1Nagi dabar jūs, turtuoliai, verkite ir raudokite dėl jums artėjančių negandų!
1አሁንም እናንተ ባለ ጠጎች፥ ስለሚደርስባችሁ ጭንቅ ዋይ ዋይ እያላችሁ አልቅሱ።
2Jūsų turtai supuvę ir jūsų drabužiai kandžių sukapoti.
2ሀብታችሁ ተበላሽቶአል፥ ልብሳችሁም በብል ተበልቶአል።
3Jūsų auksas ir sidabras surūdijo, ir jų rūdys prieš jus liudys ir ės jūsų kūnus kaip ugnis. Jūs susikrovėte turtų paskutinėmis dienomis.
3ወርቃችሁም ብራችሁም ዝጎአል፥ ዝገቱም ምስክር ይሆንባችኋል ሥጋችሁንም እንደ እሳት ይበላል። ለኋለኛው ቀን መዝገብን አከማችታችኋል።
4Štai šaukia jūsų laukus nuvaliusių darbininkų užmokestis, kurį jūs nusukote, ir pjovėjų šauksmai pasiekė kareivijų Viešpaties ausis.
4እነሆ፥ እርሻችሁን ያጨዱት የሠራተኞች ደመወዝ በእናንተ ተቀምቶ ይጮኻል፥ የአጫጆችም ድምፅ ወደ ጌታ ፀባዖት ጆሮ ገብቶአል።
5Jūs gašliai gyvenote žemėje ir mėgavotės; jūs nupenėjote savo širdis tarsi skerdimo dienai.
5በምድር ላይ ተቀማጥላችኋል በሴሰኝነትም ኖራችኋል፤ ለእርድ ቀን እንደሚያወፍር ልባችሁን አወፍራችኋል።
6Jūs pasmerkėte ir nužudėte teisųjį: jis jums nesipriešina.
6ጻድቁን ኰንናችሁታል ገድላችሁትማል፤ እናንተን አይቃወምም።
7Tad būkite kantrūs, broliai, iki Viešpaties atėjimo. Antai žemdirbys ilgai ir kantriai laukia brangaus žemės vaisiaus, kol šis gauna ankstyvojo ir vėlyvojo lietaus.
7እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ጌታ እስኪመጣ ድረስ ታገሡ። እነሆ፥ ገበሬው የፊተኛውንና የኋለኛውን ዝናብ እስኪቀበል ድረስ እርሱን እየታገሠ የከበረውን የመሬት ፍሬ ይጠብቃል።
8Ir jūs būkite kantrūs, sustiprinkite savo širdis, nes Viešpaties atėjimas arti.
8እናንተ ደግሞ ታገሡ፥ ልባችሁንም አጽኑ፤ የጌታ መምጣት ቀርቦአልና።
9Nemurmėkite, broliai, vieni prieš kitus, kad nebūtumėte teisiami. Štai teisėjas jau stovi prie durų.
9ወንድሞች ሆይ፥ እንዳይፈረድባችሁ እርስ በርሳችሁ አታጉረምርሙ፤ እነሆ፥ ፈራጅ በደጅ ፊት ቆሞአል።
10Imkite, broliai, kentėjimo ir ištvermės pavyzdžiu pranašus, kurie kalbėjo Viešpaties vardu.
10ወንድሞች ሆይ፥ የመከራና የትዕግሥት ምሳሌ የሆኑትን በጌታ ስም የተናገሩትን ነቢያትን ተመልከቱ።
11Štai mes laikome palaimintais ištvėrusius. Jūs girdėjote apie Jobo ištvermę ir matėte, kokia buvo jam Viešpaties skirta pabaiga, nes Viešpats kupinas užuojautos ir gailestingumo.
11እነሆ፥ በትዕግሥት የጸኑትን ብፁዓን እንላቸዋለን፤ ኢዮብ እንደ ታገሠ ሰምታችኋል፥ ጌታም እንደ ፈጸመለት አይታችኋል፤ ጌታ እጅግ የሚምር የሚራራም ነውና።
12Bet pirmiausia, mano broliai, neprisiekite nei dangumi, nei žeme, nei kitokia priesaika. Tebūnie jūsų “taip” taip ir jūsų “ne” ne, kad nepakliūtumėte į teismą.
12ከሁሉም በፊት፥ ወንድሞቼ ሆይ፥ በሰማይ ቢሆን በምድርም ቢሆን በሌላ መሐላም ቢሆን በምንም አትማሉ፤ ነገር ግን ከፍርድ በታች እንዳትወድቁ ነገራችሁ አዎን ቢሆን አዎን ይሁን፥ አይደለምም ቢሆን አይደለም ይሁን።
13Kenčia kas iš jūsų? Tesimeldžia. Kas nors džiaugiasi? Tegul gieda psalmes.
13ከእናንተ መከራን የሚቀበል ማንም ቢኖር እርሱ ይጸልይ፤ ደስ የሚለውም ማንም ቢኖር እርሱ ይዘምር።
14Kas nors pas jus serga? Tepasikviečia bažnyčios vyresniuosius, ir jie tesimeldžia už jį, patepdami aliejumi Viešpaties vardu.
14ከእናንተ የታመመ ማንም ቢኖር የቤተ ክርስቲያንን ሽምግሌዎች ወደ እርሱ ይጥራ፤ በጌታም ስም እርሱን ዘይት ቀብተው ይጸልዩለት።
15Ir tikėjimo malda išgelbės ligonį, ir Viešpats jį pakels, o jeigu jis būtų nusidėjęs, jam bus atleista.
15የእምነትም ጸሎት ድውዩን ያድናል ጌታም ያስነሣዋል፤ ኃጢአትንም ሠርቶ እንደ ሆነ ይሰረይለታል።
16Išpažinkite vieni kitiems savo nusižengimus ir melskitės vieni už kitus, kad būtumėte išgydyti. Daug pajėgia veiksminga, karšta teisiojo malda.
16እርስ በርሳችሁ በኃጢአታችሁ ተናዘዙ። ትፈወሱም ዘንድ እያንዳንዱ ስለ ሌላው ይጸልይ፤ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።
17Elijas buvo toks pat žmogus kaip ir mes. Jis meldė, kad nelytų, ir nelijo žemėje trejus metus ir šešis mėnesius;
17ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥
18ir jis vėl meldė, ir dangus davė lietaus, o žemė užaugino savo vaisių.
18ሰማዩም ዝናብን ሰጠ ምድሪቱም ፍሬዋን አበቀለች።
19Mano broliai, jeigu kas iš jūsų nuklystų nuo tiesos ir kas nors jį atverstų,
19ወንድሞቼ ሆይ፥ ከእናንተ ማንም ከእውነት ቢስት አንዱም ቢመልሰው፥
20težino, kad, sugrąžindamas nusidėjėlį iš jo klystkelio, išgelbės sielą nuo mirties ir uždengs daugybę nuodėmių.
20ኃጢአተኛን ከተሳሳተበት መንገድ የሚመልሰው ነፍሱን ከሞት እንዲያድን፥ የኃጢአትንም ብዛት እንዲሸፍን ይወቅ።