1Paskui Jėzus vėl pasirodė mokiniams prie Tiberiados ežero. Pasirodė taip.
1ከዚህ በኋላ ኢየሱስ በጥብርያዶስ ባሕር አጠገብ ለደቀ መዛሙርቱ እንደ ገና ተገለጠላቸው፤
2Buvo drauge Simonas Petras, Tomas, vadinamas Dvyniu, Natanaelis iš Galilėjos Kanos, Zebediejaus sūnūs ir dar du kiti Jėzaus mokiniai.
2እንዲህም ተገለጠ። ስምዖን ጴጥሮስና ዲዲሞስ የሚባለው ቶማስ ከገሊላ ቃና የሆነ ናትናኤልም የዘብዴዎስም ልጆች ከደቀ መዛሙርቱም ሌሎች ሁለት በአንድነት ነበሩ።
3Simonas Petras jiems sako: “Einu žvejoti”. Jie pasisiūlė: “Ir mes einame su tavimi”. Nuėję jie tuojau sulipo į valtį, tačiau tą naktį nieko nesugavo.
3ስምዖን ጴጥሮስ። ዓሣ ላጠምድ እሄዳለሁ አላቸው። እነርሱም። እኛም ከአንተ ጋር እንመጣለን አሉት። ወጥተውም ወደ ታንኳይቱ ገቡ በዚያችም ሌሊት ምንም እላጠመዱም።
4Rytui auštant, ant kranto pasirodė bestovįs Jėzus. Bet mokiniai nepažino, kad tai buvo Jėzus.
4በነጋም ጊዜ ኢየሱስ በባሕር ዳር ቆመ፤ ደቀ መዛሙርቱ ግን ኢየሱስ መሆኑን አላወቁም።
5O Jėzus jiems tarė: “Vaikeliai, ar neturite ko valgyti?” Jie atsakė: “Ne”.
5ኢየሱስም። ልጆች ሆይ፥ አንዳች የሚበላ አላችሁን? አላቸው። የለንም ብለው መለሱለት።
6Tada Jis pasakė: “Užmeskite tinklą į dešinę nuo valties, ir pagausite”. Jie užmetė ir nebeįstengė jo patraukti dėl žuvų gausybės.
6እርሱም። መረቡን በታንኳይቱ በስተ ቀኝ ጣሉት ታገኙማላችሁ አላቸው። ስለዚህ ጣሉት፤ በዚህም ጊዜ ከዓሣው ብዛት የተነሣ ሊጐትቱት አቃታቸው።
7Tuomet tasai mokinys, kurį Jėzus mylėjo, sako Petrui: “Tai Viešpats!” Išgirdęs, jog tai Viešpats, Simonas Petras persijuosė drabužį,mat buvo neapsirengęs,ir šoko į ežerą.
7ኢየሱስ ይወደው የነበረውም ደቀ መዝሙር ጴጥሮስን። ጌታ እኮ ነው አለው። ስለዚህ ስምዖን ጴጥሮስ ጌታ መሆኑን በሰማ ጊዜ ዕራቁቱን ነበረና ልብሱን ታጥቆ ወደ ባሕር ራሱን ጣለ።
8Kiti mokiniai atsiyrė valtimi, nes buvo netoli krantomaždaug už dviejų šimtų mastųir atitempė tinklą su žuvimis.
8ሌሎቹ ደቀ መዛሙርት ግን ከምድር ሁለት መቶ ክንድ ያህል እንጂ እጅግ አልራቁም ነበርና ዓሣ የሞላውን መረብ እየሳቡ በጀልባ መጡ።
9Išlipę į krantą, jie pamatė žėrinčias žarijas, ant jų padėtą žuvį ir duonos.
9ወደ ምድርም በወጡ ጊዜ ፍምና ዓሣ በላዩ ተቀምጦ እንጀራም አዩ።
10Jėzus jiems tarė: “Atneškite ką tik pagautų žuvų”.
10ኢየሱስም። አሁን ካጠመዳችሁት ዓሣ አምጡ አላቸው።
11Simonas Petras nuėjo ir išvilko į krantą tinklą, pilną didelių žuvų, iš viso šimtą penkiasdešimt tris. Nors jų buvo tokia gausybė, tačiau tinklas nesuplyšo.
11ስምዖን ጴጥሮስም ወደ ጀልባይቱ ገብቶ መቶ አምሳ ሦስት ታላላቅ ዓሦች ሞልቶ የነበረውን መረብ ወደ ምድር ጐተተ፤ ይህንም ያህል ብዙ ሲሆን መረቡ አልተቀደደም።
12Jėzus tarė: “Eikite šen pusryčių!” Ir nė vienas iš mokinių neišdrįso paklausti: “Kas Tu esi?”, nes jie žinojo, jog tai Viešpats.
12ኢየሱስም። ኑ፥ ምሳ ብሉ አላቸው። ከደቀ መዛሙርቱ አንድ ስንኳ። አንተ ማን ነህ? ብሎ ሊመረምረው የደፈረ አልነበረም፤ ጌታ መሆኑን አውቀው ነበርና።
13Jėzus priėjo, paėmė duonos ir davė jiems, taip pat ir žuvies.
13ኢየሱስም መጣና እንጀራ አንሥቶ ሰጣቸው፥ እንዲሁም ዓሣውን።
14Tai jau trečią kartą pasirodė savo mokiniams Jėzus, prisikėlęs iš numirusių.
14ኢየሱስ ከሙታን ከተነሣ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ ሲገለጥላቸው ይህ ሦስተኛው ጊዜ ነበረ።
15Papusryčiavus Jėzus paklausė Simoną Petrą: “Simonai, Jonos sūnau, ar myli mane labiau už šituos?” Jis atsakė: “Taip, Viešpatie, Tu žinai, kad Tave myliu”. Jėzus jam tarė: “Ganyk mano avinėlius”.
15ምሳ ከበሉ በኋላም ኢየሱስ ስምዖን ጴጥሮስን። የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ከእነዚህ ይልቅ ትወደኛለህን? አለው። አዎን ጌታ ሆይ፥ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው። ግልገሎቼን አሰማራ አለው።
16Ir antrą kartą Jėzus paklausė: “Simonai, Jonos sūnau, ar myli mane?” Tas atsiliepė: “Taip, Viešpatie, Tu žinai, kad Tave myliu”. Jėzus jam pasakė: “Ganyk mano avis”.
16ደግሞ ሁለተኛ። የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ትወደኛለህን? አለው። አዎን ጌታ ሆይ፥ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው።
17Jėzus paklausė trečią kartą: “Simonai, Jonos sūnau, ar myli mane?” Petras nuliūdo, kad Jis trečią kartą klausia: “Ar myli mane?”, ir atsakė: “Viešpatie, Tu viską žinai. Tu žinai, kad Tave myliu”. Jėzus jam tarė: “Ganyk mano avis.
17ጠቦቶቼን ጠብቅ አለው። ሦስተኛ ጊዜ። የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ትወደኛለህን? አለው። ሦስተኛ። ትወደኛለህን? ስላለው ጴጥሮስ አዘነና። ጌታ ሆይ፥ አንተ ሁሉን ታውቃለህ፤ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው። ኢየሱስም። በጎቼን አሰማራ።
18Iš tiesų, iš tiesų sakau tau: kai buvai jaunas, pats susijuosdavai ir vaikščiojai, kur norėjai. O pasenęs tu ištiesi rankas, ir kitas tave perjuos ir ves, kur tu nenori”.
18እውነት እውነት እልሃለሁ፥ አንተ ጐልማሳ ሳለህ ወገብህን በገዛ ራስህ ታጥቀህ ወደምትወደው ትሄድ ነበር፤ ነገር ግን በሸመገልህ ጊዜ እጆችህን ትዘረጋለህ፥ ሌላውም ያስታጥቅሃል ወደማትወደውም ይወስድሃል አለው።
19Jis tai pasakė, nurodydamas, kokia mirtimi Petras pašlovinsiąs Dievą. Tai pasakęs, dar pridūrė: “Sek paskui mane!”
19በምን ዓይነት ሞት እግዚአብሔርን ያከብር ዘንድ እንዳለው ሲያመለክት ይህን አለ። ይህንም ብሎ። ተከተለኝ አለው።
20Petras atsisukęs pamatė iš paskos einantį mokinį, kurį Jėzus mylėjo, kuris vakarienės metu buvo prisiglaudęs prie Jėzaus krūtinės ir klausė: “Viešpatie, kas Tave išduos?”
20ጴጥሮስም ዘወር ብሎ ኢየሱስ ይወደው የነበረውን ደቀ መዝሙር ሲከተለው አየ፤ እርሱም ደግሞ በእራት ጊዜ በደረቱ ተጠግቶ። ጌታ ሆይ፥ አሳልፎ የሚሰጥህ ማን ነው? ያለው ነበረ።
21Pamatęs jį, Petras tarė Jėzui: “Viešpatie, o kas bus šitam?”
21ጴጥሮስም ይህን አይቶ ኢየሱስን። ጌታ ሆይ፥ ይህስ እንዴት ይሆናል? አለው።
22Jėzus atsakė: “Jei Aš noriu, kad jis pasiliktų, kol ateisiu, kas gi tau? Tu sek paskui mane!”
22ኢየሱስም። እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ብወድስ፥ ምን አግዶህ? አንተ ተከተለኝ አለው።
23Todėl pasklido šis žodis tarp brolių, jog tas mokinys nemirsiąs. Bet Jėzus nesakė, kad Jis nemirs, tik: “Jei noriu, kad jis pasiliktų, kol ateisiu, kas gi tau?”
23ስለዚህ። ያ ደቀ መዝሙር አይሞትም የሚለው ይህ ነገር ወደ ወንድሞች ወጣ፤ ነገር ግን ኢየሱስ። እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ብወድስ ምን አግዶህ? አለው እንጂ አይሞትም አላለውም።
24Tai ir yra tas mokinys, kuris liudija apie tuos dalykus ir juos aprašė, ir mes žinome, kad jo liudijimas tikras.
24ስለ እነዚህም የመሰከረ ይህንንም ጽፎ ያለ ይህ ደቀ መዝሙር ነው፥ ምስክሩም እውነት እንደ ሆነ እናውቃለን።
25Yra dar daug kitų dalykų, kuriuos Jėzus padarė. Jeigu juos visus atskirai aprašytume, manau, kad visas pasaulis nesutalpintų knygų, kurios būtų parašytos. Amen.
25ኢየሱስም ያደረገው ብዙ ሌላ ነገር ደግሞ አለ፤ ሁሉ በእያንዳንዱ ቢጻፍ ለተጻፉት መጻሕፍት ዓለም ራሱ ባልበቃቸውም ይመስለኛል።