Lithuanian

Amharic: New Testament

Hebrews

10

1Kadangi Įstatymas turi tiktai būsimųjų gėrybių šešėlį, o ne patį dalykų vaizdą, jis niekada negali tomis pačiomis aukomis, kurios kasmet vis aukojamos ir aukojamos, padaryti tobulus tuos, kurie artinasi.
1ሕጉ ሊመጣ ያለው የበጎ ነገር እውነተኛ አምሳል ሳይሆን የነገር ጥላ አለውና፥ ስለዚህም በየዓመቱ ዘወትር በሚያቀርቡት በዚያ መሥዋዕት የሚቀርቡትን ሊፈጽም ከቶ አይችልም።
2Argi tos aukos nesiliautų, jeigu aukotojai, vienąkart apvalyti, daugiau nebejaustų sąžinėje nuodėmių?
2እንደዚህማ ባይሆን፥ የሚያመልኩት አንድ ጊዜ ነጽተው ከዚያ በኋላ በሕሊናቸው ኃጢአትን ስላላወቁ ማቅረብን በተዉ አልነበረምን?
3Priešingai: jos metai iš metų vis primena nuodėmes.
3ነገር ግን በዚያ መሥዋዕት በየዓመቱ የኃጢአት መታሰቢያ አለ፤
4Juk neįmanoma, kad jaučių ir ožių kraujas panaikintų nuodėmes.
4የኮርማዎችና የፍየሎች ደም ኃጢአትን እንዲያስወግድ የማይቻል ነውና።
5Todėl, ateidamas į pasaulį, Jis sako: “Aukų ir atnašų Tu nenorėjai, bet paruošei man kūną.
5ስለዚህ ወደ ዓለም ሲገባ። መሥዋዕትንና መባን አልወደድህም ሥጋን ግን አዘጋጀህልኝ፤
6Tau nepatiko deginamosios atnašos ir aukos už nuodėmes.
6በሙሉ በሚቃጠል መሥዋዕትና ሰለ ኃጢአት በሚሰዋ መሥዋዕት ደስ አላለህም።
7Tuomet tariau: ‘Štai ateinu, kaip knygos rietime apie mane parašyta, vykdyti Tavo, o Dieve, valios!’ ”
7በዚያን ጊዜ። እነሆ፥ በመጽሐፍ ጥቅልል ስለ እኔ እንደ ተጻፈ፥ አምላኬ ሆይ፥ ፈቃድህን ላደርግ መጥቼአለሁ አልሁ
8Anksčiau pasakęs: “Aukų ir atnašų, deginamųjų atnašų ir atnašų už nuodėmes Tu nenorėjai ir nemėgai”,­jos aukojamos pagal Įstatymą,­
8ይላል። በዚህ ላይ። መሥዋዕትንና መባን በሙሉ የሚቃጠል መሥዋዕትንም ስለ ኃጢአትም የሚሰዋ መሥዋዕትን አልወደድህም በእርሱም ደስ አላለህም ብሎ፥ እነዚህም እንደ ሕግ የሚቀርቡት ናቸው፥
9paskui paskelbė: “Štai ateinu vykdyti Tavo, o Dieve, valios”. Jis panaikina viena, kad įtvirtintų kita.
9ቀጥሎ። እነሆ፥ አምላኬ ሆይ፥ ፈቃድህን ላደርግ መጥቼአለሁ ብሎአል። ሁለተኛውንም ሊያቆም የፊተኛውን ይሽራል።
10Tos valios dėka esame Jėzaus Kristaus kūno auka vieną kartą pašventinti visiems laikams.
10በዚህም ፈቃድ የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ አንድ ጊዜ ፈጽሞ በማቅረብ ተቀድሰናል።
11Kiekvienas kunigas diena iš dienos tarnauja ir daug kartų aukoja tas pačias aukas, kurios niekada negali panaikinti nuodėmių.
11ሊቀ ካህናትም ሁሉ ዕለት ዕለት እያገለገለ ኃጢአትን ሊያስወግዱ ከቶ የማይችሉትን እነዚያን መሥዋዕቶች ብዙ ጊዜ እያቀረበ ቆሞአል፤
12O šis, paaukojęs vienintelę auką už nuodėmes, amžiams atsisėdo Dievo dešinėje,
12እርሱ ግን ስለ ኃጢአት አንድን መሥዋዕት ለዘላለም አቅርቦ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ፥
13nuo tol laukdamas, kol Jo priešai bus patiesti tarsi pakojis po Jo kojų.
13ጠላቶቹም የእግሩ መረገጫ እስኪደረጉ ድረስ ወደ ፊት ይጠብቃል።
14Vienintele atnaša Jis amžiams padarė tobulus šventinamuosius.
14አንድ ጊዜ በማቅረብ የሚቀደሱትን የዘላለም ፍጹማን አድርጎአቸዋልና።
15Tai mums liudija ir Šventoji Dvasia. Ji yra pasakiusi:
15መንፈስ ቅዱስም ደግሞ ስለዚህ ይመሰክርልናል፤ ከዚያ ወራት በኋላ ከእነርሱ ጋር የምገባው ኪዳን ይህ ነው ይላል ጌታ፤ በልባቸው ሕጌን አኖራለሁ በልቡናቸውም እጽፈዋለሁ
16“Štai Sandora, kurią su jais sudarysiu, praslinkus anoms dienoms,­sako Viešpats:­Aš įdėsiu savo įstatymus į jų širdis ir juos įrašysiu jų mintyse,
17ብሎ ከተናገረ በኋላ፥ ኃጢአታቸውንና ዓመጻቸውንም ደግሜ አላስብም ይላል።
17ir jų nuodėmių bei jų nedorybių daugiau nebeprisiminsiu”.
18የእነዚህም ስርየት ባለበት ዘንድ፥ ከዚህ ወዲህ ስለ ኃጢአት ማቅረብ የለም።
18O kur jos atleistos, ten nebereikia atnašos už nuodėmę.
19እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ በመረቀልን በአዲስና በሕያው መንገድ ወደ ቅድስት በኢየሱስ ደም በመጋረጃው ማለት በሥጋው በኩል እንድንገባ ድፍረት ስላለን፥
19Taigi, broliai, galėdami drąsiai įeiti į Švenčiausiąją dėl Jėzaus kraujo
21በእግዚአብሔርም ቤት ላይ የሆነ ታላቅ ካህን ስላለን፥
20nauju ir gyvu keliu, kurį Jis atvėrė mums per uždangą, tai yra savąjį kūną,
22ከክፉ ሕሊና ለመንጻት ልባችንን ተረጭተን ሰውነታችንንም በጥሩ ውኃ ታጥበን በተረዳንበት እምነት በቅን ልብ እንቅረብ፤
21ir turėdami didį Kunigą Dievo namams,
23የተስፋን ቃል የሰጠው የታመነ ነውና እንዳይነቃነቅ የተስፋችንን ምስክርነት እንጠብቅ፤
22artinkimės su tyra širdimi ir giliu, užtikrintu tikėjimu, apšlakstymu apvalę širdis nuo nešvarios sąžinės ir nuplovę kūną švariu vandeniu!
24ለፍቅርና ለመልካምም ሥራ እንድንነቃቃ እርስ በርሳችን እንተያይ፤
23Išlaikykime nepajudinamą vilties išpažinimą, nes ištikimas Tas, kuris pažadėjo.
25በአንዳንዶችም ዘንድ ልማድ እንደ ሆነው፥ መሰብሰባችንን አንተው እርስ በርሳችን እንመካከር እንጂ፤ ይልቁንም ቀኑ ሲቀርብ እያያችሁ አብልጣችሁ ይህን አድርጉ።
24Žiūrėkime vieni kitų, skatindami mylėti ir daryti gerus darbus.
26የእውነትን እውቀት ከተቀበልን በኋላ ወደን ኃጢአት ብናደርግ ከእንግዲህ ወዲህ ስለ ኃጢአት መሥዋዕት አይቀርልንምና፥
25Neapleiskime savųjų susirinkimo, kaip kai kurie yra pratę, bet raginkime vieni kitus juo labiau, juo aiškiau regime besiartinančią dieną.
27የሚያስፈራ ግን የፍርድ መጠበቅ ተቃዋሚዎችንም ሊበላ ያለው የእሳት ብርታት አለ።
26Jeigu, pasiekę tiesos pažinimą, sąmoningai nusidedame, tada nebelieka aukos už nuodėmes,
28የሙሴን ሕግ የናቀ ሰው ሁለት ወይም ሦስት ቢመሰክሩበት ያለ ርኅራኄ ይሞታል፤
27bet kažkoks baisus laukimas teismo ir liepsnojančio pykčio, kuris praris priešininkus.
29የእግዚአብሔርን ልጅ የረገጠ ያንንም የተቀደሰበትን የኪዳኑን ደም እንደ ርኵስ ነገር የቆጠረ የጸጋውንም መንፈስ ያክፋፋ፥ እንዴት ይልቅ የሚብስ ቅጣት የሚገባው ይመስላችኋል?
28Jei kas atstumia Mozės Įstatymą, tas be jokio pasigailėjimo turi mirti, dviem ar trims liudytojams paliudijus.
30በቀል የእኔ ነው፥ እኔ ብድራትን እመልሳለሁ ያለውን እናውቃለንና፤ ደግሞም። ጌታ በሕዝቡ ይፈርዳል።
29Tik pagalvokite: kaip dar sunkesnės bausmės nusipelnys tas, kuris sutrypė kojomis Dievo Sūnų, nešventu palaikė Sandoros kraują, kuriuo buvo pašventintas, ir įžeidė malonės Dvasią!
31በሕያው እግዚአብሔር እጅ መውደቅ የሚያስፈራ ነው።
30Juk pažįstame Tą, kuris pasakė: “Mano kerštas, Aš atsilyginsiu,­ sako Viešpats”. Ir vėl: “Viešpats teis savo tautą”.
32ነገር ግን ግማሽ በነቀፋና በጭንቅ እንደ መጫወቻ ስለ ሆናችሁ ግማሽም እንዲህ ካሉት ጋር ስለ ተካፈላችሁ፥ ብርሃን ከበራላችሁ በኋላ መከራ በሆነበት በትልቅ ተጋድሎ የጸናችሁበትን የቀደመውን ዘመን አስቡ።
31Baisu pakliūti į gyvojo Dievo rankas!
34የሚበልጥና ለዘወትር የሚኖር ገንዘብ በሰማይ ራሳችሁ እንዳላችሁ አውቃችሁ፥ በእስራቴ ራራችሁልኝ የገንዘባችሁንም ንጥቂያ በደስታ ተቀበላችሁ።
32Prisiminkite ankstesnes dienas, kada jūs apšviesti ištvėrėte didelę kentėjimų kovą,
35እንግዲህ ታላቅ ብድራት ያለውን ድፍረታችሁን አትጣሉ።
33tiek patys išstatyti viešam reginiui su paniekinimais ir smurtu, tiek būdami dalininkai tų, su kuriais buvo taip elgiamasi.
36የእግዚአብሔርን ፈቃድ አድርጋችሁ የተሰጣችሁን የተስፋ ቃል እንድታገኙ መጽናት ያስፈልጋችኋልና።
34Jūs užjautėte mane, kalinį, ir linksmai sutikote savo turto išplėšimą, žinodami, jog turite danguje geresnį ir išliekantį turtą.
37ገና በጣም ጥቂት ጊዜ ነው፥ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም፤
35Tad nepameskite savo pasitikėjimo, už kurį skirtas didelis atlygis!
38ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል ወደ ኋላም ቢያፈገፍግ፥ ነፍሴ በእርሱ ደስ አይላትም።
36Taip, reikia jums ištvermės, kad, įvykdę Dievo valią, gautumėte, kas pažadėta.
39እኛ ግን ነፍሳቸውን ሊያድኑ ከሚያምኑቱ ነን እንጂ ወደ ጥፋት ከሚያፈገፍጉ አይደለንም።
37Nes “dar trumpa, trumpa valandėlė, ir ateis Tas, kuris turi ateiti, ir neužtruks.
38Bet teisusis gyvens tikėjimu, ir, jeigu jis atsitrauktų, mano siela juo nebesigėrės”.
39Tačiau mes nesame tie, kurie atsitraukia savo pražūčiai, bet tie, kurie tiki, kad išgelbėtume sielą.