1Iš kur tarp jūsų atsiranda karai ir kivirčai? Ar ne iš jūsų užgaidų, kurios nerimsta jūsų nariuose?
1በእናንተ ዘንድ ጦርና ጠብ ከወዴት ይመጣሉ? በብልቶቻችሁ ውስጥ ከሚዋጉ ከእነዚህ ከምቾቶቻችሁ አይደሉምን?
2Geidžiate ir neturite; žudote ir pavyditeir negalite pasiekti; kovojate ir kariaujate; neturite, nes neprašote.
2ትመኛላችሁ ለእናንተም አይሆንም፤ ትገድላላችሁ በብርቱም ትፈልጋላችሁ፥ ልታገኙም አትችሉም፤ ትጣላላችሁ ትዋጉማላችሁ ነገር ግን አትለምኑምና ለእናንተ አይሆንም፤
3Jūs prašote ir negaunate, nes blogo prašotesavo užgaidoms išleisti.
3ትለምናላችሁ፥ በምቾቶቻችሁም ትከፍሉ ዘንድ በክፉ ትለምናላችሁና አትቀበሉም።
4Paleistuviai ir paleistuvės! Ar nežinote, kad draugystė su pasauliu yra priešiškumas Dievui? Taigi kas nori būti pasaulio bičiulis, tas tampa Dievo priešu.
4አመንዝሮች ሆይ፥ ዓለምን መውደድ ለእግዚአብሔር ጥል እንዲሆን አታውቁምን? እንግዲህ የዓለም ወዳጅ ሊሆን የሚፈቅድ ሁሉ የእግዚአብሔር ጠላት ሆኖአል።
5Gal manote, kad Raštas veltui sako: “Pavydžiai trokšta Dvasia, kuri gyvena mumyse”.
5ወይስ መጽሐፍ። በእኛ ዘንድ ያሳደረው መንፈስ በቅንዓት ይመኛል ያለው በከንቱ እንደ ተናገረ ይመስላችኋልን?
6Bet Jis duoda dar didesnę malonę, ir todėl sako: “Dievas išdidiems priešinasi, o nuolankiesiems teikia malonę”.
6ነገር ግን ጸጋን አብልጦ ይሰጣል፤ ስለዚህ። እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል ይላል።
7Todėl atsiduokite Dievui; priešinkitės velniui, ir jis bėgs nuo jūsų.
7እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል፤
8Artinkitės prie Dievo, ir Jis artinsis prie jūsų. Nusiplaukite rankas, nusidėjėliai, nusivalykite širdis, dvejojantys.
8ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ ወደ እናንተም ይቀርባል። እናንተ ኃጢአተኞች፥ እጆቻችሁን አንጹ፤ ሁለት አሳብም ያላችሁ እናንተ፥ ልባችሁን አጥሩ።
9Dejuokite, liūdėkite ir raudokite! Jūsų juokas tepavirsta gedulu, o džiaugsmasliūdesiu.
9ተጨነቁና እዘኑ አልቅሱም፤ ሳቃችሁ ወደ ኀዘን ደስታችሁም ወደ ትካዜ ይለወጥ።
10Nusižeminkite prieš Viešpatį, ir Jis jus išaukštins.
10በጌታ ፊት ራሳችሁን አዋርዱ ከፍ ከፍም ያደርጋችኋል።
11Broliai, neapkalbinėkite vieni kitų! Kas apkalba ir teisia savo brolį, tas apkalba ir teisia įstatymą. O jeigu teisi įstatymą, vadinasi, nesi įstatymo vykdytojas, bet teisėjas.
11ወንድሞች ሆይ፥ እርስ በርሳችሁ አትተማሙ። ወንድሙን የሚያማ በወንድሙም የሚፈርድ ሕግን ያማል በሕግም ይፈርዳል፤ በሕግም ብትፈርድ ፈራጅ ነህ እንጂ ሕግን አድራጊ አይደለህም።
12Yra vienas įstatymo leidėjas, kuris gali išgelbėti ir pražudyti. O kas gi tu toks, kuris teisi kitą?
12ሕግን የሚሰጥና የሚፈርድ አንድ ነው፤ እርሱም ሊያድን ሊያጠፋም የሚችል ነው፤ በሌላው ግን የምትፈርድ አንተ ማን ነህ?
13Nagi jūs, kurie sakote: “Šiandien arba rytoj keliausime į tą ir tą miestą, tenai išbūsime metus, versimės prekyba ir pasipelnysime”,
13አሁንም። ዛሬ ወይም ነገ ወደዚህ ከተማ እንሄዳለን በዚያም ዓመት እንኖራለን እንነግድማለን እናተርፍማለን የምትሉ እናንተ፥ ተመልከቱ፥ ነገ የሚሆነውን አታውቁምና።
14jūs nežinote, kas atsitiks rytoj! Ir kas gi jūsų gyvybė? Garas, kuris trumpam pasirodo ir paskui išnyksta.
14ሕይወታችሁ ምንድር ነው? ጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፍዋለት ናችሁና።
15Verčiau sakytumėte: “Jei Viešpats panorės, gyvensime ir darysime šį bei tą”.
15በዚህ ፈንታ። ጌታ ቢፈቅድ ብንኖርም ይህን ወይም ያን እናደርጋለን ማለት ይገባችኋል።
16O dabar jūs giriatės iš savo pasipūtimo, ir kiekvienas toks gyrimasis yra blogas.
16አሁን ግን በትዕቢታችሁ ትመካላችሁ፤ እንደዚህ ያለ ትምክህት ሁሉ ክፉ ነው።
17Kas moka daryti gera ir nedaro, tas nusideda.
17እንግዲህ በጎ ለማድረግ አውቆ ለማይሠራው ኃጢአት ነው።