1Buvo vienas ligonis, Lozorius iš Betanijos kaimo, kur gyveno Marija ir jos sesuo Morta.
1ከማርያምና ከእኅትዋ ከማርታ መንደር ከቢታንያ የሆነ አልዓዛር የሚባል አንድ ሰው ታሞ ነበር።
2Marija buvo ta pati moteris, kuri patepė Viešpatį kvepalais ir nušluostė savo plaukais Jo kojas. Jos brolis Lozorius sirgo.
2ማርያምም ጌታን ሽቱ የቀባችው እግሩንም በጠጕርዋ ያበሰችው ነበረች፤ ወንድምዋም አልዓዛር ታሞ ነበር።
3Todėl seserys nusiuntė Jam žinią: “Viešpatie! Tas, kurį Tu myli, serga!”
3ስለዚህ እኅቶቹ ጌታ ሆይ፥ እነሆ የምትወደው ታሞአል ብለው ወደ እርሱ ላኩ።
4Tai išgirdęs, Jėzus tarė: “Šita liga ne mirčiai, bet Dievo šlovei, kad per ją būtų pašlovintas Dievo Sūnus”.
4ኢየሱስም ሰምቶ። ይህ ህመም የእግዚአብሔር ልጅ በእርሱ ይከብር ዘንድ ስለ እግዚአብሔር ክብር ነው እንጂ ለሞት አይደለም አለ።
5Jėzus mylėjo Mortą, jos seserį ir Lozorių.
5ኢየሱስም ማርታንና እኅትዋን አልዓዛርንም ይወድ ነበር።
6Taigi išgirdęs, kad tasai serga, Jis dar dvi dienas užtruko ten, kur buvo.
6እንደ ታመመም በሰማ ጊዜ ያን ጊዜ በነበረበት ስፍራ ሁለት ቀን ዋለ፤
7Po to pasakė mokiniams: “Eikime vėl į Judėją!”
7ከዚህም በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ። ወደ ይሁዳ ደግሞ እንሂድ አላቸው።
8Mokiniai Jam atsakė: “Rabi, ką tik žydai kėsinosi užmėtyti Tave akmenimis, o Tu vėl ten eini?”
8ደቀ መዛሙርቱ። መምህር ሆይ፥ አይሁድ ከጥቂት ጊዜ በፊት ሊወግሩህ ይፈልጉ ነበር፥ ደግሞም ወደዚያ ትሄዳለህን? አሉት።
9Jėzus tarė: “Argi ne dvylika valandų turi diena? Kas vaikščioja dieną, tas nesuklumpa, nes mato šio pasaulio šviesą.
9ኢየሱስም መልሶ። ቀኑ አሥራ ሁለት ሰዓት አይደለምን? በቀን የሚመላለስ ቢኖር የዚህን ዓለም ብርሃን ያያልና አይሰናከልም፤
10O kas vaikščioja naktį, suklumpa, nes jame nėra šviesos”.
10በሌሊት የሚመላለስ ቢኖር ግን ብርሃን በእርሱ ስለ ሌለ ይሰናከላል አላቸው።
11Tai pasakęs, pridūrė: “Mūsų bičiulis Lozorius užmigo, bet Aš einu jo pažadinti”.
11ይህን ተናገረ፤ ከዚህም በኋላ። ወዳጃችን አልዓዛር ተኝቶአል፤ ነገር ግን ከእንቅልፉ ላስነሣው እሄዳለሁ አላቸው።
12Jo mokiniai atsiliepė: “Viešpatie, jeigu jis miega, pasveiks”.
12እንግዲህ ደቀ መዛሙርቱ። ጌታ ሆይ፥ ተኝቶስ እንደ ሆነ ይድናል አሉት።
13Tačiau Jėzus kalbėjo apie jo mirtį, o jie manė, kad Jis kalba apie poilsio miegą.
13ኢየሱስስ ስለ ሞቱ ተናግሮ ነበር፤ እነርሱ ግን ስለ እንቅልፍ መተኛት እንደ ተናገረ መሰላቸው።
14Pagaliau Jėzus atvirai jiems pasakė: “Lozorius mirė.
14እንግዲህ ያን ጊዜ ኢየሱስ በግልጥ። አልዓዛር ሞተ፤
15Ir Aš džiaugiuosi, kad ten nebuvau,dėl jūsų, kad tikėtumėte. Tad eikime pas jį”.
15እንድታምኑም በዚያ ባለመኖሬ ስለ እናንተ ደስ ይለኛል፤ ነገር ግን ወደ እርሱ እንሂድ አላቸው።
16Tuomet Tomas, vadinamas Dvyniu, tarė kitiems mokiniams: “Eikime ir mes numirti su Juo!”
16ስለዚህ ዲዲሞስ የሚሉት ቶማስ ለባልንጀሮቹ ለደቀ መዛሙርት። ከእርሱ ጋር እንሞት ዘንድ እኛ ደግሞ እንሂድ አለ።
17Atėjęs Jėzus rado Lozorių jau keturias dienas išgulėjusį kape.
17ኢየሱስም በመጣ ጊዜ በመቃብር እስከ አሁን አራት ቀን ሆኖት አገኘው።
18O Betanija buvo arti Jeruzalės, maždaug penkiolika stadijų atstu.
18ቢታንያም አሥራ አምስት ምዕራፍ ያህል ለኢየሩሳሌም ቅርብ ነበረች።
19Daug žydų buvo atėję pas Mortą ir Mariją paguosti jų dėl brolio.
19ከአይሁድም ብዙዎች ስለ ወንድማቸው ሊያጽናኑአቸው ወደ ማርታና ወደ ማርያም መጥተው ነበር።
20Morta, išgirdusi ateinant Jėzų, išėjo Jo pasitikti. Marija sėdėjo namie.
20ማርታም ኢየሱስ እንደ መጣ በሰማች ጊዜ ልትቀበለው ወጣች፤ ማርያም ግን በቤት ተቀምጣ ነበር።
21Morta tarė Jėzui: “Viešpatie, jei būtum čia buvęs, mano brolis nebūtų miręs.
21ማርታም ኢየሱስን። ጌታ ሆይ፥ አንተ በዚህ ኖረህ ብትሆን ወንድሜ ባልሞተም ነበር፤
22Bet ir dabar žinau: ko tik prašysi Dievo, Dievas Tau duos”.
22አሁንም ከእግዚአብሔር የምትለምነውን ሁሉ እግዚአብሔር እንዲሰጥህ አውቃለሁ አለችው።
23Jėzus jai pasakė: “Tavo brolis prisikels!”
23ኢየሱስም። ወንድምሽ ይነሣል አላት።
24Morta atsiliepė: “Aš žinau, jog jis prisikels prisikėlime, paskutinę dieną”.
24ማርታም። በመጨረሻው ቀን በትንሣኤ እንዲነሣ አውቃለሁ አለችው።
25Jėzus jai tarė: “Aš esu prisikėlimas ir gyvenimas. Kas tiki mane, nors ir mirtų, bus gyvas.
25ኢየሱስም። ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል፤
26Ir kiekvienas, kuris gyvena ir tiki mane, nemirs per amžius. Ar tai tiki?”
26ሕያው የሆነም የሚያምንብኝም ሁሉ ለዘላለም አይሞትም፤ ይህን ታምኚያለሽን? አላት።
27Ji atsakė: “Taip, Viešpatie! Aš tikiu, jog Tu esi Kristus, Dievo Sūnus, kuris turi ateiti į šį pasaulį”.
27እርስዋም። አዎን ጌታ ሆይ፤ አንተ ወደ ዓለም የሚመጣው ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆንህ እኔ አምናለሁ አለችው።
28Tai pasakiusi, ji nuėjo ir slapčiomis pašaukė savo seserį Mariją, jai pranešdama: “Mokytojas atėjo ir šaukia tave”.
28ይህንም ብላ ሄደች እኅትዋንም ማርያምን በስውር ጠርታ። መምህሩ መጥቶአል ይጠራሽማል አለቻት።
29Išgirdusi ši greitai pakilo ir nuėjo pas Jį.
29እርስዋም በሰማች ጊዜ ፈጥና ተነሣች ወደ እርሱም መጣች፤
30Jėzus dar nebuvo įėjęs į kaimą, bet tebebuvo toje vietoje, kur Jį pasitiko Morta.
30ኢየሱስም ማርታ በተቀበለችበት ስፍራ ነበረ እንጂ ገና ወደ መንደሩ አልገባም ነበር።
31Kai žydai, buvę su ja namuose ir ją guodę, pamatė ją skubiai keliantis ir išeinant, nusekė paskui, sakydami: “Ji eina prie kapo”.
31ሲያጽናኑአት ከእርስዋ ጋር በቤት የነበሩ አይሁድም ማርያም ፈጥና እንደ ተነሣችና እንደ ወጣች ባዩ ጊዜ፥ ወደ መቃብር ሄዳ በዚያ ልታለቅስ መስሎአቸው ተከተሉአት።
32Marija, atėjusi ten, kur buvo Jėzus, ir Jį pamačiusi, puolė Jam po kojų, sakydama: “Viešpatie, jei būtum čia buvęs, mano brolis nebūtų miręs”.
32ማርያምም ኢየሱስ ወዳለበት መጥታ ባየችው ጊዜ በእግሩ ላይ ወድቃ። ጌታ ሆይ፥ አንተ በዚህ ኖረህ ብትሆን ወንድሜ ባልሞተም ነበር አለችው።
33Jėzus, pamatęs ją ir kartu atėjusius žydus verkiančius, sudejavo dvasioje ir susijaudinęs
33ኢየሱስም እርስዋ ስታለቅስ ከእርስዋም ጋር የመጡት አይሁድ ሲያለቅሱ አይቶ በመንፈሱ አዘነ በራሱም ታወከ፤
34paklausė: “Kur jį paguldėte?” Jie atsakė: “Viešpatie, eik ir pažiūrėk”.
34ወዴት አኖራችሁት? አለም። እነርሱም። ጌታ ሆይ፥ መጥተህ እይ አሉት።
35Jėzus pravirko.
35ኢየሱስም እንባውን አፈሰሰ።
36Tada žydai ėmė kalbėti: “Štai kaip Jis jį mylėjo!”
36ስለዚህ አይሁድ። እንዴት ይወደው እንደ ነበረ እዩ አሉ።
37O kiti sakė: “Argi Tas, kuris atvėrė neregiui akis, negalėjo padaryti, kad šitas nemirtų?”
37ከእነርሱ ግን አንዳንዶቹ። ይህ የዕውሩን ዓይኖች የከፈተ ይህን ደግሞ እንዳይሞት ያደርግ ዘንድ ባልቻለም ነበርን? አሉ።
38Ir vėl dejuodamas Jėzus atėjo prie kapo. Tai buvo ola, užrista akmeniu.
38ኢየሱስም በራሱ አዝኖ ወደ መቃብሩ መጣ፤ እርሱም ዋሻ ነበረ፤ ድንጋይም ተገጥሞበት ነበር።
39Jėzus tarė: “Nuriskite akmenį!” Mirusiojo sesuo Morta įspėjo: “Viešpatie, jis jau dvokia, nes jau keturios dienos, kai jis miręs”.
39ኢየሱስ። ድንጋዩን አንሡ አለ። የሞተውም እኅት ማርታ። ጌታ ሆይ፥ ከሞተ አራት ቀን ሆኖታልና አሁን ይሸታል አለችው።
40Jėzus jai tarė: “Argi nesakiau tau, kad jei tikėsi, pamatysi Dievo šlovę?!”
40ኢየሱስ። ብታምኚስ የእግዚአብሔርን ክብር እንድታዪ አልነገርሁሽምን? አላት።
41Jie nurito akmenį nuo ten, kur gulėjo numirėlis. Jėzus pakėlė akis aukštyn ir prabilo: “Tėve, dėkoju Tau, kad mane išgirdai.
41ድንጋዩንም አነሡት። ኢየሱስም ዓይኖቹን ወደ ላይ አንሥቶ። አባት ሆይ፥ ስለ ሰማኸኝ አመሰግንሃለሁ።
42Aš žinojau, kad visada mane girdi. Tačiau tai sakau dėl čia esančiųjų, kad jie tikėtų, jog Tu esi mane siuntęs”.
42ሁልጊዜም እንድትሰማኝ አወቅሁ፤ ነገር ግን አንተ እንደ ላክኸኝ ያምኑ ዘንድ በዚህ ዙሪያ ስለ ቆሙት ሕዝብ ተናገርሁ አለ።
43Tai pasakęs, Jis galingu balsu sušuko: “Lozoriau, išeik!”
43ይህንም ብሎ በታላቅ ድምፅ። አልዓዛር ሆይ፥ ወደ ውጭ ና ብሎ ጮኸ።
44Ir numirėlis išėjo. Jo rankos ir kojos buvo apvyniotos laidojimo aprišalais, veidas aprištas drobule. Jėzus jiems liepė: “Atvyniokite jį ir leiskite jam eiti”.
44የሞተውም እጆቹና እግሮቹ በመግነዝ እንደ ተገነዙ ወጣ፤ ፈቱም በጨርቅ እንደ ተጠመጠመ ነበር። ኢየሱስም። ፍቱትና ይሂድ ተዉት አላቸው።
45Daugelis žydų, kurie buvo atėję pas Mariją ir matė, ką Jėzus padarė, įtikėjo Jį.
45ስለዚህ ወደ ማርያም ከመጡት፥ ኢየሱስም ያደረገውን ካዩት ከአይሁድ ብዙዎች በእርሱ አመኑ፤
46Bet kai kurie nuėjo pas fariziejus ir pranešė jiems, ką Jėzus padaręs.
46ከእነርሱ አንዳንዶቹ ግን ወደ ፈሪሳውያን ሄደው ኢየሱስ ያደረገውን ነገሩአቸው።
47Tada aukštieji kunigai ir fariziejai sušaukė sinedrioną ir svarstė: “Ką darysime? Šitas žmogus daro daug ženklų.
47እንግዲህ የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን ሸንጎ ሰብስበው። ምን እናድርግ? ይህ ሰው ብዙ ምልክቶች ያደርጋልና።
48Jei taip Jį paliksime, visi įtikės Jį; ateis romėnai ir užims mūsų vietą bei tautą”.
48እንዲሁ ብንተወው ሁሉ በእርሱ ያምናሉ፤ የሮሜም ሰዎች መጥተው አገራችንን ወገናችንንም ይወስዳሉ አሉ።
49Vienas iš jųKajafas, tais metais vyriausiasis kunigasjiems tarė: “Jūs nieko neišmanote
49በዚያችም ዓመት ሊቀ ካህናት የነበረ ቀያፋ የሚሉት ከእነርሱ አንዱ። እናንተ ምንም አታውቁም፤
50ir nepagalvojate, jog mums geriau, kad vienas žmogus mirtų už tautą, o ne visa tauta žūtų”.
50ሕዝቡም ሁሉ ከሚጠፋ አንድ ሰው ስለ ሕዝቡ ይሞት ዘንድ እንዲሻለን አታስቡም አላቸው።
51Jis tai pasakė ne iš savęs, bet, būdamas tų metų vyriausiasis kunigas, pranašavo, jog Jėzui reikės mirti už tautą,
51ይህንም የተናገረ ከራሱ አይደለም፥ ነገር ግን በዚያች ዓመት ሊቀ ካህናት ነበረና ኢየሱስ ስለ ሕዝቡ ሊሞት እንዳለው ትንቢት ተናገረ፤
52ir ne tik už tautą, bet tam, kad suburtų į viena išsklaidytuosius Dievo vaikus.
52ስለ ሕዝቡም ሁሉ አይደለም፥ ነገር ግን የተበተኑትን የእግዚአብሔርን ልጆች ደግሞ በአንድነት እንዲሰበስባቸው ነው እንጂ።
53Nuo tos dienos jie buvo nusprendę Jį nužudyti.
53እንግዲህ ከዚያ ቀን ጀምረው ሊገድሉት ተማከሩ።
54Todėl Jėzus nebevaikščiojo viešai tarp žydų, bet pasitraukė iš ten į vietovę netoli dykumos, į miestelį, vadinamą Efraimu, ir ten apsistojo kartu su savo mokiniais.
54ከዚያ ወዲያም ኢየሱስ በአይሁድ መካከል ተገልጦ አልተመላለሰም፤ ነገር ግን ከዚያ በምድረ በዳ አጠገብ ወዳለች ምድር፥ ኤፍሬም ወደምትባል ከተማ ሄደ፤ በዚያም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ተቀመጠ።
55Artinosi žydų Pascha. Daugelis iš viso krašto prieš Paschą atėjo į Jeruzalę apsivalyti.
55የአይሁድም ፋሲካ ቀርቦ ነበር። ብዙ ሰዎችም ራሳቸውን ያነጹ ዘንድ ከፋሲካ በፊት ከአገሩ ወደ ኢየሩሳሌም ወጡ።
56Jie ieškojo Jėzaus ir, stoviniuodami šventykloje, kalbėjosi: “Kaip jūs manote? Nejaugi Jis nebeateis į šventę?”
56ኢየሱስንም ይፈልጉት ነበር፤ በመቅደስም ቆመው እርስ በርሳቸው። ምን ይመስላችኋል? ወደ በዓሉ አይመጣም ይሆንን? ተባባሉ።
57Mat aukštieji kunigai ir fariziejai išleido įsakymą, kad žinantys praneštų, kur Jis esąs, kad galėtų Jį suimti.
57የካህናት አለቆችም ፈሪሳውያንም ይይዙት ዘንድ እርሱ ያለበትን ስፍራ የሚያውቀው ሰው ቢኖር እንዲያመለክታቸው አዘው ነበር።