ እናንተ አመነታለሁና አሁን በእናንተ ዘንድ ሆኜ ድምፄን ልለውጥ በወደድሁ።
21Pasakykite man jūs, norintieji būti įstatymo valdžioje, ar negirdite įstatymo?
21እናንተ ከሕግ በታች ልትኖሩ የምትወዱ፥ ሕጉን አትሰሙምን? እስኪ ንገሩኝ።
22Juk parašyta, kad Abraomas turėjo du sūnus: vieną iš vergės, o kitą iš laisvosios.
22አንዱ ከባሪያይቱ አንዱም ከጨዋይቱ የሆኑ ሁለት ልጆች ለአብርሃም እንደ ነበሩት ተጽፎአልና።
23Vergės sūnus buvo gimęs pagal kūną, o laisvosiospagal pažadą.
23ነገር ግን የባሪያይቱ ልጅ እንደ ሥጋ ተወልዶአል፥ የጨዋይቱ ግን በተስፋው ቃል ተወልዶአል።
24Tai pasakyta perkeltine prasme: jostai dvi Sandoros. Viena nuo Sinajaus kalno, gimdanti vergystei,tai Hagara.
24ይህም ነገር ምሳሌ ነው፤ እነዚህ ሴቶች እንደ ሁለቱ ኪዳኖች ናቸውና። ከደብረ ሲና የሆነችው አንዲቱ ለባርነት ልጆችን ትወልዳለች፥ እርስዋም አጋር ናት።
25Hagara yra Sinajaus kalnas Arabijoje; ji atitinka dabartinę Jeruzalę, kuri vergauja su savo vaikais.
25ይህችም አጋር በዓረብ ምድር ያለችው ደብረ ሲና ናት፤ አሁንም ያለችውን ኢየሩሳሌምን ትመስላለች፥ ከልጆችዋ ጋር በባርነት ናትና።
26Bet aukštybių Jeruzalė laisva, ji yra visų mūsų motina,
26ላይኛይቱ ኢየሩሳሌም ግን በነጻነት የምትኖር ናት እርስዋም እናታችን ናት።
27nes parašyta: “Pralinksmėk, nevaisingoji, kuri negimdei! Šūkauk ir džiūgauk, nepažinusi kentėjimų! Nes apleistoji turi daug daugiau vaikų negu turinčioji vyrą”.
27አንቺ የማትወልጅ መካን፥ ደስ ይበልሽ፤ አንቺ አምጠሽ የማታውቂ፥ እልል በዪና ጩኺ፤ ባል ካላቱ ይልቅ የብቸኛይቱ ልጆች በዝተዋልና ተብሎ ተጽፎአል።
28Mes, broliai, esame pažado vaikai kaip Izaokas.
28እኛም፥ ወንድሞች ሆይ፥ እንደ ይስሐቅ የተስፋ ቃል ልጆች ነን።
29Bet kaip tada gimęs pagal kūną persekiojo gimusį pagal Dvasią, taip ir dabar.
29ነገር ግን እንደ ሥጋ የተወለደው እንደ መንፈስ የተወለደውን በዚያን ጊዜ እንዳሳደደው ዛሬም እንዲሁ ነው።
30O ką gi sako Raštas?“Išvaryk vergę ir jos sūnų, nes vergės sūnus negaus palikimo kartu su laisvosios sūnumi”.
30ነገር ግን መጽሐፍ ምን ይላል? የባሪያይቱ ልጅ ከጨዋይቱ ልጅ ጋር አይወርስምና ባሪያይቱን ከልጅዋ ጋር አውጣት።
31Taigi, broliai, mes nesame vergės vaikai, bet laisvosios.
31ስለዚህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ የጨዋይቱ ልጆች ነን እንጂ የባሪያይቱ አይደለንም።