Lithuanian

Amharic: New Testament

John

17

1Tai pasakęs, Jėzus pakėlė akis į dangų ir prabilo: “Tėve, atėjo valanda! Pašlovink savo Sūnų, kad ir Tavo Sūnus pašlovintų Tave;
1ኢየሱስም ይህን ተናግሮ ወደ ሰማይ ዓይኖቹን አነሣና እንዲህ አለ። አባት ሆይ፥ ሰዓቱ ደርሶአል፤ ልጅህ ያከብርህ ዘንድ፥ በሥጋም ሁሉ ላይ ሥልጣን እንደ ሰጠኸው፥ ለሰጠኸው ሁሉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸው ዘንድ ልጅህን አክብረው።
2nes Tu davei Jam valdžią kiekvienam kūnui, kad visiems, kuriuos esi Jam davęs, Jis teiktų amžinąjį gyvenimą.
3እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት።
3Tai yra amžinasis gyvenimas: kad jie pažintų Tave, vienintelį tikrąjį Dievą ir Tavo siųstąjį Jėzų Kristų.
4እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ፤
4Aš pašlovinau Tave žemėje. Atlikau darbą, kurį buvai man davęs nuveikti.
5አሁንም፥ አባት ሆይ፥ ዓለም ሳይፈጠር በአንተ ዘንድ በነበረኝ ክብር አንተ በራስህ ዘንድ አክብረኝ።
5Dabar Tu, Tėve, pašlovink mane pas save ta šlove, kurią pas Tave turėjau dar prieš pasaulio buvimą.
6ከዓለም ለሰጠኸኝ ሰዎች ስምህን ገለጥሁላቸው። የአንተ ነበሩ ለእኔም ሰጠሃቸው፤
6Aš apreiškiau Tavo vardą žmonėms, kuriuos man davei iš pasaulio. Jie buvo Tavo, ir Tu juos davei man, ir jie laikėsi Tavojo žodžio.
7ቃልህንም ጠብቀዋል። የሰጠኸኝ ሁሉ ከአንተ እንደ ሆነ አሁን ያውቃሉ፤
7Dabar jie suprato, kad visa, ką man davei, yra iš Tavęs.
8የሰጠኸኝን ቃል ሰጥቻቸዋለሁና፤ እነርሱም ተቀበሉት፥ ከአንተም ዘንድ እንደ ወጣሁ በእውነት አወቁ፥ አንተም እንደ ላክኸኝ አመኑ።
8Nes Tavo man duotus žodžius Aš perdaviau jiems, ir jie priėmė juos ir tikrai pažino, kad iš Tavęs išėjau, ir jie įtikėjo, kad mane siuntei.
9እኔ ስለ እነዚህ እለምናለሁ፤ ስለ ዓለም አልለምንም ስለ ሰጠኸኝ እንጂ፤ የአንተ ናቸውና፤
9Aš meldžiu už juos. Ne už pasaulį meldžiu, bet už tuos, kuriuos man davei, nes jie yra Tavo!
10የእኔም የሆነ ሁሉ የአንተ ነው የአንተውም የእኔ ነው፤ እኔም ስለ እነርሱ ከብሬአለሁ።
10Ir visa, kas mano, yra Tavo, o kas Tavo, yra mano, ir Aš pašlovintas juose.
11ከዚህም በኋላ በዓለም አይደለሁም፥ እነርሱም በዓለም ናቸው፥ እኔም ወደ አንተ እመጣለሁ። ቅዱስ አባት ሆይ፥ እነዚህን የሰጠኸኝን እንደ እኛ አንድ እንዲሆኑ በስምህ ጠብቃቸው።
11Aš jau nebe pasaulyje, bet jie dar pasaulyje. Aš einu pas Tave. Šventasis Tėve, išlaikyk juos savo vardu­tuos, kuriuos man davei, kad jie būtų viena kaip ir mes.
12ከእነርሱ ጋር በዓለም ሳለሁ የሰጠኸኝን በስምህ እኔ እጠብቃቸው ነበር፤ ጠበቅኋቸውም መጽሐፉም እንዲፈጸም ከጥፋት ልጅ በቀር ከእነርሱ ማንም አልጠፋም።
12Kol buvau su jais pasaulyje, Aš išlaikiau juos Tavo vardu; Aš išsaugojau tuos, kuriuos man davei, ir nė vienas iš jų nepražuvo, išskyrus pražūties sūnų, kad išsipildytų Raštas.
13አሁንም ወደ አንተ እመጣለሁ፤ በእነርሱም ዘንድ ደስታዬ የተፈጸመ እንዲሆንላቸው ይህን በዓለም እናገራለሁ።
13Bet dabar Aš einu pas Tave ir tai kalbu pasaulyje, kad jie turėtų savyje tobulą mano džiaugsmą.
14እኔ ቃልህን ሰጥቻቸዋለሁ፤ እኔም ከዓለም እንዳይደለሁ ከዓለም አይደሉምና ዓለም ጠላቸው።
14Aš jiems daviau Tavo žodį, ir pasaulis jų nekentė, nes jie ne iš pasaulio, kaip ir Aš ne iš pasaulio.
15ከክፉ እንድትጠብቃቸው እንጂ ከዓለም እንድታወጣቸው አልለምንም።
15Aš neprašau, kad juos paimtum iš pasaulio, bet kad apsaugotum juos nuo pikto.
16እኔ ከዓለም እንዳይደለሁ ከዓለም አይደሉም።
16Jie nėra iš pasaulio, kaip ir Aš ne iš pasaulio.
17በእውነትህ ቀድሳቸው፤ ቃልህ እውነት ነው።
17Pašventink juos savo tiesa! Tavo žodis yra tiesa.
18ወደ ዓለም እንደ ላክኸኝ እንዲሁ እኔ ወደ ዓለም ላክኋቸው፤
18Kaip Tu mane siuntei į pasaulį, taip ir Aš juos pasiunčiau į pasaulį.
19እነርሱም ደግሞ በእውነት የተቀደሱ እንዲሆኑ እኔ ራሴን ስለ እነርሱ እቀድሳለሁ።
19Dėl jų Aš pašventinu save, kad ir jie būtų pašventinti tiesa.
20ሁሉም አንድ ይሆኑ ዘንድ፥ ከቃላቸው የተነሣ በእኔ ስለሚያምኑ ደግሞ እንጂ ስለ እነዚህ ብቻ አልለምንም፤ አንተ እንደ ላክኸኝ ዓለም ያምን ዘንድ፥ አንተ፥ አባት ሆይ፥ በእኔ እንዳለህ እኔም በአንተ፥ እነርሱ ደግሞ በእኛ አንድ ይሆኑ ዘንድ እለምናለሁ።
20Ne tik už juos meldžiu, bet ir už tuos, kurie per jų žodį mane įtikės,­
22እኛም አንድ እንደ ሆንን አንድ ይሆኑ ዘንድ፤ እኔም በእነርሱ አንተም በእኔ ስትሆን፥ በአንድ ፍጹማን እንዲሆኑ፥ የሰጠኸኝን ክብር እኔ ሰጥቻቸዋለሁ፤ እንዲሁም ዓለም አንተ እንደ ላክኸኝ በወደድኸኝም መጠን እነርሱን እንደ ወደድሃቸው ያውቃል።
21kad jie visi būtų viena. Kaip Tu, Tėve, manyje ir Aš Tavyje, kad ir jie būtų viena mumyse, kad pasaulis įtikėtų, jog Tu mane siuntei.
24አባት ሆይ፥ ዓለም ሳይፈጠር ስለ ወደድኸኝ የሰጠኸኝን ክብሬን እንዲያዩ እኔ ባለሁበት የሰጠኸኝ እነርሱ ደግሞ ከእኔ ጋር ይሆኑ ዘንድ እወዳለሁ።
22Ir tą šlovę, kurią man suteikei, daviau jiems, kad jie būtų viena, kaip mes esame viena:
25ጻድቅ አባት ሆይ፥ ዓለም አላወቀህም፥ እኔ ግን አወቅሁህ እነዚህም አንተ እንደ ላክኸኝ አወቁ፤
23Aš juose ir Tu manyje, kad jie pasiektų tobulą vienybę, ir pasaulis pažintų, jog Tu mane siuntei ir pamilai juos taip, kaip myli mane.
26እኔንም የወደድህባት ፍቅር በእነርሱ እንድትሆን እኔም በእነርሱ፥ ስምህን አስታወቅኋቸው አስታውቃቸውማለሁ።
24Tėve, Aš noriu, kad tie, kuriuos davei, taip pat būtų su manimi ten, kur Aš esu, kad jie matytų mano šlovę, kurią man suteikei, nes pamilai mane prieš pasaulio sukūrimą.
25Teisingasis Tėve, pasaulis Tavęs nepažino, o Aš Tave pažinau. Ir šitie pažino, kad Tu mane siuntei.
26Aš paskelbiau jiems Tavo vardą ir dar skelbsiu, kad meilė, kuria mane pamilai, būtų juose ir Aš juose”.