1Prieš Paschos šventę Jėzus, žinodamas, kad atėjo Jo valanda iš šio pasaulio keliauti pas Tėvą, ir mylėdamas savuosius pasaulyje, parodė jiems savo meilę iki galo.
1ኢየሱስም ከፋሲካ በዓል በፊት፥ ከዚህ ዓለም ወደ አብ የሚሄድበት ሰዓት እንደ ደረሰ አውቆ፥ በዚህ ዓለም ያሉትን ወገኖቹን የወደዳቸውን እስከ መጨረሻ ወደዳቸው።
2Vakarienės metu, kai velnias jau buvo įkvėpęs Simono sūnaus Judo Iskarijoto širdin sumanymą išduoti Jį,
2እራትም ሲበሉ ዲያብሎስ በስምዖን ልጅ በአስቆሮቱ በይሁዳ ልብ አሳልፎ እንዲሰጠው አሳብ ካገባ በኋላ፥
3žinodamas, kad Tėvas visa atidavęs į Jo rankas ir kad Jis išėjo iš Dievo ir eina pas Dievą,
3ኢየሱስ አብ ሁሉን በልጁ እንደ ሰጠው ከእግዚአብሔርም እንደ ወጣ ወደ እግዚአብሔርም እንዲሄድ አውቆ፥
4Jėzus pakilo nuo stalo, nusivilko viršutinius drabužius ir persijuosė rankšluosčiu.
4ከእራት ተነሣ ልብሱንም አኖረ፥ ማበሻም ጨርቅ ወስዶ ታጠቀ፤
5Po to įpylė vandens į praustuvą ir ėmė plauti mokiniams kojas bei šluostyti rankšluosčiu, kuriuo buvo persijuosęs.
5በኋላም በመታጠቢያው ውኃ ጨመረ፥ የደቀ መዛሙርቱንም እግር ሊያጥብና በታጠቀበትም ማበሻ ጨርቅ ሊያብስ ጀመረ።
6Taip Jis priėjo prie Simono Petro. Šis Jam tarė: “Viešpatie, nejaugi Tu plausi man kojas?”
6ወደ ስምዖን ጴጥሮስም መጣ፤ እርሱም። ጌታ ሆይ፥ አንተ የእኔን እግር ታጥባለህን? አለው።
7Jėzus jam atsakė: “Tu dabar nesupranti, ką Aš darau, bet vėliau suprasi”.
7ኢየሱስም መልሶ። እኔ የማደርገውን አንተ አሁን አታውቅም፥ በኋላ ግን ታስተውለዋለህ አለው።
8Petras atsiliepė: “Tu neplausi man kojų per amžius!” Jėzus jam atsakė: “Jei nenuplausiu tavęs, neturėsi dalies su manimi”.
8ጴጥሮስም። የእኔን እግር ለዘላለም አታጥብም አለው። ኢየሱስም። ካላጠብሁህ፥ ከእኔ ጋር ዕድል የለህም ብሎ መለሰለት።
9Tada Simonas Petras sušuko: “Viešpatie, ne tik mano kojas, bet ir rankas, ir galvą!”
9ስምዖን ጴጥሮስም። ጌታ ሆይ፥ እጄንና ራሴን ደግሞ እንጂ እግሬን ብቻ አይደለም አለው።
10Jėzus jam atsakė: “Kas nuplautas, tam reikia tik kojas nusiplauti, nes jis visas švarus. Ir jūs esate švarūs, bet ne visi”.
10ኢየሱስም። የታጠበ እግሩን ከመታጠብ በቀር ሌላ አያስፈልገውም፥ ሁለንተናው ግን ንጹሕ ነው፤ እናንተም ንጹሐን ናችሁ፥ ነገር ግን ሁላችሁ አይደላችሁም አለው።
11Nes Jis žinojo, kas Jį išduos, ir todėl sakė: “Jūs ne visi švarūs”.
11አሳልፎ የሚሰጠውን ያውቅ ነበርና፤ ስለዚህ። ሁላችሁ ንጹሐን አይደላችሁም አለው።
12Nuplovęs jų kojas, Jis užsivilko drabužius ir atsisėdęs paklausė: “Ar supratote, ką jums padariau?
12እግራቸውንም አጥቦ ልብሱንም አንሥቶ ዳግመኛ ተቀመጠ፥ እንዲህም አላቸው። ያደረግሁላችሁን ታስተውላላችሁን?
13Jūs vadinate mane ‘Mokytoju’ ir ‘Viešpačiu’, ir gerai sakote, nes Aš Tas esu.
13እናንተ መምህርና ጌታ ትሉኛላችሁ፤ እንዲሁ ነኝና መልካም ትላላችሁ።
14Jei tad AšViešpats ir Mokytojasnuploviau jums kojas, tai ir jūs turite vieni kitiems kojas plauti.
14እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ፥ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል።
15Aš jums daviau pavyzdį, kad Jūs darytumėte, kaip Aš jums dariau.
15እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና።
16Iš tiesų, iš tiesų sakau jums: tarnas ne didesnis už savo šeimininką ir pasiuntinys ne didesnis už savo siuntėją.
16እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ባሪያ ከጌታው አይበልጥም። መልእክተኛም ከላከው አይበልጥም።
17Jeigu tai suprantate, palaiminti esate, taip elgdamiesi.
17ይህን ብታውቁ፥ ብታደርጉትም ብፁዓን ናችሁ።
18Ne apie jus visus tai sakau. Aš žinau, ką išsirinkau, bet turi išsipildyti Raštas: ‘Tas, kuris valgo su manimi duoną, pakėlė virš manęs savo kulną’.
18ስለ ሁላችሁ አልናገርም፤ እኔ የመረጥኋቸውን አውቃለሁ፤ ነገር ግን መጽሐፍ። እንጀራዬን የሚበላ በእኔ ላይ ተረከዙን አነሣብኝ ያለው ይፈጸም ዘንድ ነው።
19Sakau jums dabar, prieš įvykstant, kad įvykus tikėtumėte, jog Aš Esu.
19በሆነ ጊዜ እኔ እንደ ሆንሁ ታምኑ ዘንድ፥ ከአሁን ጀምሬ አስቀድሞ ሳይሆን እነግራችኋለሁ።
20Iš tiesų, iš tiesų sakau jums: kas priima mano pasiuntinį, tas priima mane, o kas mane priima, priima Tą, kuris mane siuntė”.
20እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ማናቸውን የምልከውን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል።
21Tai pasakęs, Jėzus, sukrėstas dvasioje, tarė: “Iš tiesų, iš tiesų sakau jums: vienas iš jūsų išduos mane!”
21ኢየሱስ ይህን ብሎ በመንፈሱ ታወከ መስክሮም። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ከእናንተ አንዱ አሳልፎ ይሰጠኛል አለ።
22Tada mokiniai ėmė žvalgytis vienas į kitą, nesusivokdami, apie kurį Jis taip pasakė.
22ደቀ መዛሙርቱ ስለ ማን እንደ ተናገረ አመንትተው እርስ በርሳቸው ተያዩ።
23Vienas iš Jo mokinių, kurį Jėzus mylėjo, buvo prisiglaudęs prie Jėzaus krūtinės.
23ኢየሱስም ይወደው የነበረ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ በኢየሱስ ደረት ላይ ተጠጋ፤
24Simonas Petras pamojo jam, kad šis paklaustų, apie kurį Jis kalba.
24ስለዚህ ስምዖን ጴጥሮስ እርሱን ጠቅሶ። ስለማን እንደ ተናገረ ንገረን አለው።
25Tasai, pasilenkęs prie Jėzaus krūtinės, paklausė: “Kas jis, Viešpatie?”
25እርሱም በኢየሱስ ደረት እንዲህ ተጠግቶ። ጌታ ሆይ፥ ማን ነው? አለው።
26Jėzus atsiliepė: “Tai tas, kuriam padažęs paduosiu kąsnį duonos”. Ir, pamirkęs duoną, Jis padavė Judui Iskarijotui, Simono sūnui.
26ኢየሱስም። እኔ ቍራሽ አጥቅሼ የምሰጠው እርሱ ነው ብሎ መለሰለት። ቍራሽም አጥቅሶ ለአስቆሮቱ ለስምዖን ልጅ ለይሁዳ ሰጠው።
27Ir po šio kąsnio įėjo į jį šėtonas. Tada Jėzus jam pasakė: “Ką darai, daryk greičiau!”
27ቍራሽም ከተቀበለ በኋላ ያን ጊዜ ሰይጣን ገባበት። እንግዲህ ኢየሱስ። የምታደርገውን ቶሎ ብለህ አድርግ አለው።
28Bet nė vienas iš esančių prie stalo nesuprato, kodėl Jis jam taip pasakė.
28ነገር ግን ከተቀመጡት ስለ ምን ይህን እንዳለው ማንም አላወቀም፤
29Kadangi Judo žinioje buvo kasa, kai kurie manė, jog Jėzus jam liepė: “Nupirk, ko mums reikia šventei”, arba kad jis duotų ką nors vargšams.
29ይሁዳ ከረጢቱን የያዘ ስለ ሆነ፥ ኢየሱስ። ለበዓሉ የሚያስፈልገንን ግዛ፥ ወይም ለድሆች ምጽዋት እንዲሰጥ ያለው ለአንዳንዱ መስሎአቸው ነበርና።
30Taigi, paėmęs duonos kąsnį, anas tuojau išėjo. Buvo naktis.
30እርሱም ቍራሹን ከተቀበለ በኋላ ወዲያው ወጣ፤ ሌሊትም ነበረ።
31Jam išėjus, Jėzus prabilo: “Dabar Žmogaus Sūnus pašlovintas, ir Dievas pašlovintas Jame.
31ከወጣም በኋላ ኢየሱስ እንዲ አለ። አሁን የሰው ልጅ ከበረ እግዚአብሔርም ሰለ እርሱ ከበረ፤
32O jeigu Dievas pašlovintas Jame, tai Dievas pašlovins Jį savyje,bematant Jį pašlovins”.
32እግዚአብሔር ስለ እርሱ የከበረ ከሆነ፥ እግዚአብሔር ደግሞ እርሱን ራሱን ያከብረዋል ወዲያውም ያከብረዋል።
33“Vaikeliai, Aš jau nebeilgai būsiu su jumis. Jūs ieškosite manęs, bet sakau jums tą patį, ką žydams pasakiau: kur Aš einu, jūs negalite nueiti.
33ልጆች ሆይ፥ ገና ጥቂት ጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ፤ ትፈልጉኛላችሁ፤ ለአይሁድም። እኔ ወደምሄድበት እናንተ ልትመጡ አይቻላችሁም እንዳልኋቸው፥ አሁን ለእናንተ ደግሞ እላችኋለሁ።
34Aš jums duodu naują įsakymą, kad jūs vienas kitą mylėtumėte: kaip Aš jus pamilau, kad ir jūs mylėtumėte vienas kitą.
34እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ፥ እንደ ወደድኋችሁ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ አዲስ ትእዛዝ እሰጣችኋለሁ።
35Iš to visi pažins, kad esate mano mokiniai, jei mylėsite vieni kitus”.
35እርስ በርሳችሁ ፍቅር ቢኖራችሁ፥ ደቀ መዛሙርቴ እንደ ሆናችሁ ሰዎች ሁሉ በዚህ ያውቃሉ።
36Simonas Petras Jį paklausė: “Viešpatie, kur Tu eini?” Jėzus atsakė: “Kur Aš einu, tu dabar negali paskui mane sekti, bet vėliau nuseksi mane”.
36ስምዖን ጴጥሮስም። ጌታ ሆይ፥ ወዴት ትሄዳለህ? አለው። ኢየሱስም። ወደምሄድበት አሁን ልትከተለኝ አትችልም፥ ነገር ግን በኋላ ትከተለኛለህ ብሎ መለሰለት።
37Petras vėl klausė: “Viešpatie, kodėl gi negaliu dabar paskui Tave sekti? Aš savo gyvybę už Tave guldysiu!”
37ጴጥሮስም። ጌታ ሆይ፥ አሁን ልከተልህ አለመቻሌ ስለ ምንድር ነው? ነፍሴን ስንኳ ስለ አንተ እሰጣለሁ አለው።
38Jėzus atsakė: “Tu guldysi už mane gyvybę? Iš tiesų, iš tiesų sakau tau: dar gaidžiui nepragydus, tu tris kartus manęs išsiginsi!”
38ኢየሱስም እንዲህ ብሎ መለሰለት። ነፍስህን ስለ እኔ ትሰጣለህን? እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሦስት ጊዜ እስክትክደኝ ድረስ ዶሮ አይጮኽም።