Lithuanian

Amharic: New Testament

John

19

1Tuomet Pilotas ėmė ir nuplakdino Jėzų.
1በዚያን ጊዜም ጲላጦስ ኢየሱስን ይዞ ገረፈው።
2Kareiviai, nupynę vainiką iš erškėčių, uždėjo Jam ant galvos, apsiautė Jį purpurine skraiste
2ወታደሮችም ከእሾህ አክሊል ጐንጕነው በራሱ ላይ አኖሩ ቀይ ልብስም አለበሱት፤
3ir sakė: “Sveikas, žydų karaliau!” Ir daužė Jam per veidą.
3እየቀረቡም። የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን ይሉት ነበር፤
4O Pilotas dar kartą išėjo laukan ir kalbėjo žydams: “Štai išvedu Jį jums, kad žinotumėte, jog nerandu Jame jokios kaltės”.
4በጥፊም ይመቱት ነበር። ጲላጦስም ደግሞ ወደ ውጭ ወጥቶ። እነሆ፥ አንዲት በደል ስንኳ እንዳላገኘሁበት ታውቁ ዘንድ እርሱን ወደ ውጭ አወጣላችኋለሁ አላቸው።
5Jėzus išėjo laukan su erškėčių vainiku ir purpurine skraiste. Pilotas tarė: “Štai žmogus!”
5ኢየሱስም የእሾህ አክሊል ደፍቶ ቀይ ልብስም ለብሶ ወደ ውጭ ወጣ።
6Jį pamatę, aukštieji kunigai ir tarnai pradėjo šaukti: “Nukryžiuok Jį, nukryžiuok!” Pilotas jiems sako: “Jūs imkite Jį ir nukryžiuokite! Aš nerandu Jame jokios kaltės”.
6ጲላጦስም። እነሆ ሰውዬው አላቸው። የካህናት አለቆችና ሎሌዎች ባዩትም ጊዜ። ስቀለው ስቀለው እያሉ ጮኹ። ጲላጦስም። እኔስ አንዲት በደል ስንኳ አላገኘሁበትምና እናንተ ወስዳችሁ ስቀሉት አላቸው።
7Žydai jam atsakė: “Mes turime Įstatymą, ir pagal mūsų Įstatymą Jis turi mirti, nes laikė save Dievo Sūnumi”.
7አይሁድም መልሰው። እኛ ሕግ አለን፥ እንደ ሕጋችንም ሊሞት ይገባዋል፥ ራሱን የእግዚአብሔር ልጅ አድርጎአልና አሉት።
8Išgirdęs tuos žodžius, Pilotas dar labiau nusigando.
8ስለዚህ ጲላጦስ ይህን ነገር በሰማ ጊዜ እግጅ ፈራ፤
9Jis vėl nuėjo į pretorijų ir klausė Jėzų: “Iš kur Tu?” Bet Jėzus jam neatsakė.
9ተመልሶም ወደ ገዡ ግቢ ገባና ኢየሱስን። አንተ ከወዴት ነህ? አለው። ኢየሱስ ግን አንድ እንኳ አልመለሰለትም።
10Tada Pilotas Jam tarė: “Tu nekalbi su manimi? Ar nežinai, kad turiu valdžią Tave nukryžiuoti ir turiu valdžią Tave paleisti?”
10ስለዚህ ጲላጦስ። አትነግረኝምን? ልሰቅልህ ሥልጣን እንዳለኝ ወይም ልፈታህ ሥልጣን እንዳለኝ አታውቅምን? አለው።
11Jėzus atsakė: “Tu neturėtum prieš mane jokios valdžios, jeigu tau nebūtų jos duota iš aukštybių. Todėl tam, kuris mane tau įdavė, didesnė nuodėmė”.
11ኢየሱስም መልሶ። ከላይ ካልተሰጠህ በቀር በእኔ ላይ ምንም ሥልጣን ባልነበረህም፤ ስለዚህ ለአንተ አሳልፎ የሰጠኝ ኃጢአቱ የባሰ ነው አለው።
12Nuo tol Pilotas stengėsi Jį paleisti, bet žydai šaukė: “Jei šitą paleidi, nebesi ciesoriaus draugas. Kiekvienas, kas skelbiasi karaliumi, kalba prieš ciesorių”.
12ከዚህ በኋላ ጲላጦስ ሊፈታው ፈለገ፤ ነገር ግን አይሁድ። ይህንስ ብትፈታው የቄሣር ወዳጅ አይደለህም፤ ራሱን ንጉሥ የሚያደርግ ሁሉ የቄሣር ተቃዋሚ ነው እያሉ ጮኹ።
13Tai išgirdęs, Pilotas išvedė Jėzų laukan ir atsisėdo į teisėjo krasę, kuri stovėjo vietoje, vadinamoje “Akmeninis grindinys”, hebrajiškai Gabata.
13ጲላጦስም ይህን ነገር ሰምቶ ኢየሱስን ወደ ውጭ አወጣው፥ በዕብራይስጥም ገበታ በተባለው ጸፍጸፍ በሚሉት ስፍራ በፍርድ ወንበር ተቀመጠ።
14Buvo diena prieš Paschą, apie šeštą valandą. Jis tarė žydams: “Štai jūsų karalius!”
14ለፋሲካም የማዘጋጀት ቀን ነበረ፤ ስድስት ሰዓትም የሚያህል ነበረ፤ አይሁድንም። እነሆ ንጉሣችሁ አላቸው።
15Bet tie šaukė: “Šalin, šalin! Nukryžiuok Jį!” Pilotas paklausė: “Nejaugi turiu nukryžiuoti jūsų karalių?” Aukštieji kunigai atsakė: “Mes neturime karaliaus, tiktai ciesorių”.
15እነርሱ ግን። አስወግደው፥ አስወግደው፥ ስቀለው እያሉ ጮኹ። ጲላጦስም። ንጉሣችሁን ልስቀለውን? አላቸው። የካህናት አለቆችም። ከቄሣር በቀር ሌላ ንጉሥ የለንም ብለው መለሱለት።
16Tada Pilotas atidavė jiems Jį nukryžiuoti. Jie pasiėmė Jėzų ir išsivedė.
16ስለዚህ በዚያን ጊዜ እንዲሰቀል አሳልፎ ሰጣቸው።
17Nešdamas savo kryžių, Jis ėjo į vadinamąją Kaukolės vietą, hebrajiškai Golgotą.
17ኢየሱስንም ይዘው ወሰዱት፤ መስቀሉንም ተሸክሞ በዕብራይስጥ ጎልጎታ ወደ ተባለው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሉት ወጣ።
18Tenai jie Jį nukryžiavo; kartu su Juo ir kitus du, vienoje ir antroje pusėje, o Jėzų viduryje.
18በዚያም ሰቀሉት፥ ከእርሱም ጋር ሌሎች ሁለት፥ አንዱን በዚህ አንዱን በዚያ ኢየሱስንም በመካከላቸው ሰቀሉ።
19Pilotas parašė užrašą ir prikalė ant kryžiaus. Buvo parašyta: “Jėzus Nazarietis, žydų karalius”.
19ጲላጦስም ደግሞ ጽሕፈት ጽፎ በመስቀሉ ላይ አኖረው፤ ጽሕፈቱም። የአይሁድ ንጉሥ የናዝሬቱ ኢየሱስ የሚል ነበረ።
20Šį užrašą skaitė daugybė žydų, nes vieta, kur Jėzų nukryžiavo, buvo arti miesto, o parašyta buvo hebrajiškai, graikiškai ir lotyniškai.
20ኢየሱስም የተሰቀለበት ስፍራ ለከተማ ቅርብ ነበረና ከአይሁድ ብዙዎች ይህን ጽሕፈት አነበቡት፤ በዕብራይስጥና በሮማይስጥ በግሪክም ተጽፎ ነበር።
21Žydų aukštieji kunigai sakė Pilotui: “Nerašyk: ‘Žydų karalius’, bet: ‘Šitas sakė: Aš esu žydų karalius’ ”.
21ስለዚህ የአይሁድ ካህናት አለቆች ጲላጦስን። እርሱ። የአይሁድ ንጉስ ነኝ እንዳለ እንጂ የአይሁድ ንጉሥ ብለህ አትጻፍ አሉት።
22Pilotas atsakė: “Ką parašiau, parašiau!”
22ጲላጦስም። የጻፍሁትን ጽፌአለሁ ብሎ መለሰ።
23Kareiviai, nukryžiavę Jėzų, pasiėmė Jo drabužius ir pasidalino juos į keturias dalis­kiekvienam kareiviui po dalį; pasiėmė ir tuniką. Ji buvo be siūlės, nuo viršaus iki apačios ištisai megzta.
23ጭፍሮችም ኢየሱስን በሰቀሉት ጊዜ ልብሶቹን ወስደው ለእያንዳንዱ ጭፍራ አንድ ክፍል ሆኖ በአራት ከፋፈሉት፤ እጀጠባቡን ደግሞ ወሰዱ። እጀ ጠባቡም ከላይ ጀምሮ ወጥ ሆኖ የተሠራ ነበረ እንጂ የተሰፋ አልነበረም።
24Todėl jie tarėsi: “Neplėšykime jos, bet meskime burtą, kuriam ji atiteks”,­kad išsipildytų Raštas: “Jie pasidalijo mano drabužius tarp savęs ir dėl mano apdaro metė burtą”. Šitaip kareiviai ir padarė.
24ስለዚህ እርስ በርሳቸው። ለማን እንዲሆን በእርሱ ዕጣ እንጣጣልበት እንጂ አንቅደደው ተባባሉ። ይህም። ልብሴን እርስ በርሳቸው ተከፋፈሉ በእጀ ጠባቤም ዕጣ ተጣጣሉበት የሚለው የመጽሐፍ ቃል ይፈጸም ዘንድ ነው።
25Prie Jėzaus kryžiaus stovėjo Jo motina, Jo motinos sesuo, Marija—Kleopo žmona, ir Marija Magdalietė.
25ጭፍሮችም እንዲህ አደረጉ። ነገር ግን በኢየሱስ መስቀል አጠገብ እናቱ፥ የእናቱም እኅት፥ የቀለዮጳም ሚስት ማርያም፥ መግደላዊትም ማርያም ቆመው ነበር።
26Pamatęs stovinčius savo motiną ir mokinį, kurį mylėjo, Jėzus tarė motinai: “Moterie, štai tavo sūnus!”
26ኢየሱስም እናቱን ይወደው የነበረውንም ደቀ መዝሙር በአጠገቡ ቆሞ ባየ ጊዜ እናቱን። አንቺ ሴት፥ እነሆ ልጅሽ አላት።
27Paskui tarė mokiniui: “Štai tavo motina!” Ir nuo tos valandos mokinys pasiėmė ją pas save.
27ከዚህ በኋላ ደቀ መዝሙሩን። እናትህ እነኋት አለው። ከዚህም ሰዓት ጀምሮ ደቀ መዝሙሩ ወደ ቤቱ ወሰዳት።
28Tada, žinodamas, jog viskas įvykdyta,­kad išsipildytų Raštas, Jėzus tarė: “Trokštu!”
28ከዚህ በኋላ ኢየሱስ አሁን ሁሉ እንደተፈጸመ አውቆ የመጽሐፉ ቃል ይፈጸም ዘንድ። ተጠማሁ አለ።
29Tenai stovėjo indas, pilnas rūgštaus vyno. Jie pakėlė ant yzopo šakelės kempinę, pamirkytą vyne, ir prinešė prie Jo lūpų.
29በዚያም ሆምጣጤ የሞላበት ዕቃ ተቀምጦ ነበር፤ እነርሱም ሆምጣጤውን በሰፍነግ ሞልተው በሁሶፕም አድርገው ወደ አፉ አቀረቡለት።
30Paragavęs to vyno, Jėzus tarė: “Atlikta!” Ir, nuleidęs galvą, Jis atidavė dvasią.
30ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ። ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ።
31Kad kūnai neliktų ant kryžiaus per sabatą,­nes tas sabatas buvo didi diena,­žydai Prisirengimo dieną prašė Pilotą, kad nukryžiuotiesiems būtų sulaužyti blauzdikauliai ir kūnai nuimti.
31አይሁድም የማዘጋጀት ቀን ስለ ሆነ ያ ሰንበት ትልቅ ነበረና ሥጋቸው በሰንበት በመስቀል ላይ እንዳይኖር፥ ጭናቸውን ሰብረው እንዲያወርዱአቸው ጲላጦስን ለመኑት።
32Tad atėjo kareiviai ir sulaužė blauzdas vienam ir antram, kurie buvo su Juo nukryžiuoti.
32ጭፍሮችም መጥተው የፊተኛውን ጭን ከእርሱም ጋር የተሰቀለውን የሌላውን ጭን ሰበሩ፤
33Priėję prie Jėzaus ir pamatę, kad Jis jau miręs, jie nebelaužė Jam blauzdų,
33ወደ ኢየሱስ በመጡ ጊዜ ግን እርሱ ፈጽሞ እንደ ሞተ አይተው ጭኑን አልሰበሩም፤
34tik vienas kareivis ietimi perdūrė Jam šoną, ir tuojau ištekėjo kraujo ir vandens.
34ነገር ግን ከጭፍሮች አንዱ ጎኑን በጦር ወጋው፤ ወዲያውም ደምና ውኃ ወጣ።
35Tai matęs paliudijo, ir jo liudijimas teisingas; jis žino sakąs tiesą, kad jūs tikėtumėte.
35ያየውም መስክሮአል፤ ምስክሩም እውነት ነው፤ እናንተም ደግሞ ታምኑ ዘንድ እርሱ እውነት እንዲናገር ያውቃል።
36Taip įvyko, kad išsipildytų Raštas: “Nė vienas Jo kaulas nebus sulaužytas”.
36ይህ የሆነ። ከእርሱ አጥንት አይሰበርም የሚል የመጽሐፉ ቃል እንዲፈጸም ነው።
37Ir vėl kitoje vietoje Raštas sako: “Jie žiūrės į Tą, kurį perdūrė”.
37ደግሞም ሌላው መጽሐፍ። የወጉትን ያዩታል ይላል።
38Po to Juozapas iš Arimatėjos, kuris buvo Jėzaus mokinys, tik slaptas dėl žydų baimės, paprašė Pilotą leisti nuimti Jėzaus kūną. Pilotas leido. Jis atėjo ir nuėmė Jėzaus kūną.
38ከዚህም በኋላ አይሁድን ስለ ፈራ በስውር የኢየሱስ ደቀ መዝሙር የነበረ የአርማትያስ ዮሴፍ የኢየሱስን ሥጋ ሊወስድ ጲላጦስን ለመነ፤ ጲላጦስም ፈቀደለት። ስለዚህም መጥቶ የኢየሱስን ሥጋ ወሰደ።
39Taip pat atvyko ir Nikodemas, kuris anksčiau buvo atėjęs pas Jėzų nakčia. Jis atsivežė apie šimtą svarų miros ir alavijo mišinio.
39ደግሞም አስቀድሞ በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ መቶ ንጥር የሚያህል የከርቤና የእሬት ቅልቅል ይዞ መጣ።
40Taigi jie paėmė Jėzaus kūną ir suvyniojo į drobules su kvepalais, kaip reikalavo žydų laidojimo paprotys.
40የኢየሱስንም ሥጋ ወስደው እንደ አይሁድ አገናነዝ ልማድ ከሽቱ ጋር በተልባ እግር ልብስ ከፈኑት።
41Toje vietoje, kur Jį nukryžiavo, buvo sodas ir sode naujas kapas, kuriame dar niekas nebuvo laidotas.
41በተሰቀለበትም ስፍራ አትክልት ነበረ፥ በአትክልቱም ማንም ገና ያልተቀበረበት አዲስ መቃብር ነበረ።
42Ten jie ir paguldė Jėzų, nes buvo žydų Prisirengimo diena, o kapas arti.
42ስለዚህ መቃብሩ ቅርብ ነበረና ስለ አይሁድ ማዘጋጀት ቀን ኢየሱስን በዚያ አኖሩት።