1Baigęs kalbėti, Jėzus su savo mokiniais nuėjo anapus Kedrono upelio, kur buvo sodas. Jis ir mokiniai įėjo į sodą.
1ኢየሱስም ይህን ብሎ አትክልት ወዳለበት ስፍራ ወደ ቄድሮን ወንዝ ማዶ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወጣ፤ እርሱም ደቀ መዛሙርቱም በዚያ ገቡ።
2Jo išdavėjas Judas taip pat žinojo tą vietą, nes Jėzus ir Jo mokiniai dažnai ten rinkdavosi.
2ኢየሱስም ደቀ መዛሙርቱም ብዙ ጊዜ ወደዚያ ስለ ተሰበሰቡ አሳልፎ የሰጠው ይሁዳ ደግሞ ስፍራውን ያውቅ ነበር።
3Taigi Judas, gavęs kareivių būrį ir aukštųjų kunigų bei fariziejų tarnų, atėjo ten su žibintais, deglais ir ginklais.
3ስለዚህ ይሁዳ ጭፍሮችንና ከካህናት አለቆች ከፈሪሳውያንም ሎሌዎችን ተቀብሎ በችቦና በፋና በጋሻ ጦርም ወደዚያ መጣ።
4Tuomet Jėzus, žinodamas visa, kas Jo laukia, išėjo į priekį ir paklausė: “Ko ieškote?”
4ኢየሱስም የሚመጣበትን ሁሉ አውቆ ወጣና። ማንን ትፈልጋላችሁ አላቸው።
5Jie atsakė: “Jėzaus iš Nazareto!” Jėzus tarė jiems: “Tai Aš”. Jo išdavėjas Judas irgi stovėjo tarp jų.
5የናዝሬቱን ኢየሱስን ብለው መለሱለት። ኢየሱስ። እኔ ነኝ አላቸው። አሳልፎ የሰጠውም ይሁዳ ደግሞ ከእነርሱ ጋር ቆሞ ነበር።
6Kai Jėzus ištarė: “Tai Aš”, jie atšoko atgal ir parpuolė ant žemės.
6እንግዲህ። እኔ ነኝ ባላቸው ጊዜ ወደ ኋላ አፈግፍገው በምድር ወደቁ።
7O Jis vėl juos klausė: “Ko ieškote?” Jie atsakė: “Jėzaus iš Nazareto”.
7ደግሞም። ማንን ትፈልጋላችሁ? ብሎ ጠየቃቸው። እነርሱም። የናዝሬቱን ኢየሱስን አሉት።
8Jėzus atsiliepė: “Jau jums sakiau, kad tai Aš. Jei tad manęs ieškote, leiskite šitiem pasišalinti”,
8ኢየሱስ መልሶ። እኔ ነኝ አልኋችሁ፤ እንግዲህ እኔን ትፈልጉ እንደ ሆናችሁ እነዚህ ይሂዱ ተዉአቸው አለ፤
9kad išsipildytų Jo pasakyti žodžiai: “Iš tų, kuriuos man davei, nepražudžiau nė vieno”.
9ይህም። ከእነዚህ ከሰጠኸኝ አንዱን ስንኳ አላጠፋሁም ያለው ቃል ይፈጸም ዘንድ ነው።
10Tuomet Simonas Petras, kuris turėjo kalaviją, išsitraukė jį, smogė vyriausiojo kunigo tarnui ir nukirto jam dešinę ausį. Tarnas buvo vardu Malkus.
10ስምዖን ጴጥሮስም ሰይፍ ስለ ነበረው መዘዘው፥ የሊቀ ካህናቱንም ባርያ መትቶ ቀኝ ጆሮውን ቈረጠ፤ የባርያውም ስም ማልኮስ ነበረ።
11Jėzus pasakė Petrui: “Kišk kalaviją į makštį! Nejaugi Aš negersiu tos taurės, kurią Tėvas man davė?”
11ኢየሱስም ጴጥሮስን። ሰይፍህን ወደ ሰገባው ክተተው፤ አብ የሰጠኝን ጽዋ አልጠጣትምን? አለው።
12Būrys, jo vadas ir žydų tarnai suėmė Jėzų, surišo
12እንግዲህ የሻለቃውና ጭፍሮቹ የአይሁድም ሎሌዎች ኢየሱስን ይዘው አሰሩት፥
13ir nuvedė pirmiausia pas Aną. Mat jis buvo tų metų vyriausiojo kunigo Kajafo uošvis.
13አስቀድመውም ወደ ሐና ወሰዱት፤ በዚያች ዓመት ሊቀ ካህናት ለነበረው ለቀያፋ አማቱ ነበርና።
14Tai tas pats Kajafas, kuris buvo žydams pataręs: “Geriau, kad vienas žmogus mirtų už tautą”.
14ቀያፋም። አንድ ሰው ስለ ሕዝብ ይሞት ዘንድ ይሻላል ብሎ ለአይሁድ የመከራቸው ነበረ።
15Paskui Jėzų nusekė Simonas Petras ir kitas mokinys. Tas mokinys buvo pažįstamas su vyriausiuoju kunigu ir įėjo su Jėzumi į vyriausiojo kunigo kiemą.
15ስምዖን ጴጥሮስም ሌላውም ደቀ መዝሙር ኢየሱስን ተከተሉ። ያም ደቀ መዝሙር በሊቀ ካህናቱ ዘንድ የታወቀ ነበረ፥ ወደ ሊቀ ካህናቱም ግቢ ከኢየሱስ ጋር ገባ፤
16O Petras liko stovėti lauke prie vartų. Tada anas mokinys, kuris buvo pažįstamas su vyriausiuoju kunigu, išėjo laukan, pasikalbėjo su durininke ir įsivedė Petrą vidun.
16ጴጥሮስ ግን በውጭ በበሩ ቆሞ ነበር። እንግዲህ በሊቀ ካህናቱ ዘንድ የታወቀው ሌላው ደቀ መዝሙር ወጣ ለበረኛይቱም ነግሮ ጴጥሮስን አስገባው።
17Tarnaitė durininkė tarė Petrui: “Ar tik ir tu nebūsi vienas iš to žmogaus mokinių?” Šis atsakė: “Ne!”
17በረኛ የነበረችይቱም ገረድ ጴጥሮስን። አንተ ደግሞ ከዚህ ሰው ደቀ መዛሙርት አንዱ አይደለህምን? አለችው። እርሱ። አይደለሁም አለ።
18Ten stoviniavo samdiniai ir tarnai, dėl šalčio susikūrę ugnį, ir šildėsi. Prie jų atsistojo Petras ir taip pat šildėsi.
18ብርድ ነበረና ባሮችና ሎሌዎች የፍም እሳት አንድደው ቆሙ ይሞቁም ነበር፤ ጴጥሮስም ደግሞ ከእነርሱ ጋር ቆሞ ይሞቅ ነበር።
19Vyriausiasis kunigas paklausė Jėzų apie Jo mokinius bei Jo mokymą.
19ሊቀ ካህናቱም ኢየሱስን ስለ ደቀ መዛሙርቱና ስለ ትምህርቱ ጠየቀው።
20Jėzus jam atsakė: “Aš viešai kalbėjau pasauliui. Aš visada mokiau sinagogoje ir šventykloje, kur visuomet susirenka žydai, ir nieko nekalbėjau slapčia.
20ኢየስስም መልሶ። እኔ በግልጥ ለዓለም ተናገርሁ፤ አይሁድ ሁሉ በሚሰበሰቡበት በምኵራብና በመቅደስ እኔ ሁልጊዜ አስተማርሁ፥ በስውርም ምንም አልተናገርሁም።
21Kodėl tad mane klausi? Klausk tų, kurie girdėjo, ką jiems kalbėjau. Jie žino, ką Aš sakiau”.
21ስለምን ትጠይቀኛለህ? ለእነርሱ የተናገርሁትን የሰሙትን ጠይቅ፤ እነሆ፥ እነዚህ እኔ የነገርሁትን ያውቃሉ አለው።
22Jam tai pasakius, vienas iš ten buvusių tarnų smogė Jėzui per veidą, tardamas: “Šitaip atsakai vyriausiajam kunigui?!”
22ይህንም ሲል በዚያ ቆሞ የነበረው ከሎሌዎች አንዱ። ለሊቀ ካህናቱ እንዲህ ትመልሳለህን? ብሎ ኢየሱስን በጥፊ መታው።
23Jėzus jam tarė: “Jei kalbėjau negerai, pasakyk, kas negerai, o jei gerai,kodėl mane muši?”
23ኢየሱስም መልሶ። ክፉ ተናግሬ እንደ ሆንሁ ስለ ክፉ መስክር፤ መልካም ተናግሬ እንደ ሆንሁ ግን ሰለ ምን ትመታኛለህ? አለው።
24Tada Anas pasiuntė Jį surištą pas vyriausiąjį kunigą Kajafą.
24ስለዚህ ሐና እንደ ታሰረ ወደ ሊቀ ካህናቱ ወደ ቀያፋ ሰደደው።
25Simonas Petras tebestovėjo ir šildėsi. Aplinkiniai paklausė jį: “Ar tik nebūsi vienas iš Jo mokinių?” Tas išsigynė: “Ne!”
25ስምዖን ጴጥሮስም ቆሞ እሳት ይሞቅ ነበር። እንግዲህ። አንተ ደግሞ ከደቀ መዛሙርቱ አይደለህምን? አሉት። እርሱም። አይደለሁም ብሎ ካደ።
26Vienas iš vyriausiojo kunigo tarnų, giminaitis to, kuriam Petras nukirto ausį, pasakė: “Argi aš nemačiau tavęs sode kartu su Juo?”
26ጴጥሮስ ጆሮውን የቈረጠው ዘመድ የሆነ ከሊቀ ካህናቱ ባሮች አንዱ። በአትክልቱ ከእርሱ ጋር እኔ አይቼህ አልነበረምን? አለው።
27Petras ir vėl išsigynė, ir tuojau pragydo gaidys.
27ጴጥሮስም እንደ ገና ካደ፥ ወዲያውም ዶሮ ጮኸ።
28Iš Kajafo rūmų jie nuvedė Jėzų į pretorijų. Buvo ankstyvas rytas. Jie patys nėjo į pretorijų, kad nesusiteptų ir galėtų valgyti Paschą.
28ኢየሱስንም ከቀያፋ ወደ ገዡ ግቢ ወሰዱት፤ ማለዳም ነበረ፤ እነርሱም የፋሲካ በግ ይበሉ ዘንድ እንጂ እንዳይረክሱ ወደ ገዡ ግቢ አልገቡም።
29Todėl Pilotas išėjo laukan pas juos ir paklausė: “Kuo kaltinate šitą žmogų?”
29ስለዚህ ጲላጦስ ወደ ውጭ ወደ እነርሱ ወጥቶ። ይህን ሰው ስለ ምን ትከሱታላችሁ አላቸው።
30Jie atsakė: “Jeigu Jis nebūtų piktadarys, nebūtume tau Jo atvedę”.
30እነርሱም መልሰው። ይህስ ክፉ አድራጊ ባይሆን ወደ አንተ አሳልፈን ባልሰጠነውም ነበር አሉት።
31Pilotas jiems tarė: “Pasiimkite Jį ir teiskite pagal savo Įstatymą”. Žydai jam atsakė: “Mums neleista nieko bausti mirtimi”,
31ጲላጦስም። እናንተ ወስዳችሁ እንደ ሕጋችሁ ፍረዱበት አላቸው። አይሁድም። ለእኛስ ማንንም ልንገድል አልተፈቀደልንም አሉት፤
32kad išsipildytų Jėzaus žodžiai, kuriais Jis nurodė, kokia mirtimi Jam reikės mirti.
32ኢየሱስ በምን ዓይነት ሞት ሊሞት እንዳለው ሲያመለክት የተናገረው ቃል ይፈጸም ዘንድ ነው።
33Tada Pilotas vėl įėjo į pretorijų, pasišaukė Jėzų ir paklausė: “Ar Tu esi žydų karalius?”
33ጲላጦስም እንደ ገና ወደ ገዡ ግቢ ገባና ኢየሱስን ጠርቶ። የአይሁድ ንጉሥ አንተ ነህን? አለው።
34Jėzus jam atsakė: “Ar nuo savęs šito klausi, ar kiti apie mane tau pasakė?”
34ኢየሱስም መልሶ። አንተ ይህን የምትለው ከራስህ ነውን ወይስ ሌሎች ስለ እኔ ነገሩህን? አለው።
35Pilotas tarė: “Bene aš žydas?! Tavoji tauta ir aukštieji kunigai man Tave atvedė. Ką padarei?”
35ጲላጦስ መልሶ። እኔ አይሁዳዊ ነኝን? ወገኖችህና የካህናት አለቆች ለእኔ አሳልፈው ሰጡህ፤ ምን አድርገሃል? አለው።
36Jėzus atsakė: “Mano karalystė ne iš šio pasaulio. Jei mano karalystė būtų iš šio pasaulio, mano tarnai kovotų, kad nebūčiau atiduotas žydams. Bet mano karalystė ne iš čia”.
36ኢየሱስም መልሶ። መንግሥቴ ከዚህ ዓለም አይደለችም፤ መንግሥቴስ ከዚህ ዓለም ብትሆን፥ ወደ አይሁድ እንዳልሰጥ ሎሌዎቼ ይዋጉልኝ ነበር፤ አሁን ግን መንግሥቴ ከዚህ አይደለችም አለው።
37Tada Pilotas Jį paklausė: “Vadinasi, Tu esi karalius?” Jėzus atsakė: “Taip yra, kaip sakai: Aš esu karalius. Aš tam gimiau ir atėjau į šį pasaulį, kad liudyčiau tiesą. Kiekvienas, kas laikosi tiesos, klauso mano balso”.
37ጲላጦስም። እንግዲያ ንጉሥ ነህን? አለው። ኢየሱስም መልሶ። እኔ ንጉሥ እንደ ሆንሁ አንተ ትላለህ። እኔ ለእውነት ልመሰክር ስለዚህ ተወልጃለሁ ስለዚህም ወደ ዓለም መጥቻለሁ፤ ከእውነት የሆነ ሁሉ ድምፄን ይሰማል አለው።
38Pilotas Jo paklausė: “O kas yra tiesa?!” Po šių žodžių jis vėl išėjo pas žydus ir tarė jiems: “Aš nerandu Jame jokios kaltės.
38ጲላጦስ። እውነት ምንድር ነው? አለው። ይህንም ብሎ ዳግመኛ ወደ አይሁድ ወጥቶ። እኔስ አንዲት በደል ስንኳ አላገኘሁበትም።
39Yra jūsų paprotys, kad per Paschą aš paleisčiau vieną suimtąjį. Tad ar norite, kad paleisčiau jums žydų karalių?”
39ነገር ግን በፋሲካ አንድ ልፈታላችሁ ልማድ አላችሁ፤ እንግዲህ የአይሁድን ንጉሥ ልፈታላችሁ ትወዳላችሁን? አላቸው።
40Tada jie vėl visi ėmė šaukti: “Ne šitą, bet Barabą!” O Barabas buvo plėšikas.
40ሁሉም ደግመው። በርባንን እንጂ ይህን አይደለም እያሉ ጮኹ። በርባን ግን ወንበዴ ነበረ።