1Paskui Jėzus nuvyko į kitą pusę Galilėjos, arba Tiberiados, ežero.
1ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ወደ ገሊላ ባሕር ማዶ ተሻገረ፤ እርሱም የጥብርያዶስ ባሕር ነው።
2Jį lydėjo gausi minia, nes žmonės matė stebuklus, kuriuos Jis darė ligoniams.
2በበሽተኞችም ያደረገውን ምልክቶች ስላዩ ብዙ ሕዝብ ተከተሉት።
3Jėzus užkopė į kalną ir ten atsisėdo su savo mokiniais.
3ኢየሱስም ወደ ተራራ ወጣና በዚያ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ተቀመጠ።
4Artėjo žydų šventė Pascha.
4የአይሁድ በዓልም ፋሲካ ቀርቦ ነበር።
5Pakėlęs akis ir pamatęs, kokia didelė minia pas Jį atėjusi, Jėzus paklausė Pilypą: “Kur pirksime duonos jiems pavalgydinti?”
5ኢየሱስም ዓይኖቹን አንሥቶ ብዙ ሕዝብ ወደ እርሱ ሲመጣ አየና ፊልጶስን። እነዚህ እንዲበሉ እንጀራ ከወዴት እንገዛለን? አለው።
6Jis klausė, mėgindamas jį, nes pats žinojo, ką darysiąs.
6ራሱ ሊያደርግ ያለውን ያውቅ ነበርና ሊፈትነው ይህን ተናገረ።
7Pilypas Jam atsakė: “Už du šimtus denarų duonos neužteks, kad kiekvienas gautų bent gabalėlį”.
7ፊልጶስ። እያንዳንዳቸው ትንሽ ትንሽ እንኳ እንዲቀበሉ የሁለት መቶ ዲናር እንጀራ አይበቃቸውም ብሎ መለሰለት።
8Vienas iš mokinių, Simono Petro brolis Andriejus, Jam pasakė:
8ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ የስምዖን ጴጥሮስ ወንድም እንድርያስ።
9“Čia yra vienas berniukas, kuris turi penkis miežinės duonos kepalus ir dvi žuveles. Bet ką tai reiškia tokiai daugybei!”
9አምስት የገብስ እንጀራና ሁለት ዓሣ የያዘ ብላቴና በዚህ አለ፤ ነገር ግን እነዚህን ለሚያህሉ ሰዎች ይህ ምን ይሆናል? አለው።
10Jėzus tarė: “Susodinkite žmones!” Toje vietoje buvo daug žolės. Taigi jie susėdo, iš viso kokie penki tūkstančiai vyrų.
10ኢየሱስም። ሰዎቹን እንዲቀመጡ አድርጉ አለ። በዚያም ስፍራ ብዙ ሣር ነበረበት። ወንዶችም ተቀመጡ ቍጥራቸውም አምስት ሺህ የሚያህል ነበር።
11Tada Jėzus paėmė duoną ir padėkojęs išdalino mokiniams, o mokiniai ten sėdintiems; taip pat ir žuvis, kiek kas norėjo.
11ኢየሱስም እንጀራውን ያዘ፥ አመስግኖም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም ለተቀመጡት ሰዎች ሰጡአቸው እንዲሁም ከዓሣው በፈለጉት መጠን።
12Kai žmonės pasisotino, Jis pasakė savo mokiniams: “Surinkite trupinius, kad niekas nepražūtų”.
12ከጠገቡም በኋላ ደቀ መዛሙርቱን። አንድ ስንኳ እንዳይጠፋ የተረፈውን ቍርስራሽ አከማቹ አላቸው።
13Taigi jie surinko ir iš penkių miežinės duonos kepalų pripylė dvylika pintinių trupinių, kurie buvo atlikę nuo valgiusiųjų.
13ሰለዚህ አከማቹ፥ ከበሉትም ከአምስቱ የገብስ እንጀራ የተረፈውን ቍርስራሽ አሥራ ሁለት መሶብ ሞሉ።
14Pamatę Jėzaus padarytą stebuklą, žmonės sakė: “Jis tikrai yra Tas pranašas, kuris turi ateiti į pasaulį”.
14ከዚህ የተነሣ ሰዎቹ ኢየሱስ ያደረገውን ምልክት ባዩ ጊዜ። ይህ በእውነት ወደ ዓለም የሚመጣው ነቢይ ነው አሉ።
15O Jėzus, supratęs, kad jie ruošiasi pasigriebti Jį ir paskelbti karaliumi, vėl pasitraukė pats vienas į kalną.
15በዚህም ምክንያት ኢየሱስ ያነግሡት ዘንድ ሊመጡና ሊነጥቁት እንዳላቸው አውቆ ደግሞ ወደ ተራራ ብቻውን ፈቀቅ አለ።
16Atėjus vakarui, Jo mokiniai nusileido prie ežero,
16በመሸም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ወደ ባሕር ወረዱ፥
17sulipo į valtį ir išplaukė į kitą pusę ežero, į Kafarnaumą. Jau sutemo, o Jėzus vis dar nebuvo grįžęs pas juos.
17በታንኳም ገብተው በባሕር ማዶ ወደ ቅፍርናሆም ይመጡ ነበር። አሁንም ጨልሞ ነበር፤ ኢየሱስም ገና ወደ እነርሱ አልመጣም ነበር፤
18Ežeras bangavo, nes pūtė smarkus vėjas.
18ብርቱ ነፋስም ስለ ነፈሰ ባሕሩ ተናወጠ።
19Nusiyrę apie dvidešimt penkiastrisdešimt stadijų, jie pamatė Jėzų, einantį ežeru ir besiartinantį prie valties. Jie išsigando.
19ሀያ አምስት ወይም ሠላሳ ምዕራፍ ከቀዘፉ በኋላም፥ ኢየሱስ በባሕር ላይ እየሄደ ወደ ታንኳይቱ ሲቀርብ አይተው ፈሩ።
20O Jis jiems tarė: “Tai Aš, nebijokite!”
20እርሱ ግን። እኔ ነኝ፤ አትፍሩ አላቸው።
21Jie norėjo Jį paimti į valtį, bet valtis netrukus priartėjo prie kranto, į kurį jie yrėsi.
21ስለዚህ በታንኳይቱ ሊቀበሉት ወደዱ፤ ወዲያውም ታንኳይቱ ወደሚሄዱበት ምድር ደረሰች።
22Kitą dieną minia, buvusi anoje pusėje, pamatė, kad ten nebuvo kitos valties, tik ta, į kurią įlipo Jo mokiniai. O Jėzus su jais neįlipo, ir šie išplaukė vieni.
22በነገው በባሕር ማዶ ቆመው የነበሩ ሕዝቡ ከአንዲት ጀልባ በቀር በዚያ ሌላ ጀልባ እንዳልነበረች፥ ደቀ መዛሙርቱም ለብቻቸው እንደ ሄዱ እንጂ ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደ ታንኳይቱ እንዳልገባ አዩ፤
23Iš Tiberiados atplaukė kitų valčių netoli tos vietos, kur žmonės buvo valgę duonos, Viešpačiui padėkojus.
23ዳሩ ግን ሌሎች ጀልባዎች ጌታ የባረከውን እንጀራ ወደ በሉበት ስፍራ አጠገብ ከጥብርያዶስ መጡ።
24Pamatę, kad čia nėra nei Jėzaus, nei Jo mokinių, žmonės lipo į valtis ir plaukė į Kafarnaumą, ieškodami Jėzaus.
24ሕዝቡም ኢየሱስ ወይም ደቀ መዛሙርቱ በዚያ እንዳልነበሩ ባዩ ጊዜ፥ ራሳቸው በጀልባዎቹ ገብተው ኢየሱስን እየፈለጉ ወደ ቅፍርናሆም መጡ።
25Suradę Jį kitoje ežero pusėje, jie klausinėjo: “Rabi, kada čia atvykai?”
25በባሕር ማዶም ሲያገኙት። መምህር ሆይ፥ ወደዚህ መቼ መጣህ? አሉት።
26Jėzus, atsakydamas jiems, tarė: “Iš tiesų, iš tiesų sakau jums: jūs ieškote manęs ne todėl, kad matėte ženklų, bet kad prisivalgėte duonos lig soties.
26ኢየሱስም መልሶ። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ የምትፈልጉኝ እንጀራን ስለ በላችሁና ስለ ጠገባችሁ ነው እንጂ ምልክቶችን ስላያችሁ አይደለም።
27Darbuokitės ne dėl žūvančio maisto, bet dėl išliekančio amžinajam gyvenimui! Jį duos jums Žmogaus Sūnus, nes TėvasDievas Jį savo antspaudu yra pažymėjęs”.
27ለሚጠፋ መብል አትሥሩ፤ ነገር ግን ለዘላለም ሕይወት ለሚኖር መብል የሰው ልጅ ለሚሰጣችሁ ሥሩ፤ እርሱን እግዚአብሔር አብ አትሞታልና።
28Jie paklausė: “Ką mums daryti, kad vykdytume Dievo darbus?”
28እንግዲህ። የእግዚአብሔርን ሥራ እንድንሠራ ምን እናድርግ? አሉት።
29Jėzus atsakė: “Tai yra Dievo darbas: tikėkite Tą, kurį Jis siuntė”.
29ኢየሱስ መልሶ። ይህ የእግዚአብሔር ሥራ እርሱ በላከው እንድታምኑ ነው አላቸው።
30Tada jie klausė: “Kokį padarysi ženklą, kad pamatytume ir Tave įtikėtume? Ką nuveiksi?
30እንግዲህ። እንኪያ አይተን እንድናምንህ አንተ ምን ምልክት ታደርጋለህ? ምንስ ትሠራለህ?
31Mūsų tėvai dykumoje valgė maną, kaip parašyta: ‘Jis davė jiems valgyti duonos iš dangaus’ ”.
31ይበሉ ዘንድ ከሰማይ እንጀራ ሰጣቸው ተብሎ እንደ ተጻፈ አባቶቻችን በምድረ በዳ መና በሉ አሉት።
32Tuomet Jėzus jiems tarė: “Iš tiesų, iš tiesų sakau jums: ne Mozė davė jums duonos iš dangaus, bet mano Tėvas duoda jums iš dangaus tikrosios duonos.
32ኢየሱስም። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ እውነተኛ እንጀራ ከሰማይ የሚሰጣችሁ አባቴ ነው እንጂ ከሰማይ እንጀራ የሰጣችሁ ሙሴ አይደለም፤
33Nes Dievo duona yra Tas, kuris nužengia iš dangaus ir duoda pasauliui gyvybę”.
33የእግዚአብሔር እንጀራ ከሰማይ የሚወርድ ለዓለምም ሕይወትን የሚሰጥ ነውና አላቸው።
34Tada jie tarė Jam: “Viešpatie, duok visuomet mums tos duonos!”
34ስለዚህ። ጌታ ሆይ፥ ይህን እንጀራ ዘወትር ስጠን አሉት።
35Jėzus atsakė: “Aš esu gyvenimo duona! Kas ateina pas mane, niekuomet nebealks, ir kas tiki mane, niekuomet nebetrokš.
35ኢየሱስም እንዲህ አላቸው። የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፤ ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም በእኔ የሚያምንም ሁልጊዜ ከቶ አይጠማም።
36Bet Aš jums sakiau: jūs mane matėte, ir netikite.
36ነገር ግን አይታችሁኝ እንዳላመናችሁ አልኋችሁ።
37Visi, kuriuos man duoda Tėvas, ateis pas mane, ir ateinančio pas mane Aš neišvarysiu lauk,
37አብ የሚሰጠኝ ሁሉ ወደ እኔ ይመጣል፥ ወደ እኔም የሚመጣውን ከቶ ወደ ውጭ አላወጣውም፤
38nes Aš nužengiau iš dangaus vykdyti ne savo valios, bet valios To, kuris mane siuntė.
38ፈቃዴን ለማድረግ አይደለም እንጂ የላከኝን ፈቃድ ለማድረግ ከሰማይ ወርጃለሁና።
39O mane siuntusio Tėvo valia, kad nepražudyčiau nė vieno iš tų, kuriuos Jis man davė, bet kad prikelčiau juos paskutiniąją dieną.
39ከሰጠኝም ሁሉ አንድን ስንኳ እንዳላጠፋ በመጨረሻው ቀን እንዳስነሣው እንጂ የላከኝ የአብ ፈቃድ ይህ ነው።
40Tokia mano Siuntėjo valia, kad kiekvienas, kuris regi Sūnų ir tiki Jį, turėtų amžinąjį gyvenimą; ir Aš jį prikelsiu paskutiniąją dieną”.
40ልጅንም አይቶ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወትን እንዲያገኝ የአባቴ ፈቃድ ይህ ነው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።
41Tada žydai ėmė murmėti prieš Jį dėl to, kad Jis pasakė: “Aš duona, nužengusi iš dangaus”.
41እንግዲህ አይሁድ። ከሰማይ የወረደ እንጀራ እኔ ነኝ ስላለ ስለ እርሱ አንጐራጐሩና።
42Jie sakė: “Argi Jis ne Jėzus, Juozapo sūnus?! Argi nepažįstame Jo tėvo ir motinos? Tad kodėl Jis sako: ‘Aš nužengiau iš dangaus’?”
42አባቱንና እናቱን የምናውቃቸው ይህ የዮሴፍ ልጅ ኢየሱስ አይደለምን? እንግዲህ። ከሰማይ ወርጃለሁ እንዴት ይላል? አሉ።
43Jėzus jiems atsakė: “Nemurmėkite tarpusavyje!
43ኢየሱስ መለሰ አላቸውም። እርስ በርሳችሁ አታንጐራጕሩ።
44Niekas negali ateiti pas mane, jei mane siuntęs Tėvas jo nepatraukia; ir tą Aš prikelsiu paskutiniąją dieną.
44የላከኝ አብ ከሳበው በቀር ወደ እኔ ሊመጣ የሚችል የለም፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።
45Pranašų parašyta: ‘Ir visi bus mokomi Dievo’. Todėl, kas išgirdo iš Tėvo ir pasimokė, ateina pas mane.
45ሁሉም ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ ተብሎ በነቢያት ተጽፎአል፤ እንግዲህ ከአብ የሰማ የተማረም ሁሉ ወደ እኔ ይመጣል።
46Bet tai nereiškia, jog kas nors būtų Tėvą regėjęs; tiktai Tas, kuris iš Dievo yra, Jis matė Tėvą.
46አብን ያየ ማንም የለም፤ ከእግዚአብሔር ከሆነ በቀር፥ እርሱ አብን አይቶአል።
47Iš tiesų, iš tiesų sakau jums: kas tiki mane, tas turi amžinąjį gyvenimą.
47እውነት እውነት እላችኋለሁ በእኔ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው።
48Aš esu gyvenimo duona.
48የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ።
49Jūsų tėvai dykumoje valgė maną ir mirė.
49አባቶቻችሁ በምድረ በዳ መና በሉ ሞቱም፤
50O ši duona yra nužengusi iš dangaus, kad, kas ją valgys, nemirtų.
50ሰው ከእርሱ በልቶ እንዳይሞት ከሰማይ አሁን የወረደ እንጀራ ይህ ነው።
51Aš esu gyvoji duona, nužengusi iš dangaus. Kas valgo šitos duonosgyvens per amžius. Duona, kurią Aš duosiu, yra mano kūnas, kurį Aš atiduosiu už pasaulio gyvybę”.
51ከሰማይ የወረደ ሕያው እንጀራ እኔ ነኝ፤ ሰው ከዚህ እንጀራ ቢበላ ለዘላለም ይኖራል፤ እኔም ስለ ዓለም ሕይወት የምሰጠው እንጀራ ሥጋዬ ነው።
52Tada žydai ėmė tarp savęs ginčytis ir klausinėti: “Kaip Jis gali duoti mums valgyti savo kūną?!”
52እንግዲህ አይሁድ። ይህ ሰው ሥጋውን ልንበላ ይሰጠን ዘንድ እንዴት ይችላል? ብለው እርስ በርሳቸው ተከራከሩ።
53O Jėzus jiems kalbėjo: “Iš tiesų, iš tiesų sakau jums: jei nevalgysite Žmogaus Sūnaus kūno ir negersite Jo kraujo, neturėsite savyje gyvybės!
53ስለዚህ ኢየሱስ እንዲህ አላቸው። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ የሰውን ልጅ ሥጋ ካልበላችሁ ደሙንም ካልጠጣችሁ በራሳችሁ ሕይወት የላችሁም።
54Kas valgo mano kūną ir geria mano kraują, tas turi amžinąjį gyvenimą, ir Aš jį prikelsiu paskutiniąją dieną.
54ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።
55Nes mano kūnas tikrai yra valgis, ir mano kraujas tikrai yra gėrimas.
55ሥጋዬ እውነተኛ መብል ደሜም እውነተኛ መጠጥ ነውና።
56Kas valgo mano kūną ir geria mano kraują, tas pasilieka manyje, ir Aš jame.
56ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ በእኔ ይኖራል እኔም በእርሱ እኖራለሁ።
57Kaip mane siuntė gyvasis Tėvas ir Aš gyvenu per Tėvą, taip ir tas, kuris mane valgo, gyvens per mane.
57ሕያው አብ እንደ ላከኝ እኔም ከአብ የተነሣ ሕያው እንደምሆን፥ እንዲሁ የሚበላኝ ደግሞ ከእኔ የተነሣ ሕያው ይሆናል።
58Štai duona, nužengusi iš dangaus,ne taip, kaip jūsų tėvai valgė maną ir mirė. Kas valgo šią duonągyvens per amžius”.
58ከሰማይ የወረደ እንጀራ ይህ ነው፤ አባቶቻችሁ መና በልተው እንደ ሞቱ አይደለም፤ ይህን እንጀራ የሚበላ ለዘላለም ይኖራል
59Visa tai Jis paskelbė, mokydamas sinagogoje, Kafarnaume.
59በቅፍርናሆም ሲያስተምር ይህን በምኵራብ አለ።
60Tai išgirdę, daugelis Jo mokinių sakė: “Kieti šie žodžiai, kas gali jų klausytis!”
60ከደቀ መዛሙርቱም ብዙዎች በሰሙ ጊዜ። ይህ የሚያስጨንቅ ንግግር ነው፤ ማን ሊሰማው ይችላል? አሉ።
61Jėzus, žinodamas, kad mokiniai dėl to murma, paklausė: “Jus tai piktina?
61ኢየሱስ ግን ደቀ መዛሙርቱ ስለዚህ እንዳንጐራጐሩ በልቡ አውቆ አላቸው። ይህ ያሰናክላችኋልን?
62O kas būtų, jei pamatytumėte Žmogaus Sūnų, pakylantį ten, kur Jis buvo pirmiau?!
62እንግዲህ የሰው ልጅ አስቀድሞ ወደ ነበረበት ሲወጣ ብታዩ እንዴት ይሆናል?
63Dvasia teikia gyvybę, o kūnas nieko neduoda. Žodžiai, kuriuos jums kalbu, yra dvasia ir gyvenimas.
63ሕይወትን የሚሰጥ መንፈስ ነው፤ ሥጋ ምንም አይጠቅምም፤ እኔ የነገርኋችሁ ቃል መንፈስ ነው ሕይወትም ነው።
64Bet kai kurie iš jūsų netiki”. Jėzus iš pat pradžių žinojo, kas netiki ir kas Jį išduos.
64ነገር ግን ከእናንተ የማያምኑ አሉ። ኢየሱስ የማያምኑት እነማን እንደ ሆኑ አሳልፎ የሚሰጠውም ማን እንደ ሆነ ከመጀመሪያ ያውቅ ነበርና።
65Ir Jis sakė: “Štai kodėl Aš jums sakiau: niekas negali ateiti pas mane, jeigu jam nėra duota mano Tėvo”.
65ደግሞ። ስለዚህ አልኋችሁ፥ ከአብ የተሰጠው ካልሆነ ወደ እኔ ሊመጣ የሚችል የለም አለ።
66Nuo to laiko daug Jo mokinių pasitraukė ir daugiau su Juo nebevaikščiojo.
66ከዚህም የተነሣ ከደቀ መዛሙርቱ ብዙዎች ወደ ኋላ ተመለሱ፤ ወደ ፊትም ከእርሱ ጋር አልሄዱም።
67Tada Jėzus paklausė dvylika: “Gal ir jūs norite pasitraukti?”
67ኢየሱስም ለአሥራ ሁለቱ። እናንተ ደግሞ ልትሄዱ ትወዳላችሁን? አለ።
68Simonas Petras atsakė: “Viešpatie, pas ką mes eisime?! Tu turi amžinojo gyvenimo žodžius.
68ስምዖን ጴጥሮስ። ጌታ ሆይ፥ ወደ ማን እንሄዳለን? አንተ የዘላለም ሕይወት ቃል አለህ፤
69Mes įtikėjome ir pažinome, kad Tu esi Kristus, gyvojo Dievo Sūnus”.
69እኛስ አንተ ክርስቶስ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆንህ አምነናል አውቀናልም ብሎ መለሰለት።
70Jėzus jiems atsakė: “Argi Aš neišsirinkau jūsų, dvylikos? Tačiau tarp jūsų vienas yra velnias”.
70ኢየሱስም። እኔ እናንተን አሥራ ሁለታችሁን የመረጥኋችሁ አይደለምን? ከእናንተም አንዱ ዲያብሎስ ነው ብሎ መለሰላቸው።
71Jis kalbėjo apie Judą, Simono Iskarijoto sūnų. Šis, vienas iš dvylikos, turėjo Jį išduoti.
71ስለ ስምዖንም ልጅ ስለ አስቆሮቱ ይሁዳ ተናገረ፤ ከአሥራ ሁለቱ አንዱ የሆነ እርሱ አሳልፎ ይሰጠው ዘንድ አለውና።