1Jėzus nuėjo į Alyvų kalną.
1ኢየሱስ ግን ወደ ደብረ ዘይት ሄደ።
2Anksti rytą Jis vėl atėjo į šventyklą. Visi žmonės rinkosi prie Jo, ir Jis atsisėdęs juos mokė.
2ማለዳም ደግሞ ወደ መቅደስ ደረሰ ሕዝቡም ሁሉ ወደ እርሱ መጡ። ተቀምጦም ያስተምራቸው ነበር።
3Rašto žinovai ir fariziejai atvedė pas Jį moterį, sugautą svetimaujant. Pastatė ją viduryje
3ጻፎችና ፈሪሳውያንም በምንዝር የተያዘችን ሴት ወደ እርሱ አመጡ በመካከልም እርሱዋን አቁመው።
4ir kreipėsi į Jį: “Mokytojau, ši moteris buvo pagauta svetimaujant.
4መምህር ሆይ፥ ይህች ሴት ስታመነዝር ተገኝታ ተያዘች።
5Mozė Įstatyme mums įsakė tokias užmėtyti akmenimis. O ką Tu pasakysi?”
5ሙሴም እንደነዚህ ያሉት እንዲወገሩ በሕግ አዘዘን፤ አንተስ ስለ እርስዋ ምን ትላለህ? አሉት።
6Jie tai sakė, mėgindami Jį, kad turėtų kuo apkaltinti. Bet Jėzus, jų nepaisydamas, pasilenkęs rašė pirštu ant žemės.
6የሚከሱበትንም እንዲያገኙ ሊፈትኑት ይህን አሉ። ኢየሱስ ግን ጐንበስ ብሎ በጣቱ በምድር ላይ ጻፈ፤
7Jiems nesiliaujant klausinėti, Jis atsitiesė ir tarė: “Kas iš jūsų be nuodėmės, tegul pirmas sviedžia į ją akmenį”.
7መላልሰው በጠየቁት ጊዜ ግን ቀና ብሎ። ከእናንተ ኃጢአት የሌለበት አስቀድሞ በድንጋይ ይውገራት አላቸው።
8Ir vėl pasilenkęs rašė ant žemės.
8ደግሞም ጐንበስ ብሎ በጣቱ በምድር ላይ ጻፈ።
9Tai išgirdę, sąžinės apkaltinti jie vienas po kito ėmė trauktis šalin, pradedant nuo vyresniųjų iki paskutiniojo.
9እነርሱም ይህን ሲሰሙ ሕሊናቸው ወቀሳቸውና ከሽማግሌዎች ጀምረው እስከ ኋለኞች አንድ አንድ እያሉ ወጡ፤ ኢየሱስም ብቻውን ቀረ ሴቲቱም በመካከል ቆማ ነበረች።
10Atsitiesęs ir nebematydamas nė vieno, tik moterį, Jėzus paklausė: “Moterie, kur tie tavo kaltintojai? Niekas tavęs nepasmerkė?”
10ኢየሱስም ቀና ብሎ ከሴቲቱ በቀር ማንንም ባላየ ጊዜ። አንቺ ሴት፥ እነዚያ ከሳሾችሽ ወዴት አሉ? የፈረደብሽ የለምን? አላት።
11Ji atsiliepė: “Niekas, Viešpatie”. Jėzus jai tarė: “Nė Aš tavęs nesmerkiu. Eik ir daugiau nebenusidėk”.
11እርስዋም። ጌታ ሆይ፥ አንድ ስንኳ አለች። ኢየሱስም። እኔም አልፈርድብሽም፤ ሂጂ ከአሁንም ጀምሮ ደግመሽ ኃጢአት አትሥሪ አላት።
12Jėzus vėl prabilo: “Ašpasaulio šviesa. Kas seka manimi, nebevaikščios tamsoje, bet turės gyvenimo šviesą”.
12ደግሞም ኢየሱስ። እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም ብሎ ተናገራቸው።
13Tada fariziejai Jam pasakė: “Tu pats apie save liudiji,tavo liudijimas netikras”.
13ፈሪሳውያንም። አንተ ስለ ራስህ ትመሰክራለህ፤ ምስክርነትህ እውነት አይደለም አሉት።
14Jėzus jiems atsakė: “Nors Aš ir liudiju pats apie save, mano liudijimas yra tikras, nes Aš žinau, iš kur atėjau ir kur einu. O jūs nežinote, nei iš kur Aš atėjau, nei kur einu.
14ኢየሱስ መለሰ አላቸውም። እኔ ስለ ራሴ ምንም እንኳ ብመሰክር ከወዴት እንደመጣሁ ወዴትም እንድሄድ አውቃለሁና ምስክርነቴ እውነት ነው፤ እናንተ ግን ከወዴት እንደ መጣሁ ወዴትም እንድሄድ አታውቁም።
15Jūs teisiate pagal kūną, Aš neteisiu nė vieno.
15እናንተ ሥጋዊ ፍርድን ትፈርዳላችሁ፤ እኔ በአንድ ሰው ስንኳ አልፈርድም።
16O jeigu Aš ir teisiumano teismas teisingas, nes Aš ne vienas, bet esu Aš ir mane siuntęs Tėvas.
16የላከኝ አብ ከእኔ ጋር ነው እንጂ ብቻዬን አይደለሁምና እኔ ብፈርድ ፍርዴ እውነት ነው።
17Ir jūsų Įstatyme parašyta, kad dviejų asmenų liudijimas tikras.
17የሁለት ሰዎችም ምስክርነት እውነት እንደ ሆነ በሕጋችሁ ተጽፎአል።
18Aš liudiju pats apie save, ir apie mane liudija mane siuntęs Tėvas”.
18ስለ ራሴ የምመሰክር እኔ ነኝ፥ የላከኝም አብ ስለ እኔ ይመሰክራል።
19Jie paklausė: “Kur yra Tavo Tėvas?” Jėzus atsakė: “Jūs nepažįstate nei manęs, nei mano Tėvo. Jei pažintumėte mane, pažintumėte ir mano Tėvą”.
19እንግዲህ። አባትህ ወዴት ነው? አሉት። ኢየሱስ መልሶ። እኔንም ወይም አባቴንም አታውቁም፤ እኔንስ ብታውቁኝ አባቴን ደግሞ ባወቃችሁ ነበር አላቸው።
20Šiuos žodžius Jėzus pasakė, mokydamas šventyklos iždinėje. Ir niekas Jo nesuėmė, nes dar nebuvo atėjusi Jo valanda.
20ኢየሱስ በመቅደስ ሲያስተምር በግምጃ ቤት አጠገብ ይህን ነገር ተናገረ፤ ጊዜው ገና አልደረሰምና ማንም አልያዘውም።
21Jėzus vėl jiems kalbėjo: “Aš išeinu, ir jūs ieškosite manęs ir mirsite savo nuodėmėse. Kur Aš einu, jūs negalite nueiti”.
21ኢየሱስም ደግሞ። እኔ እሄዳለሁ ትፈልጉኛላችሁም በኃጢአታችሁም ትሞታላችሁ እኔ ወደምሄድበት እናንተ ልትመጡ አትችሉም አላቸው።
22Tada žydai ėmė kalbėti: “Nejaugi Jis nusižudys, kad sako: ‘Kur Aš einu, jūs negalite nueiti’?”
22አይሁድም። እኔ ወደ ምሄድበት እናንተ ልትመጡ አትችሉም ማለቱ ራሱን ይገድላልን? እንጃ አሉ።
23Jis atsakė: “Jūs esate iš pažemių, o Aš esu iš aukštybės. Jūsiš šio pasaulio, o Ašne iš šio pasaulio.
23እናንተ ከታች ናችሁ፥ እኔ ከላይ ነኝ፤ እናንተ ከዚህ ዓለም ናችሁ፥ እኔ ከዚህ ዓለም አይደለሁም።
24Dėl to Aš jums sakiau, kad mirsite savo nuodėmėse. Jeigu netikėsite, kad Aš Esu,mirsite savo nuodėmėse”.
24እንግዲህ። በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁ አልኋችሁ፤ እኔ እንደሆንሁ ባታምኑ በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁና አላቸው።
25Tada jie klausė: “Kas Tu esi?” Jėzus atsakė: “Tas, ką nuo pradžios jums sakiau.
25እንግዲህ። አንተ ማን ነህ? አሉት። ኢየሱስም። ከመጀመሪያ ለእናንተ የተናገርሁት ነኝ።
26Daug turiu ką apie jus kalbėti ir teisti, bet teisingas yra mano Siuntėjas, ir Aš skelbiu pasauliui, ką iš Jo girdėjau”.
26ስለ እናንተ የምናገረው የምፈርደውም ብዙ ነገር አለኝ፤ ዳሩ ግን የላከኝ እውነተኛ ነው እኔም ከእርሱ የሰማሁትን ይህን ለዓለም እናገራለሁ አላቸው።
27Jie nesuprato, kad Jis kalbėjo jiems apie Tėvą.
27ስለ አብ እንደ ነገራቸው አላስተዋሉም።
28O Jėzus tęsė: “Kai Žmogaus Sūnų būsite aukštyn iškėlę, tuomet suprasite, kad Aš Esu ir kad nieko nedarau iš savęs, bet skelbiu tai, ko mane Tėvas išmokė.
28ስለዚህም ኢየሱስ። የሰውን ልጅ ከፍ ከፍ ባደረጋችሁት ጊዜ እኔ እሆን ዘንድ አባቴም እንዳስተማረኝ እነዚህን እናገር ዘንድ እንጂ ከራሴ አንዳች እንዳላደርግ በዚያን ጊዜ ታውቃላችሁ።
29Mano Siuntėjas yra su manimi; Tėvas nepaliko manęs vieno, nes visuomet darau, kas Jam patinka”.
29የላከኝም ከእኔ ጋር ነው፤ እኔ ደስ የሚያሰኘውን ዘወትር አደርጋለሁና አብ ብቻዬን አይተወኝም አላቸው።
30Jam tai kalbant, daugelis įtikėjo Jį.
30ይህን ሲናገር ብዙዎች በእርሱ አመኑ።
31Jėzus kalbėjo įtikėjusiems Jį žydams: “Jei jūs pasiliekate mano žodyje, iš tiesų esate mano mokiniai;
31ኢየሱስም ያመኑትን አይሁድ። እናንተ በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ፤
32ir jūs pažinsite tiesą, ir tiesa padarys jus laisvus”.
32እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል አላቸው።
33Jie Jam atsakė: “Mes esame Abraomo palikuonys ir niekada niekam nevergavome. Kaipgi Tu sakai: ‘Tapsite laisvi’?”
33እነርሱም መልሰው። የአብርሃም ዘር ነን ለአንድም ስንኳ ከቶ ባሪያዎች አልሆንም፤ አንተ። አርነት ትወጣላችሁ እንዴት ትላለህ? አሉት።
34Jėzus jiems tarė: “Iš tiesų, iš tiesų sakau jums: kiekvienas, kas daro nuodėmę, yra nuodėmės vergas.
34ኢየሱስ መለሰ፥ እንዲህ ሲል። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ኃጢአት የሚያደርግ ሁሉ የኃጢአት ባርያ ነው።
35Bet vergas nepasilieka namuose amžinai, o Sūnus pasilieka amžinai.
35ባርያም ለዘላለም በቤት አይኖርም፤ ልጁ ለዘላለም ይኖራል።
36Jei tad Sūnus jus išlaisvins, iš tiesų būsite laisvi.
36እንግዲህ ልጁ አርነት ቢያወጣችሁ በእውነት አርነት ትወጣላችሁ።
37Aš žinau, kad jūs Abraomo palikuonys. Bet jūs norite mane nužudyti, nes mano žodžiui nėra jumyse vietos.
37የአብርሃም ዘር መሆናችሁንስ አውቃለሁ ነገር ግን ቃሌ በእናንተ አይኖርምና ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ።
38Aš kalbu, ką esu matęs pas savo Tėvą. O jūs darote, ką matėte pas savo tėvą”.
38እኔ በአባቴ ዘንድ ያየሁትን እናገራለሁ፤ እናንተም ደግሞ በአባታችሁ ዘንድ ያያችሁትን ታደርጋላችሁ።
39Jie atsiliepė: “Mūsų tėvas Abraomas!” Jėzus jiems tarė: “Jei jūs būtumėte Abraomo vaikai, darytumėte Abraomo darbus.
39መልሰውም። አባታችንስ አብርሃም ነው አሉት። ኢየሱስም። የአብሃም ልጆች ብትሆኑ የአብርሃምን ሥራ ባደረጋችሁ ነበር።
40Bet dabar jūs norite nužudyti manežmogų, kuris kalbėjo jums tiesą, girdėtą iš Dievo. Šitaip Abraomas nedarė!
40ነገር ግን አሁን ከእግዚእብሔር የሰማሁትን እውነት የነገርኋችሁን ሰው ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ፤ አብርሃም እንዲህ አላደረገም።
41Jūs darote savo tėvo darbus”. Jie atsakė: “Mes nesame pavainikiai ir turime vieną TėvąDievą”.
41እናንተ የአባታችሁን ሥራ ታደርጋላችሁ አላቸው። እኛስ ከዝሙት አልተወለድንም አንድ አባት አለን እርሱም እግዚአብሔር ነው አሉት።
42Jėzus kalbėjo jiems toliau: “Jei Dievas būtų jūsų Tėvas, jūs mylėtumėte mane, nes Aš iš Dievo išėjau ir čia atėjau. Aš ne pats nuo savęs atėjau, bet Jis mane siuntė.
42ኢየሱስም አላቸው። እግዚአብሔርስ አባታችሁ ከሆነ በወደዳችሁኝ ነበር፤ እኔ ከእግዚአብሔር ወጥቼ መጥቻለሁና፤ እርሱ ላከኝ እንጂ ከራሴ አልመጣሁምና።
43Kodėl gi nesuprantate, ką jums sakau? Todėl, kad negalite mano žodžių klausyti.
43ንግግሬን የማታስተውሉ ስለ ምንድር ነው? ቃሌን ልትሰሙ ስለማትችሉ ነው።
44Jūsų tėvasvelnias, ir jūs norite vykdyti savo tėvo troškimus. Jis nuo pat pradžios buvo žmogžudys ir nesilaikė tiesos, nes jame nėra tiesos. Kalbėdamas melą, jis kalba, kas jam sava, nes jis melagis ir melo tėvas.
44እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ። እርሱ ከመጀመሪያ ነፍሰ ገዳይ ነበረ፤ እውነትም በእርሱ ስለ ሌለ በእውነት አልቆመም። ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል፥ ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና።
45O kadangi Aš kalbu tiesą, jūs netikite manimi.
45እኔ ግን እውነትን የምናገር ስለ ሆንሁ አታምኑኝም።
46Kas iš jūsų apkaltins mane nuodėme? Jeigu tad tiesą sakau, kodėl netikite manimi?
46ከእናንተ ስለ ኃጢአት የሚወቅሰኝ ማን ነው? እውነት የምናገር ከሆንሁ እናንተ ስለ ምን አታምኑኝም?
47Kas iš Dievo yra, tas Dievo žodžių klauso. Jūs neklausote todėl, kad nesate iš Dievo”.
47ከእግዚአብሔር የሆነ የእግዚአብሔርን ቃል ይሰማል፤ እናንተ ከእግዚአብሔር አይደላችሁምና ስለዚህ አትሰሙም።
48Tuomet žydai atsiliepė: “Argi mes ne teisingai sakome, kad Tu samarietis ir Tavyje demonas?”
48አይሁድ መልሰው። ሳምራዊ እንደ ሆንህ ጋኔንም እንዳለብህ በማለታችን እኛ መልካም እንል የለምን? አሉት።
49Jėzus jiems atsakė: “Nėra manyje demono. Aš gerbiu savo Tėvą, o jūs negerbiate manęs.
49ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል። እኔስ ጋኔን የለብኝም ነገር ግን አባቴን አከብራለሁ እናንተም ታዋርዱኛላችሁ።
50Aš neieškau sau šlovės: yra, kas ieško ir teisia.
50እኔ ግን የራሴን ክብር አልፈልግም፤ የሚፈልግ የሚፈርድም አለ።
51Iš tiesų, iš tiesų sakau jums: kas laikysis mano žodžio, nematys mirties per amžius”.
51እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ቃሌን የሚጠብቅ ቢኖር ለዘላለም ሞትን አያይም።
52Žydai Jam pasakė: “Dabar mes žinome, kad Tu demono apsėstas! Juk mirė Abraomas ir pranašai, o Tu sakai: ‘Kas laikysis mano žodžio, tas neragaus mirties per amžius’.
52አይሁድ። ጋኔን እንዳለብህ አሁን አወቅን። አብርሃም ስንኳ ሞተ ነቢያትም፤ አንተም። ቃሌን የሚጠብቅ ቢኖር ለዘላለም ሞትን አይቀምስም ትላለህ።
53Argi Tu didesnis už mūsų tėvą Abraomą, kuris mirė? Pranašai irgi mirė. Kuo Tu dediesi?”
53በእውኑ አንተ ከሞተው ከአባታችን ከአብርሃም ትበልጣለህን? ነቢያትም ሞቱ፤ ራስህን ማንን ታደርጋለህ? አሉት።
54Jėzus atsakė: “Jei Aš save šlovinčiau, mano šlovė būtų niekai. Mane šlovina mano Tėvas, apie kurį jūs sakote: ‘Jis yra mūsų Dievas’.
54ኢየሱስም መለሰ አለም። እኔ ራሴን ባከብር ክብሬ ከንቱ ነው፤ የሚያከብረኝ እናንተ አምላካችን የምትሉት አባቴ ነው፤
55Ir jūs Jo nepažįstate, o Aš Jį pažįstu. Jei sakyčiau, kad Jo nepažįstu, būčiau toks kaip jūsmelagis. Bet Aš Jį pažįstu ir laikausi Jo žodžio.
55አላወቃችሁትምም፥ እኔ ግን አውቀዋለሁ። አላውቀውም ብል እንደ እናንተ ሐሰተኛ በሆንሁ፤ ዳሩ ግን አውቀዋለሁ ቃሉንም እጠብቃለሁ።
56Jūsų tėvas Abraomas džiūgavo, kad matysiąs manąją dieną; jis ją išvydo ir džiaugėsi”.
56አባታችሁ አብርሃም ቀኔን ያይ ዘንድ ሐሤት አደረገ፥ አየም ደስም አለው።
57Tada žydai Jam sakė: “Dar neturi nė penkiasdešimt metų ir esi matęs Abraomą?!”
57አይሁድም። ገና አምሳ ዓመት ያልሆነህ አብርሃምን አይተሃልን? አሉት።
58Jėzus jiems tarė: “Iš tiesų, iš tiesų sakau jums: pirmiau, negu buvo Abraomas, Aš Esu!”
58ኢየሱስም። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ አብርሃም ሳይወለድ እኔ አለሁ አላቸው።
59Tada jie griebėsi akmenų, norėdami mesti į Jį, bet Jėzus pasislėpė ir, praeidamas pro juos, išėjo iš šventyklos ir nuėjo tolyn.
59ስለዚህ ሊወግሩት ድንጋይ አነሡ፤ ኢየሱስ ግን ተሰወራቸው ከመቅደስም ወጥቶ በመካከላቸው አልፎ ሄደ።