1Šešioms dienoms belikus iki Paschos, Jėzus atėjo į Betaniją, kur gyveno jo prikeltasis iš numirusių Lozorius.
1ከፋሲካም በፊት በስድስተኛው ቀን ኢየሱስ ከሙታን ያስነሣው አልዓዛር ወደ ነበረበት ወደ ቢታንያ መጣ።
2Ten iškėlė Jam vaišes. Morta patarnavo, o Lozorius kartu su kitais sėdėjo prie stalo su Jėzumi.
2በዚያም እራት አደረጉለት፤ ማርታም ታገለግል ነበር፤ አልዓዛር ግን ከእርሱ ጋር ከተቀመጡት አንዱ ነበረ።
3Paėmusi svarą labai brangaus tepalo iš gryno nardo, Marija patepė Jėzui kojas ir nušluostė jas savo plaukais. Namuose pasklido tepalo kvapas.
3ማርያምም ዋጋው እጅግ የከበረ የጥሩ ናርዶስ ሽቱ ንጥር ወስዳ የኢየሱስን እግር ቀባች፤ በጠጕርዋም እግሩን አበሰች፤ ቤቱም ከናርዶስ ሽቱ ሞላ።
4Vienas iš Jo mokinių, Simono sūnus Judas Iskarijotas, kuris turėjo Jį išduoti, pasakė:
4ነገር ግን ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ አሳልፎ ሊሰጠው ያለው የስምዖን ልጅ የአስቆሮቱ ይሁዳ።
5“Kodėl to tepalo neparduoda už tris šimtus denarų ir neatiduoda vargšams?”
5ይህ ሽቱ ለሦስት መቶ ዲናር ተሽጦ ለድሆች ያልተሰጠ ስለ ምን ነው? አለ።
6Jis taip sakė ne todėl, kad jam būtų rūpėję vargšai, bet kad pats buvo vagis ir, turėdamas kasą, grobstė įplaukas.
6ይህንም የተናገረ ሌባ ስለ ነበረ ነው እንጂ ለድሆች ተገድዶላቸው አይደለም፤ ከረጢትም ይዞ በውስጡ ከሚገባው ይወስድ ስለ ነበረ ነው።
7O Jėzus tarė: “Palik ją ramybėje. Ji tai laikė mano laidotuvių dienai.
7ኢየሱስም። ለምቀበርበት ቀን እንድትጠብቀው ተውአት፤
8Vargšų jūs visada turėsite su savimi, o mane ne visuomet turėsite”.
8ድሆችስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ይኖራሉና፥ እኔ ግን ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር አልኖርም አለ።
9Daug žydų sužinojo Jėzų ten esant ir atėjo ne tik dėl Jėzaus, bet taip pat pamatyti Lozoriaus, kurį Jis prikėlė iš numirusių.
9ከአይሁድም ብዙ ሕዝብ በዚያ እንደ ነበረ አውቀው መጡ፥ ከሙታንም ያስነሣውን አልዓዛርን ደግሞ እንዲያዩ ነበረ እንጂ ስለ ኢየሱስ ብቻ አይደለም።
10O aukštieji kunigai nusprendė nužudyti ir Lozorių,
10የካህናት አለቆችም አልዓዛርን ደግሞ ሊገድሉት ተማከሩ፥
11nes daugybė žydų per jį pasitraukė nuo jų ir įtikėjo Jėzų.
11ከአይሁድ ብዙዎች ከእርሱ የተነሣ ሄደው በኢየሱስ ያምኑ ነበርና።
12Kitą dieną gausi minia, susirinkusi į šventę, sužinojo, kad Jėzus ateinąs į Jeruzalę.
12በማግሥቱ ወደ በዓሉ መጥተው የነበሩ ብዙ ሕዝብ ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም እንዲመጣ በሰሙ ጊዜ፥
13Žmonės pasiėmė palmių šakų ir išėjo Jo pasitikti, šaukdami: “Osana! Palaimintas Tas, kuris ateina Viešpaties varduIzraelio karalius!”
13የዘንባባ ዛፍ ዝንጣፊ ይዘው ሊቀበሉት ወጡና። ሆሣዕና፤ በጌታ ስም የሚመጣ የእስራኤል ንጉሥ የተባረከ ነው እያሉ ጮኹ።
14Jėzus, radęs asiliuką, užsėdo ant jo, kaip parašyta:
14አንቺ የጽዮን ልጅ አትፍሪ፤ እነሆ፥ ንጉሥሽ በአህያ ውርንጫ ላይ ተቀምጦ ይመጣል ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ ኢየሱስ የአህያ ውርንጫ አግኝቶ በእርሱ ተቀመጠ።
15“Nebijok, Siono dukra: štai atvyksta tavo karalius, sėdėdamas ant asilaičio!”
16ደቀ መዛሙርቱም ይህን ነገር በመጀመሪያ አላስተዋሉም፤ ነገር ግን ኢየሱስ ከከበረ በኋላ በዚያን ጊዜ ይህ ስለ እርሱ እንደ ተጻፈ ይህንም እንዳደረጉለት ትዝ አላቸው።
16Iš pradžių mokiniai šito nesuprato, bet, kai Jėzus buvo pašlovintas, atsiminė, kad tai buvo apie Jį parašyta ir jie buvo Jam tai padarę.
17አልዓዛርንም ከመቃብር ጠርቶ ከሙታን ሲያስነሣው ከእርሱ ጋር የነበሩት ሕዝብ ይመሰክሩለት ነበር።
17Taigi dabar liudijo minia, buvusi su Juo, kai Jis pašaukė Lozorių iš kapo ir prikėlė iš numirusių.
18ስለዚህ ደግሞ ሕዝቡ ይህን ምልክት እንዳደረገ ስለ ሰሙ ሊቀበሉት ወጡ።
18Žmonės todėl ir išėjo Jo pasitikti, kad buvo girdėję Jį padarius tą ženklą.
19ሰለዚህ ፈሪሳውያን እርስ በርሳቸው። አንድ ስንኳ ልታደርጉ እንዳይቻላችሁ ታያላችሁን? እነሆ፥ ዓለሙ በኋላው ተከትሎት ሄዶአል ተባባሉ።
19O fariziejai kalbėjo vieni kitiems: “Žiūrėkite, jūs nieko negalite padaryti. Štai visas pasaulis nuėjo paskui Jį!”
20በበዓሉም ሊሰግዱ ከወጡት አንዳንዶቹ የግሪክ ሰዎች ነበሩ፤
20Tarp atėjusių per šventes pagarbinti buvo ir graikų.
21እነርሱም ከገሊላ ቤተ ሳይዳ ወደሚሆን ወደ ፊልጶስ መጥተው። ጌታ ሆይ፥ ኢየሱስን ልናይ እንወዳለን ብለው ለመኑት።
21Jie priėjo prie Pilypo, kilusio iš Galilėjos miesto Betsaidos, ir paprašė: “Gerbiamasis, mes norėtume pamatyti Jėzų”.
22ፊልጶስም መጥቶ ለእንድርያስ ነገረው፤ እንድርያስና ፊልጶስ መጥተው ለኢየሱስ ነገሩት።
22Pilypas nuėjo ir pasakė Andriejui. Paskui Andriejus ir Pilypas pranešė Jėzui.
23ኢየሱስም መለሰላቸው፥ እንዲህ ሲል። የሰው ልጅ ይከብር ዘንድ ሰዓቱ ደርሶአል።
23O Jėzus jiems tarė: “Atėjo valanda, kad būtų pašlovintas Žmogaus Sūnus.
24እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ የስንዴ ቅንጣት በምድር ወድቃ ካልሞተች ብቻዋን ትቀራለች፤ ብትሞት ግን ብዙ ፍሬ ታፈራለች።
24Iš tiesų, iš tiesų sakau jums: jei kviečio grūdas nekris į žemę ir nenumirs, jis pasiliks vienas, o jei numirs, jis duos gausių vaisių.
25ነፍሱን የሚወድ ያጠፋታል፥ ነፍሱንም በዚህ ዓለም የሚጠላ ለዘላለም ሕይወት ይጠብቃታል።
25Kas myli savo gyvybę, ją praras, o kas nekenčia savo gyvybės šiame pasaulyje, išsaugos ją amžinajam gyvenimui.
26የሚያገለግለኝ ቢኖር ይከተለኝ፥ እኔም ባለሁበት አገልጋዬ ደግሞ በዚያ ይሆናል፤ የሚያገለግለኝም ቢኖር አብ ያከብረዋል።
26Kas man tarnauja, tegul seka paskui mane; ir kur Aš esu, ten bus ir mano tarnas. Kas man tarnauja, tą pagerbs mano Tėvas.
27አሁን ነፍሴ ታውካለች ምንስ እላለሁ? አባት ሆይ፥ ከዚህ ሰዓት አድነኝ። ነገር ግን ስለዚህ ወደዚህ ሰዓት መጣሁ።
27Dabar mano siela sukrėsta. Ir ką Aš pasakysiu: ‘Tėve, gelbėk mane nuo šios valandos!’? Bet juk tam Aš ir atėjau į šią valandą.
28አባት ሆይ፥ ስምህን አክብረው። ስለዚህም። አከበርሁት ደግሞም አከብረዋለሁ የሚል ድምፅ ከሰማይ መጣ።
28Tėve, pašlovink savo vardą!” Tada iš dangaus pasigirdo balsas: “Aš jį pašlovinau ir dar pašlovinsiu!”
29በዚያ ቆመው የነበሩትም ሕዝብ በሰሙ ጊዜ። ነጐድጓድ ነው አሉ፤ ሌሎች። መልአክ ተናገረው አሉ።
29Aplink stovinti minia, tai išgirdusi, sakė griaustinį sugriaudus. Kai kurie tvirtino: “Angelas Jam kalbėjo”.
30ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል። ይህ ድምፅ ስለ እናንተ መጥቶአል እጂ ስለ እኔ አይደለም።
30O Jėzus atsakė: “Ne dėl manęs, o dėl jūsų pasigirdo šitas balsas.
31አሁን የዚህ ዓለም ፍርድ ደርሶአል፤ አሁን የዚህ ዓለም ገዥ ወደ ውጭ ይጣላል፤
31Dabar teisiamas šitas pasaulis. Dabar šio pasaulio kunigaikštis bus išmestas laukan.
32እኔም ከምድር ከፍ ከፍ ያልሁ እንደ ሆነ ሁሉን ወደ እኔ እስባለሁ።
32O Aš, kai būsiu pakeltas nuo žemės, visus patrauksiu prie savęs”.
33በምን ዓይነትም ሞት ይሞት ዘንድ እንዳለው ሲያመለክታቸው ይህን ተናገረ።
33Jis tai pasakė, nurodydamas, kokia mirtimi Jam reikės mirti.
34እንግዲህ ሕዝቡ። እኛስ ክርስቶስ ለዘላለም እንዲኖር ከሕጉ ሰምተናል፤ አንተስ የሰው ልጅ ከፍ ከፍ ይል ዘንድ እንዲያስፈልገው እንዴት ትላላህ? ይህ የሰው ልጅ ማን ነው? ብለው መለሱለት።
34O žmonės Jam sakė: “Mes girdėjome iš Įstatymo, kad Kristus pasilieka per amžius. Kodėl Tu sakai, kad Žmogaus Sūnus turės būti iškeltas aukštyn? Kas gi tas Žmogaus Sūnus?”
35ኢየሱስም። ገና ጥቂት ጊዜ ብርሃን ከእናንተ ጋር ነው። ጨለማ እንዳይደርስባችሁ ብርሃን ሳለላችሁ ተመላለሱ፤ በጨለማም የሚመላለስ ወዴት እንዲሄድ አያውቅም።
35Jėzus jiems tarė: “Dar trumpą laiką šviesa bus su jumis. Vaikščiokite, kol turite šviesą, kad neužkluptų jūsų tamsa. Kas vaikščioja tamsoje, tas nežino, kur eina.
36የብርሃን ልጆች እንድትሆኑ ብርሃን ሳለላችሁ በብርሃኑ እመኑ አላቸው። ኢየሱስም ይህን ተናግሮ ሄደና ተሰወረባቸው።
36Kol turite šviesą, tikėkite ją, kad taptumėte šviesos vaikais”. Tai pasakęs, Jėzus pasišalino ir pasislėpė nuo jų.
37ነገር ግን ይህን ያህል ምልክት በፊታቸው ምንም ቢያደርግ፤ ነቢዩ ኢሳይያስ። ጌታ ሆይ፥ ማን ምስክርነታችንን አመነ? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገለጠ? ብሎ የተናገረው ቃል ይፈጸም ዘንድ በእርሱ አላመኑም።
37Nors Jis jų akivaizdoje padarė tiek daug ženklų, jie Juo netikėjo,
39ኢሳይያስ ደግሞ። በዓይኖቻቸው እንዳያዩ፥ በልባቸውም እንዳያስተውሉ፥ እንዳይመለሱም፥ እኔም እንዳልፈውሳቸው፥ ዓይኖቻቸውን አሳወረ ልባቸውንም አደነደነ ብሎአልና ስለዚህ ማመን አቃታቸው።
38kad išsipildytų pranašo Izaijo žodžiai: “Viešpatie, kas patikėjo mūsų skelbimu ir kam buvo apreikšta Viešpaties rankos galybė?”
41ክብሩን ስለ አየ ኢሳይያስ ይህን አለ፥ ስለ እርሱም ተናገረ።
39Jie neįstengė tikėti, nes vėl, anot Izaijo:
42ከዚህም ጋር ከአለቆች ደግሞ ብዙዎች በእርሱ አመኑ፤ ነገር ግን ከምኵራብ እንዳያስወጡአቸው በፈሪሳውያን ምክንያት አልመሰከሩለትም፤
40“Jis apakino jų akis ir sukietino jų širdį, kad nematytų akimis ir nesuvoktų širdimi, ir neatsiverstų, ir Aš jų nepagydyčiau”.
43ከእግዚአብሔር ክብር ይልቅ የሰውን ክብር ወደዋልና።
41Izaijas tai pasakė, regėdamas Jo šlovę ir kalbėdamas apie Jį.
44ኢየሱስም ጮኸ፥ እንዲህም አለ። በእኔ የሚያምን በላከኝ ማመኑ ነው እንጂ በእኔ አይደለም፤
42Vis dėlto daugelis įtikėjo Jėzų net iš vyresnybės, tačiau dėl fariziejų Jo neišpažino, kad nebūtų pašalinti iš sinagogos,
45እኔንም የሚያይ የላከኝን ያያል።
43nes žmonių šlovę jie brangino labiau už Dievo šlovę.
46በእኔ የሚያምን ሁሉ በጨለማ እንዳይኖር እኔ ብርሃን ሆኜ ወደ ዓለም መጥቻለሁ።
44O Jėzus šaukė: “Kas mane tiki, tiki ne mane, bet Tą, kuris mane siuntė.
47ዓለምን ላድን እንጂ በዓለም ልፈርድ አልመጣሁምና ቃሌን ሰምቶ የማይጠብቀው ቢኖር የምፈርድበት እኔ አይደለሁም።
45Ir kas mane mato, mato Tą, kuris mane siuntė.
48የሚጥለኝ ቃሌንም የማይቀበለው እርሱ የሚፈርድበት አለው፤ እኔ የተናገርሁት ቃል እርሱ በመጨረሻው ቀን ይፈርድበታል።
46Aš atėjau į pasaulį kaip šviesa, kad visi, kurie mane tiki, neliktų tamsoje.
49እኔ ከራሴ አልተናገርሁምና፤ ነገር ግን የላከኝ አብ እርሱ የምለውን የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ።
47Jei kas klausosi mano žodžių ir netiki, Aš jo neteisiu, nes atėjau ne teisti pasaulio, bet gelbėti pasaulį.
50ትእዛዙም የዘላለም ሕይወት እንደ ሆነች አውቃለሁ። ስለዚህ እኔ የምናገረውን አብ እንደ ነገረኝ እንዲሁ እናገራለሁ።
48Kas mane atstumia ir mano žodžių nepriima, tas turi savo teisėją: žodis, kurį kalbėjau, teis jį paskutiniąją dieną.
49Nes Aš kalbėjau ne iš savęs,Tėvas, kuris mane siuntė, įsakė man, ką turiu sakyti ir ką skelbti.
50Aš žinau, kad Jo įsakymas yra amžinasis gyvenimas. Tad ką Aš kalbu, kalbu taip, kaip Tėvas yra man sakęs”.