1“Tenebūgštauja jūsų širdys! Tikite Dievątikėkite ir mane!
1ልባችሁ አይታወክ፤ በእግዚአብሔር እመኑ፥ በእኔም ደግሞ እመኑ።
2Mano Tėvo namuose daug buveinių. Jeigu taip nebūtų, būčiau jums pasakęs. Einu jums vietos paruošti.
2በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ እንዲህስ ባይሆን ባልኋችሁ ነበር፤ ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁና፤
3Kai nuėjęs paruošiu, vėl sugrįšiu ir jus pas save pasiimsiu, kad jūs būtumėte ten, kur ir Aš.
3ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ፥ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ።
4Kur Aš einu, jūs žinote, ir kelią jūs žinote”.
4ወደምሄድበትም ታውቃላችሁ፥ መንገዱንም ታውቃላችሁ።
5Tomas Jam sako: “Viešpatie, mes nežinome, kur Tu eini, tai kaip žinosime kelią?”
5ቶማስም። ጌታ ሆይ፥ ወደምትሄድበት አናውቅም፤ እንዴትስ መንገዱን እናውቃለን? አለው።
6Jėzus jam sako: “Aš esu kelias, tiesa ir gyvenimas. Niekas nenueina pas Tėvą kitaip, kaip tik per mane.
6ኢየሱስም። እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።
7Jeigu pažinote mane, tai pažinsite ir mano Tėvą. Jau nuo šiol Jį pažįstate ir esate Jį matę”.
7እኔንስ ብታውቁኝ አባቴን ደግሞ ባወቃችሁ ነበር። ከአሁንም ጀምራችሁ ታውቁታላችሁ አይታችሁትማል አለው።
8Pilypas Jam sako: “Viešpatie, parodyk mums Tėvą, ir bus mums gana”.
8ፊልጶስ። ጌታ ሆይ፥ አብን አሳየንና ይበቃናል አለው።
9Jėzus jam taria: “Jau tiek laiko esu su jumis, ir tu, Pilypai, vis dar manęs nepažįsti? Kas matė mane, matė Tėvą! Tad kaip gali sakyti: ‘Parodyk mums Tėvą’?
9ኢየሱስም አለው። አንተ ፊልጶስ፥ ይህን ያህል ዘመን ከእናንተ ጋር ስኖር አታውቀኝምን? እኔን ያየ አብን አይቶአል፤ እንዴትስ አንተ። አብን አሳየን ትላለህ?
10Nejaugi tu netiki, kad Aš esu Tėve ir Tėvas manyje? Žodžius, kuriuos jums kalbu, ne iš savęs kalbu; Tėvas, esantis manyjeJis daro darbus.
10እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ አታምንምን? እኔ የምነግራችሁን ቃል ከራሴ አልናገረውም፤ ነገር ግን በእኔ የሚኖረው አብ እርሱ ሥራውን ይሠራል።
11Tikėkite manimi, kad Aš esu Tėve ir Tėvas manyje, arba tikėkite mane dėl pačių darbų!
11እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ እመኑኝ፤ ባይሆንስ ስለ ራሱ ስለ ሥራው እመኑኝ።
12Iš tiesų, iš tiesų sakau jums: kas mane tiki, darys darbus, kuriuos Aš darau, ir dar už juos didesnių darys, nes Aš einu pas savo Tėvą.
12እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ሥራ እርሱ ደግሞ ያደርጋል፤ ከዚህም የሚበልጥ ያደርጋል፥
13Ir ko tik prašysite mano vardu, Aš padarysiu, kad Tėvas būtų pašlovintas Sūnuje.
13እኔ ወደ አብ እሄዳለሁና፤ አብም ስለ ወልድ እንዲከበር በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ አደርገዋለሁ።
14Ko tik prašysite mano vardu, Aš padarysiu.
14ማናቸውንም ነገር በስሜ ብትለምኑ እኔ አደርገዋለሁ።
15Jei mylite mane, laikykitės mano įsakymų.
15ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ። እኔም አብን እለምናለሁ ለዘላለምም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤
16Ir Aš paprašysiu Tėvą, ir Jis duos jums kitą Guodėją, kad Jis liktų su jumis per amžius.
17እርሱም ዓለም የማያየውና የማያውቀው ስለ ሆነ ሊቀበለው የማይቻለው የእውነት መንፈስ ነው፤ ነገር ግን ከእናንተ ዘንድ ስለሚኖር በውሥጣችሁም ስለሚሆን እናንተ ታውቃላችሁ።
17Tiesos Dvasią, kurios pasaulis neįstengia priimti, nes Jos nemato ir nepažįsta. O jūs Ją pažįstate, nes Ji yra su jumis ir bus jumyse.
18ወላጆች እንደ ሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም፤ ወደ እናንተ እመጣለሁ።
18Nepaliksiu jūsų našlaičiais ateisiu pas jus.
19ገና ጥቂት ዘመን አለ ከዚህም በኋላ ዓለም አያየኝም፤ እናንተ ግን ታዩኛላችሁ፤ እኔ ሕያው ነኝና እናንተ ደግሞ ሕያዋን ትሆናላችሁ።
19Dar valandėlė, ir pasaulis manęs nebematys. O jūs mane matysite, nes Aš gyvenu ir jūs gyvensite.
20እኔ በአባቴ እንዳለሁ እናንተም በእኔ እንዳላችሁ እኔም በእናንተ እንዳለሁ በዚያን ቀን ታውቃላችሁ።
20Tą dieną jūs suprasite, kad Aš esu savo Tėve, ir jūs manyje, ir Aš jumyse.
21ትእዛዜ በእርሱ ዘንድ ያለችው የሚጠብቃትም የሚወደኝ እርሱ ነው፤ የሚወደኝንም አባቴ ይወደዋል እኔም እወደዋለሁ ራሴንም እገልጥለታለሁ።
21Kas žino mano įsakymus ir jų laikosi, tas myli mane. O kas mane myli, tą mylės mano Tėvas, ir Aš jį mylėsiu ir pats jam apsireikšiu”.
22የአስቆሮቱ ያይደለ ይሁዳ። ጌታ ሆይ፥ ለዓለም ሳይሆን ራስህን ለእኛ ልትገልጥ ያለህ እንዴት ነው? አለው።
22Judasne Iskarijotaspaklausė: “Viešpatie, kas atsitiko, jog ketini apsireikšti mums, o ne pasauliui?”
23ኢየሱስም መለሰ አለውም። የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤ አባቴም ይወደዋል ወደ እርሱም እንመጣለን በእርሱም ዘንድ መኖሪያ እናደርጋለን።
23Jėzus jam atsakė: “Jei kas mane myli, laikysis mano žodžio ir mano Tėvas jį mylės; mes pas jį ateisime ir apsigyvensime.
24የማይወደኝ ቃሌን አይጠብቅም፤ የምትሰሙትም ቃል የላከኝ የአብ ነው እንጂ የእኔ አይደለም።
24Kas manęs nemyli, mano žodžių nesilaiko. O žodis, kurį girdite, ne mano, bet Tėvo, kuris mane siuntė.
25ከእናንተ ዘንድ ስኖር ይህን ነግሬአችኋለሁ፤
25Aš jums tai pasakiau, būdamas su jumis,
26አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል።
26o GuodėjasŠventoji Dvasia, kurią mano vardu Tėvas atsiųs, mokys jus visko ir viską primins, ką jums sakiau.
27ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም። ልባችሁ አይታወክ አይፍራም።
27Aš palieku jums ramybę, duodu jums savo ramybę. Ne kaip pasaulis duoda, Aš jums duodu. Tenebūgštauja jūsų širdys ir teneišsigąsta.
28እኔ እሄዳለሁ ወደ እናንተም እመጣለሁ እንዳልኋችሁ ሰማችሁ። የምትወዱኝስ ብትሆኑ ከእኔ አብ ይበልጣልና ወደ አብ በመሄዴ ደስ ባላችሁ ነበር።
28Jūs girdėjote, kaip Aš pasakiau: ‘Aš išeinu ir vėl sugrįšiu pas jus!’ Jei mylėtumėte mane, džiaugtumėtės, kad pasakiau: ‘Einu pas Tėvą’, nes mano Tėvas už mane didesnis.
29ከሆነም በኋላ ታምኑ ዘንድ አሁን አስቀድሞ ሳይሆን። ነግሬአችኋለሁ።
29Ir dabar, prieš įvykstant, jums tai pasakiau, kad tikėtumėte, kada tai įvyks.
30ከእንግዲህ ወዲህ ከእናንተ ጋር ብዙ አልናገርም፥ የዚህ ዓለም ገዥ ይመጣልና፤ በእኔ ላይም አንዳች የለውም፤
30Jau nebedaug su jumis kalbėsiu, nes ateina šio pasaulio kunigaikštis, ir manyje jis neturi nieko.
31ነገር ግን አብን እንድወድ ዓለም ሊያውቅ፥ አብም እንዳዘዘኝ፥ እንዲሁ አደርጋለሁ። ተነሡ፤ ከዚህ እንሂድ።
31Bet pasaulis turi pažinti, jog Aš myliu Tėvą ir darau taip, kaip Jis man įsakė.Kelkitės, eikime iš čia!”