1Pirmąją savaitės dieną, labai anksti, dar neišaušus, Marija Magdalietė atėjo prie kapo ir pamatė, kad akmuo nuo kapo nuristas.
1ከሳምንቱም በፊተኛው ቀን መግደላዊት ማርያም ገና ጨለማ ሳለ ማለዳ ወደ መቃብር መጣች ድንጋዩም ከመቃብሩ ተፈንቅሎ አየች።
2Ji nubėgo pas Simoną Petrą ir kitą mokinį, kurį Jėzus mylėjo, ir pranešė jiems: “Paėmė Viešpatį iš kapo, ir nežinome, kur Jį padėjo”.
2እየሮጠችም ወደ ስምዖን ጴጥሮስና ኢየሱስ ይወደው ወደ ነበረው ወደ ሌላው ደቀ መዝሙር መጥታ። ጌታን ከመቃብር ወስደውታል ወዴትም እንዳኖሩት አናውቅም አለቻቸው።
3Petras ir tas kitas mokinys nuskubėjo prie kapo.
3ስለዚህ ጴጥሮስና ሌላው ደቀ መዝሙር ወጥተው ወደ መቃብሩ ሄዱ።
4Bėgo abu kartu, bet tasai kitas mokinys pralenkė Petrą ir pirmas pasiekė kapą.
4ሁለቱም አብረው ሮጡ፤ ሌላው ደቀ መዝሙርም ከጴጥሮስ ይልቅ ፈጥኖ ወደ ፊት ሮጠና አስቀድሞ ከመቃብሩ ደረሰ፤
5Pasilenkęs jis pamatė numestas drobules, tačiau į vidų nėjo.
5ዝቅም ብሎ ቢመለከት የተልባ እግሩን ልብስ ተቀምጦ አየ፥ ነገር ግን አልገባም።
6Netrukus iš paskos atbėgo ir Simonas Petras. Jis įėjo į rūsį ir pamatė numestas drobules
6ስምዖን ጴጥሮስም ተከትሎት መጣ ወደ መቃብሩም ገባ፤ የተልባ እግሩን ልብስ ተቀምጦ አየ፥
7ir skarą, buvusią ant Jėzaus galvos, ne su drobulėmis paliktą, bet suvyniotą ir atskirai padėtą.
7ደግሞም በራሱ የነበረውን ጨርቅ ለብቻው በአንድ ስፍራ ተጠምጥሞ እንደ ነበረ እንጂ ከተልባ እግሩ ልብስ ጋር ተቀምጦ እንዳልነበረ አየ።
8Tada įėjo ir kitas mokinys, kuris pirmas buvo atbėgęs prie kapo. Jis pamatė ir įtikėjo.
8በዚያን ጊዜ አስቀድሞ ወደ መቃብር የመጣውም ሌላው ደቀ መዝሙር ደግሞ ገባ፥ አየም፥ አመነም፤
9Mat jie dar nebuvo supratę Rašto, kad Jis turėsiąs prisikelti iš numirusių.
9ከሙታን ይነሣ ዘንድ እንዲገባው የሚለውን የመጽሐፉን ቃል ገና አላወቁም ነበርና።
10Paskui mokiniai vėl sugrįžo namo.
10ደቀ መዛሙርቱም ወደ ቤታቸው ደግሞ ሄዱ።
11O Marija stovėjo lauke prie kapo ir verkė. Verkdama ji pasilenkė, pažvelgė į kapo vidų
11ማርያም ግን እያለቀሰች ከመቃብሩ በስተ ውጭ ቆማ ነበር። ስታለቅስም ወደ መቃብር ዝቅ ብላ ተመለከተች፤
12ir pamatė du angelus baltais drabužiais sėdinčiusvieną galvūgalyje, kitą kojų vietojeten, kur būta Jėzaus kūno.
12ሁለት መላእክትም ነጭ ልብስ ለብሰው የኢየሱስ ሥጋ ተኝቶበት በነበረው አንዱ በራስጌ ሌላውም በእግርጌ ተቀምጠው አየች።
13Jie paklausė ją: “Moterie, ko verki?” Ji atsakė: “Paėmė mano Viešpatį ir nežinau, kur Jį padėjo”.
13እነርሱም። አንቺ ሴት፥ ስለ ምን ታለቅሻለሽ? አሉአት። እርስዋም። ጌታዬን ወስደውታል ወዴትም እንዳኖሩት አላውቅም አለቻቸው።
14Tai tarusi, ji atsisuko ir pamatė stovintį Jėzų, bet nepažino, kad tai Jėzus.
14ይህንም ብላ ወደ ኋላ ዘወር ስትል ኢየሱስን ቆሞ አየችው፤ ኢየሱስም እንደ ሆነ አላወቀችም።
15Jėzus jai tarė: “Moterie, ko verki? Ko ieškai?” Ji, manydama, jog tai sodininkas, atsakė: “Gerbiamasis, jei tamsta Jį išnešei, pasakyk man, kur Jį padėjai. Aš Jį pasiimsiu”.
15ኢየሱስም። አንቺ ሴት፥ ስለ ምን ታለቅሻለሽ? ማንንስ ትፈልጊያለሽ? አላት። እርስዋም የአትክልት ጠባቂ መስሎአት። ጌታ ሆይ፥ አንተ ወስደኸው እንደ ሆንህ ወዴት እንዳኖርኸው ንገረኝ እኔም እወስደዋለሁ አለችው።
16Jėzus jai sako: “Marija!” Ji atsigręžė ir sušuko: “Rabuni!” (Tai reiškia: “Mokytojau”).
16ኢየሱስም። ማርያም አላት። እርስዋ ዘወር ብላ በዕብራይስጥ። ረቡኒ አለችው፤ ትርጓሜውም። መምህር ሆይ ማለት ነው።
17Jėzus jai tarė: “Neliesk manęs! Aš dar neįžengiau pas savo Tėvą. Eik pas mano brolius ir pasakyk jiems: ‘Aš žengiu pas savo Tėvą ir jūsų Tėvą, pas savo Dievą ir jūsų Dievą’ ”.
17ኢየሱስም። ገና ወደ አባቴ አላረግሁምና አትንኪኝ፤ ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሄደሽ። እኔ ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ ወደ አምላኬና ወደ አምላካችሁ ዓርጋለሁ ብለሽ ንገሪአቸው አላት።
18Marija Magdalietė nuėjo ir pranešė mokiniams, kad mačiusi Viešpatį ir ką Jis jai sakęs.
18መግደላዊት ማርያም መጥታ ጌታን እንዳየች ይህንም እንዳላት ለደቀ መዛሙርቱ ነገረች።
19Tos pirmosios savaitės dienos vakare, durims, kur buvo susirinkę mokiniai, dėl žydų baimės esant užrakintoms, atėjo Jėzus, atsistojo viduryje ir tarė: “Ramybė jums!”
19ያም ቀን እርሱም ከሳምንቱ ፊተኛው በመሸ ጊዜ፥ ደቀ መዛሙርቱ ተሰብስበው በነበሩበት፥ አይሁድን ስለ ፈሩ ደጆቹ ተዘግተው ሳሉ፥ ኢየሱስ መጣ፤ በመካከላቸውም ቆሞ። ሰላም ለእናንተ ይሁን አላቸው።
20Tai pasakęs, Jis parodė jiems rankas ir šoną. Mokiniai nudžiugo, išvydę Viešpatį.
20ይህንም ብሎ እጆቹንም ጎኑንም አሳያቸው። ደቀ መዛሙርቱም ጌታን ባዩ ጊዜ ደስ አላቸው።
21Jėzus vėl tarė: “Ramybė jums! Kaip mane siuntė Tėvas, taip ir Aš jus siunčiu”.
21ኢየሱስም ዳግመኛ። ሰላም ለእናንተ ይሁን፤ አብ እንደ ላከኝ እኔ ደግሞ እልካችኋለሁ አላቸው።
22Tai pasakęs, Jis kvėpė į juos ir tarė: “Priimkite Šventąją Dvasią.
22ይህንም ብሎ እፍ አለባቸውና። መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ።
23Kam atleisite nuodėmes, tiems jos bus atleistos, o kam sulaikysite,sulaikytos”.
23ኃጢአታቸውን ይቅር ያላችኋቸው ሁሉ ይቀርላቸዋል፤ የያዛችሁባቸው ተይዞባቸዋል አላቸው።
24Vieno iš dvylikosTomo, vadinamo Dvyniu,nebuvo su jais, kai Jėzus atėjo.
24ነገር ግን ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ዲዲሞስ የሚሉት ቶማስ ኢየሱስ በመጣ ጊዜ ከእነርሱ ጋር አልነበረም።
25Tad kiti mokiniai jam kalbėjo: “Mes matėme Viešpatį!” O jis atsakė: “Jeigu aš nepamatysiu Jo rankose vinių dūrio ir neįleisiu piršto į vinių vietą, ir jeigu ranka nepaliesiu Jo šononetikėsiu”.
25ሌሎቹም ደቀ መዛሙርቱ። ጌታን አይተነዋል አሉት። እርሱ ግን። የችንካሩን ምልክት በእጆቹ ካላየሁ ጣቴንም በችንካሩ ምልክት ካላገባሁ እጄንም በጎኑ ካላገባሁ አላምንም አላቸው።
26Po aštuonių dienų Jo mokiniai vėl buvo kambaryje, ir Tomas su jais. Jėzus atėjo, durims esant užrakintoms, atsistojo viduryje ir prabilo: “Ramybė jums!”
26ከስምንት ቀን በኋላም ደቀ መዛሙርቱ ደግመው በውስጥ ነበሩ፥ ቶማስም ከእነርሱ ጋር ነበረ። ደጆች ተዘግተው ሳሉ ኢየሱስ መጣ፤ በመካከላቸውም ቆሞ። ሰላም ለእናንተ ይሁን አላቸው።
27Paskui kreipėsi į Tomą: “Įleisk čia pirštą ir pažiūrėk į mano rankas. Pakelk ranką ir paliesk mano šoną; nebūk netikintisbūk tikintis”.
27ከዚያም በኋላ ቶማስን። ጣትህን ወደዚህ አምጣና እጆቼን እይ፤ እጅህንም አምጣና በጎኔ አግባው፤ ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን አለው።
28Tomas atsakė Jam: “Mano Viešpats ir mano Dievas!”
28ቶማስም። ጌታዬ አምላኬም ብሎ መለሰለት።
29Jėzus jam tarė: “Tomai, tu įtikėjai, nes mane pamatei. Palaiminti, kurie tiki nematę!”
29ኢየሱስም። ስለ አየኸኝ አምነሃል፤ ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው አለው።
30Savo mokinių akivaizdoje Jėzus padarė ir daug kitų ženklų, kurie nesurašyti šitoje knygoje.
30ኢየሱስም በዚህ መጽሐፍ ያልተጻፈ ሌላ ብዙ ምልክት በደቀ መዛሙርቱ ፊት አደረገ፤
31O šitie yra surašyti, kad tikėtumėte, jog Jėzus yra Kristus, Dievo Sūnus, ir kad tikėdami turėtumėte gyvenimą per Jo vardą.
31ነገር ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፎአል።