1“Aš jums tai pasakiau, kad nepasipiktintumėte.
1እንዳትሰናከሉ ይህን ተናግሬአችኋለሁ።
2Jie šalins jus iš sinagogų, ir ateina valanda, kada tie, kurie jus žudys, tarsis tarnaują Dievui.
2ከምኵራባቸው ያወጡአችኋል፤ ከዚህ በላይ ደግሞ የሚገድላችሁ ሁሉ እግዚአብሔርን እንደሚያገለግል የሚመስልበት ጊዜ ይመጣል።
3Jie jums tai darys, nes nei Tėvo, nei manęs nepažįsta.
3ይህንም የሚያደርጉባችሁ አብንና እኔን ስላላወቁ ነው።
4Aš jums visa tai kalbėjau, kad tai valandai atėjus, atsimintumėte, jog buvau jus įspėjęs. Aš jums to nesakiau iš pradžių, nes buvau su jumis.
4ነገር ግን ጊዜው ሲደርስ እኔ እንደ ነገርኋችሁ ታስቡ ዘንድ ይህን ተናግሬአችኋለሁ። ከእንናንተም ጋር ስለ ነበርሁ በመጀመሪያ ይህን አልነገርኋችሁም።
5O dabar einu pas Tą, kuris mane siuntė, ir niekas iš jūsų neklausia: ‘Kur Tu eini?’
5አሁን ግን ወደ ላከኝ እሄዳለሁ ከእናንተም። ወዴት ትሄዳለህ? ብሎ የሚጠይቀኝ የለም።
6Kadangi jums tai pasakiau, liūdesys jūsų širdis užliejo.
6ነገር ግን ይህን ስለ ተናገርኋችሁ ኀዘን በልባችሁ ሞልቶአል።
7Bet sakau jums tiesą: jums geriau, kad Aš išeinu, nes jei neišeičiau, pas jus neateitų Guodėjas. O nuėjęs Jį jums atsiųsiu.
7እኔ ግን እውነት እነግራችኋለሁ፤ እኔ እንድሄድ ይሻላችኋል። እኔ ባልሄድ አጽናኙ ወደ እናንተ አይመጣምና፤ እኔ ብሄድ ግን እርሱን እልክላችኋለሁ።
8Atėjęs Jis įtikins pasaulį dėl nuodėmės, dėl teisumo ir dėl teismo.
8እርሱም መጥቶ ስለ ኃጢአት ስለ ጽድቅም ስለ ፍርድም ዓለምን ይወቅሳል፤
9Dėl nuodėmės,kad netiki manimi.
9ስለ ኃጢአት፥ በእኔ ስለማያምኑ ነው፤ ስለ ጽድቅም፥ ወደ አብ ስለምሄድ ከዚህም በኋላ ስለማታዩኝ ነው፤
10Dėl teisumo,kad Aš pas savo Tėvą einu, ir jūs manęs daugiau nebematysite.
11ስለ ፍርድም፥ የዚህ ዓለም ገዥ ስለ ተፈረደበት ነው።
11Dėl teismo,kad šio pasaulio kunigaikštis yra nuteistas.
12የምነግራችሁ ገና ብዙ አለኝ፥ ነገር ግን አሁን ልትሸከሙት አትችሉም።
12Dar daug ką turiu jums pasakyti, bet dabar negalite pakelti.
13ግን እርሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል፤ የሚሰማውን ሁሉ ይናገራል እንጂ ከራሱ አይነግርምና፤ የሚመጣውንም ይነግራችኋል።
13Bet kai ateis Ji, Tiesos Dvasia, jus Ji įves į visą tiesą. Ji nekalbės iš savęs, bet kalbės, ką išgirs, ir praneš, kas dar turi įvykti.
14እርሱ ያከብረኛል፥ ለእኔ ካለኝ ወስዶ ይነግራችኋልና።
14Ji pašlovins mane, nes ims iš to, kas mano, ir jums tai paskelbs.
15ለአብ ያለው ሁሉ የእኔ ነው፤ ስለዚህ። ለእኔ ካለኝ ወስዶ ይነግራችኋል አልሁ።
15Visa, ką turi Tėvas, yra mano, todėl Aš pasakiau, kad Ji ims iš to, kas mano, ir jums tai paskelbs.
16ጥቂት ጊዜ አለ፥ አታዩኝምም፤ ደግሞም ጥቂት ጊዜ አለ፥ ታዩኛላችሁም፥ እኔ ወደ አብ እሄዳለሁና።
16Prabėgs valandėlėir manęs nematysite, ir dar valandėlėir vėl mane pamatysite, nes Aš pas Tėvą einu”.
17ከደቀ መዛሙርቱም አንዳንዶቹ እርስ በርሳቸው። ጥቂት ጊዜ አለ፥ አታዩኝምም፤ ደግሞም ጥቂት ጊዜ አለ፥ ታዩኛላችሁም፤ ደግሞ። ወደ አብ እሄዳለሁና የሚለን ይህ ምንድር ነው? ተባባሉ።
17Tada kai kurie mokiniai ėmė vienas kitą klausinėti: “Ką reiškia Jo pasakyti žodžiai: ‘Prabėgs valandėlėir manęs nematysite, ir dar valandėlėir vėl mane pamatysite’ ir: ‘Aš pas Tėvą einu’?”
18እንግዲህ። ጥቂት የሚለው ይህ ምንድር ነው? የሚናገረውን አናውቅም አሉ።
18Tad jie klausinėjo: “Ką reiškia ‘valandėlė’? Mums neaišku, ką Jis kalba”.
19ኢየሱስም ሊጠይቁት እንደ ወደዱ አውቆ እንዲህ አላቸው። ጥቂት ጊዜ አለ፥ አታዩኝምም፤ ደግሞም ጥቂት ጊዜ አለ፥ ታዩኛላችሁ ስላልሁ፥ ስለዚህ እርስ በርሳችሁ ትመራመራላችሁን?
19Supratęs, kad jie norėjo Jį klausti, Jėzus tarė: “Klausinėjate vieni kitus dėl mano žodžių: ‘Prabėgs valandėlėir manęs nematysite, ir dar valandėlėir vėl mane pamatysite’?
20እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ እናንተ ታለቅሳለችሁ ሙሾም ታወጣላችሁ፥ ዓለም ግን ደስ ይለዋል፤ እናንተም ታዝናላችሁ፥ ነገር ግን ኀዘናችሁ ወደ ደስታ ይለወጣል።
20Iš tiesų, iš tiesų sakau jums: jūs verksite ir vaitosite, o pasaulis džiaugsis. Jūs liūdėsite, bet jūsų liūdesys pavirs džiaugsmu.
21ሴት በምትወልድበት ጊዜ ወራትዋ ስለ ደረሰ ታዝናለች፤ ነገር ግን ሕፃን ከወለደች በኋላ፥ ሰው በዓለም ተወልዶአልና ስለ ደስታዋ መከራዋን ኋላ አታስበውም።
21Gimdydama moteris būna sielvarto prislėgta, nes atėjo jos valanda, bet, kūdikiui gimus, ji skausmą užmiršta iš džiaugsmo, kad gimė į pasaulį žmogus.
22እንግዲህ እናንተ ደግሞ አሁን ታዝናላችሁ፤ ነገር ግን እንደ ገና አያችኋለሁ ልባችሁም ደስ ይለዋል፥ ደስታችሁንም የሚወስድባችሁ የለም።
22Taip ir jūs dabar nuliūdę, bet Aš vėl jus pamatysiu; ir jūsų širdys džiūgaus, ir jūsų džiaugsmo niekas iš jūsų nebeatims.
23በዚያን ቀንም ከእኔ አንዳች አትለምኑም። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ አብ በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ ይሰጣችኋል።
23Tą dieną jūs manęs nieko neklausinėsite. Iš tiesų, iš tiesų sakau jums: ko tik prašysite Tėvą mano vardu, Jis jums duos.
24እስከ አሁን በስሜ ምንም አልለመናችሁም፤ ደስታችሁ ፍጹም እንዲሆን ለምኑ ትቀበሉማላችሁ።
24Iki šiol jūs nieko neprašėte mano vardu. Prašykite ir gausite, kad jūsų džiaugsmui nieko netrūktų.
25ይህን በምሳሌ ነግሬአችኋለሁ፤ ነገር ግን ስለ አብ ለእናንተ በግልጥ የምናገርበት እንጂ ከዚያ ወዲያ በምሳሌ የማልናገርበት ሰዓት ይመጣል።
25Aš jums kalbėjau palyginimais, bet ateina valanda, kada nebekalbėsiu jums palyginimais, bet atvirai apie Tėvą jums skelbsiu.
26በዚያን ቀን በስሜ ትለምናላችሁ፤ እኔም ስለ እናንተ አብን እንድለምን የምላችሁ አይደለሁም፤
26Tą dieną jūs prašysite mano vardu, ir Aš nesakau, kad Aš prašysiu Tėvą už jus,
27እናንተ ስለ ወደዳችሁኝ ከእግዚአብሔርም ዘንድ እኔ እንደ ወጣሁ ስላመናችሁ አብ እርሱ ራሱ ይወዳችኋልና።
27juk pats Tėvas jus myli, nes jūs mane pamilote ir įtikėjote, jog Aš esu iš Dievo išėjęs.
28ከአብ ወጥቼ ወደ ዓለም መጥቻለሁ፤ ደግሞ ዓለምን እተወዋለሁ ወደ አብም እሄዳለሁ።
28Išėjau iš Tėvo ir atėjau į pasaulį. Vėl palieku pasaulį ir einu pas Tėvą”.
29ደቀ መዛሙርቱ። እነሆ፥ አሁን በግልጥ ትናገራለህ በምሳሌም ምንም አትነግርም።
29Mokiniai tarė: “Štai dabar Tu aiškiai kalbi ir nebesakai jokių palyginimų.
30ሁሉን እንድታውቅ ማንምም ሊጠይቅህ እንዳትፈልግ አሁን እናውቃለን፤ ስለዚህ ከእግዚአብሔር እንደ ወጣህ እናምናለን አሉት።
30Mes dabar suprantame, kad Tu viską žinai ir nereikia, kad kas Tave klausinėtų. Todėl tikime, kad Tu esi išėjęs iš Dievo”.
31ኢየሱስም እንዲህ ብሎ መለሰላቸው። አሁን ታምናላችሁን?
31Jėzus jiems atsakė: “Dabar tikite?
32እነሆ፥ እያንዳንዳችሁ ወደ ቤት የምትበታተኑበት እኔንም ለብቻዬ የምትተዉበት ሰዓት ይመጣል፥ አሁንም ደርሶአል፤ ነገር ግን አብ ከእኔ ጋር ስለ ሆነ ብቻዬን አይደለሁም።
32Štai ateina valanda,ir jau atėjo,kai jūs išsisklaidysite kas sau ir paliksite mane vieną. Tačiau Aš ne vienas, nes su manimi yra Tėvas.
33በእኔ ሳላችሁ ሰላም እንዲሆንላችሁ ይህን ተናግሬአችኋለሁ። በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።
33Aš jums tai kalbėjau, kad manyje turėtumėte ramybę. Pasaulyje jūs turėsite priespaudą, bet būkite drąsūs: Aš nugalėjau pasaulį!”