Lithuanian

Amharic: New Testament

John

9

1Eidamas pro šalį, Jėzus pamatė žmogų, aklą gimusį.
1ሲያልፍም ከመወለዱ ጀምሮ ዕውር የሆነውን ሰው አየ።
2Jo mokiniai paklausė: “Rabi, kas nusidėjo,­jis pats ar jo tėvai,­ kad gimė aklas?”
2ደቀ መዛሙርቱም። መምህር ሆይ፥ ይህ ሰው ዕውር ሆኖ እንዲወለድ ኃጢአት የሠራ ማን ነው? እርሱ ወይስ ወላጆቹ? ብለው ጠየቁት።
3Jėzus atsakė: “Nei jis nusidėjo, nei jo tėvai, bet dėl to, kad jame apsireikštų Dievo darbai.
3ኢየሱስም እንዲህ ብሎ መለሰ። የእግዚአብሔር ሥራ በእርሱ እንዲገለጥ ነው እንጂ እርሱ ወይም ወላጆቹ ኃጢአት አልሠሩም።
4Man reikia dirbti darbus To, kuris mane siuntė, kol yra diena. Ateina naktis, kada niekas negalės dirbti.
4ቀን ሳለ የላከኝን ሥራ ላደርግ ይገባኛል፤ ማንም ሊሠራ የማይችልባት ሌሊት ትመጣለች።
5Kol esu pasaulyje, esu pasaulio šviesa!”
5በዓለም ሳለሁ የዓለም ብርሃን ነኝ።
6Tai taręs, Jis spjovė žemėn, padarė purvo iš seilių, patepė juo neregio akis
6ይህን ብሎ ወደ መሬት እንትፍ አለ በምራቁም ጭቃ አድርጎ በጭቃው የዕውሩን ዓይኖች ቀባና።
7ir tarė jam: “Eik ir nusiprausk Siloamo tvenkinyje”. (Išvertus “Siloamas” reiškia: “Pasiųstasis”.) Tas nuėjo, nusiplovė ir sugrįžo regintis.
7ሂድና በሰሊሆም መጠመቂያ ታጠብ አለው፤ ትርጓሜው የተላከ ነው። ስለዚህ ሄዶ ታጠበ እያየም መጣ።
8Kaimynai ir tie, kurie anksčiau matydavo jį aklą, klausė: “Ar čia ne tas, kuris sėdėdavo elgetaudamas?”
8ጐረቤቶቹም ቀድሞም ሲለምን አይተውት የነበሩ። ይህ ተቀምጦ ይለምን የነበረ አይደለምን? አሉ።
9Vieni sakė: “Tai jis”. Kiti: “Ne, tik panašus į jį”. O jis atsakė: “Tai aš”.
9ሌሎች። እርሱ ነው አሉ፤ ሌሎች። አይደለም እርሱን ይመስላል እንጂ አሉ፤ እርሱ። እኔ ነኝ አለ።
10Tada jie klausė jį: “Kaip atsivėrė tau akys?”
10ታድያ። ዓይኖችህ እንዴት ተከፈቱ? አሉት።
11Jis atsakė: “Žmogus, vadinamas Jėzumi, padarė purvo, patepė juo mano akis ir pasakė: ‘Eik į Siloamo tvenkinį ir nusiprausk’. Aš nuėjau, nusiprausiau ir praregėjau”.
11እርሱ መልሶ። ኢየሱስ የሚባለው ሰው ጭቃ አድርጎ አይኖቼን ቀባና። ወደ ሰሊሆም መጠመቂያ ሄደህ ታጠብ አለኝ፤ ሄጄ ታጥቤም አየሁ አለ።
12Tada jie paklausė: “Kur Jis?” Šis atsakė: “Nežinau”.
12ያ ሰው ወዴት ነው? አሉት። አላውቅም አለ።
13Jie nusivedė buvusį neregį pas fariziejus.
13በፊት ዕውር የነበረውን ሰው ወደ ፈሪሳውያን ወሰዱት።
14O toji diena, kai Jėzus padarė purvo ir atvėrė akis, buvo sabatas.
14ኢየሱስም ጭቃ አድርጎ ዓይኖቹን የከፈተበት ቀን ሰንበት ነበረ።
15Fariziejai jį iš naujo paklausė, kaip jis praregėjęs. Tas jiems paaiškino: “Jis uždėjo man ant akių purvo, aš nusiprausiau, ir dabar regiu”.
15ስለዚህ ፈሪሳውያን ደግሞ እንዴት እንዳየ እንደ ገና ጠየቁት። እርሱም። ጭቃ በዓይኖቼ አኖረ ታጠብሁም አያለሁም አላቸው።
16Kai kurie fariziejai kalbėjo: “Tas žmogus ne iš Dievo, nes nesilaiko sabato”. O kiti sakė: “Kaip galėtų nuodėmingas žmogus daryti tokius ženklus?!” Ir jie tarp savęs nesutarė.
16ከፈሪሳውያንም አንዳንዶቹ። ይህ ሰው ሰንበትን አያከብርምና ከእግዚአብሔር አይደለም አሉ። ሌሎች ግን። ኃጢአትኛ ሰው እንደነዚህ ያሉ ምልክቶች ሊያደርግ እንዴት ይችላል? አሉ።
17Tuomet jie vėl paklausė buvusį neregį: “O ką tu pasakysi apie žmogų, atvėrusį tau akis?” Šis atsakė: “Jis pranašas”.
17በመካከላቸውም መለያየት ሆነ። ከዚህም የተነሣ ዕውሩን። አንተ ዓይኖችህን ስለ ከፈተ ስለ እርሱ ምን ትላለህ? ደግሞ አሉት። እርሱም። ነቢይ ነው አለ።
18Bet žydai netikėjo, kad jis buvo aklas ir praregėjo, kol pašaukė praregėjusiojo tėvus
18አይሁድ የዚያን ያየውን ወላጆች እስኪጠሩ ድረስ ዕውር እንደ ነበረ እንዳየም ስለ እርሱ አላመኑም፥
19ir paklausė jų: “Ar šitas jūsų sūnus, kurį sakote gimus aklą? Tai kaip jis dabar regi?”
19እነርሱንም። እናንተ ዕውር ሆኖ ተወለደ የምትሉት ልጃችሁ ይህ ነውን? ታድያ አሁን እንዴት ያያል? ብለው ጠየቁአቸው።
20Jo tėvai jiems atsakė: “Mes žinome, kad jis mūsų sūnus ir kad jis gimė aklas.
20ወላጆቹም መልሰው። ይህ ልጃችን እንደ ሆነ ዕውርም ሆኖ እንደ ተወለደ አናውቃለን፤
21O kaip jis praregėjo, mes nežinome, nei kas jam atvėrė akis, nežinome. Klauskite jį patį, jis suaugęs ir pats tegul kalba už save”.
21ዳሩ ግን አሁን እንዴት እንዳየ አናውቅም፥ ወይም ዓይኖቹን ማን እንደ ከፈተ እኛ አናውቅም፤ ጠይቁት እርሱ ሙሉ ሰው ነው፤ እርሱ ስለ ራሱ ይናገራል አሉ።
22Jo tėvai taip kalbėjo, bijodami žydų. Nes žydai jau buvo nutarę: jei kas tik išpažintų Jėzų esant Kristų, turėtų būti pašalintas iš sinagogos.
22ወላጆቹ አይሁድን ስለ ፈሩ ይህን አሉ፤ እርሱ ክርስቶስ ነው ብሎ የሚመሰክር ቢኖር ከምኵራብ እንዲያወጡት አይሁድ ከዚህ በፊት ተስማምተው ነበርና።
23Todėl jo tėvai pasakė: “Jis suaugęs, klauskite jį patį”.
23ስለዚህ ወላጆቹ። ሙሉ ሰው ነው፥ ጠይቁት አሉ።
24Tada jie antrą kartą pasišaukė buvusį neregį ir pasakė jam: “Šlovink Dievą! Mes žinome, kad Tas žmogus nusidėjėlis”.
24ስለዚህ ዕውር የነበረውን ሰው ሁለተኛ ጠርተው። እግዚአብሔርን አክብር፤ ይህ ሰው ኃጢአተኛ መሆኑን እኛ እናውቃለን አሉት።
25Jis atsiliepė: “Ar Jis nusidėjėlis, aš nežinau. Viena žinau: buvau aklas, o dabar regiu”.
25እርሱም መልሶ። ኃጢአተኛ መሆኑን አላውቅም፤ ዕውር እንደ ነበርሁ አሁንም እንዳይ ይህን አንድ ነገር አውቃለሁ አለ።
26Jie vėl klausė: “Ką Jis tau darė? Kaip Jis tau atvėrė akis?”
26ደግመውም። ምን አደረገልህ? እንዴትስ ዓይኖችህን ከፈተ? አሉት።
27Šis atsakė: “Aš jau sakiau jums, tik jūs neklausėte. Ar dar kartą norite išgirsti? Gal ir jūs norite tapti Jo mokiniais?”
27እርሱም መልሶ። አስቀድሜ ነገርኋችሁ አልሰማችሁምም፤ ስለ ምን ዳግመኛ ልትሰሙ ትወዳላችሁ? እናንተ ደግሞ ደቀ መዛሙርቱ ልትሆኑ ትወዳላችሁን? አላቸው።
28Tada jie išplūdo jį ir pasakė: “Tu esi Jo mokinys, o mes­Mozės mokiniai.
28ተሳድበውም። አንተ የእርሱ ደቀ መዝሙር ነህ፥ እኛ ግን የሙሴ ደቀ መዛሙርት ነን፤
29Mes žinome, kad Mozei Dievas kalbėjo, o iš kur šitas, nežinome”.
29እግዚአብሔር ሙሴን እንደ ተናገረው እኛ እናውቃለን፥ ይህ ሰው ግን ከወዴት እንደ ሆነ አናውቅም አሉት።
30Žmogus jiems atsakė: “Tai tikrai nuostabu, kad nežinote, iš kur Jis. O juk Jis man atvėrė akis!
30ሰውዬው መለሰ እንዲህም አላቸው። ከወዴት እንደ ሆነ እናንተ አለማወቃችሁ ይህ ድንቅ ነገር ነው፥ ዳሩ ግን ዓይኖቼን ከፈተ።
31Žinome, kad Dievas neišklauso nusidėjėlių. Bet jei kas yra Dievo garbintojas ir vykdo Jo valią­tą Jis išklauso.
31እግዚአብሔርን የሚፈራ ፈቃዱንም የሚያደርግ ቢኖር ያንን እግዚአብሔር ይሰማዋል እንጂ ኃጢአተኞችን እንዳይሰማ እናውቃለን።
32Nuo amžių negirdėta, kad kas būtų atvėręs aklo gimusio akis!
32ዕውር ሆኖ የተወለደውን ዓይኖች ማንም እንደ ከፈተ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ አልተሰማም፤
33Jei šitas nebūtų iš Dievo, Jis nieko negalėtų padaryti”.
33ይህ ሰው ከእግዚአብሔር ባይሆን ምንም ሊያደርግ ባልቻለም ነበር።
34Jie atsakė jam: “Tu visas gimęs nuodėmėse ir dar mus mokai?!” Ir išvarė jį lauk.
34መልሰው። አንተ ሁለንተናህ በኃጢአት ተወለድህ፥ አንተም እኛን ታስተምረናለህን? አሉት። ወደ ውጭም አወጡት።
35Jėzus, išgirdęs, kad jie išvarė jį lauk, surado jį ir paklausė: “Ar tiki Dievo Sūnų?”
35ኢየሱስም ወደ ውጭ እንዳወጡት ሰማ ሲያገኘውም። አንተ በእግዚአብሔር ልጅ ታምናለህን? አለው።
36Šis atsakė: “O kas Jis, Viešpatie, kad Jį tikėčiau?”
36እርሱም መልሶ። ጌታ ሆይ፥ በእርሱ አምን ዘንድ ማን ነው? አለ።
37Jėzus jam tarė: “Tu jau esi Jį matęs, ir dabar Jis su tavimi kalba”.
37ኢየሱስም። አይተኸዋልም ከአንተ ጋርም የሚናገረው እርሱ ነው አለው።
38Tada jis sušuko: “Tikiu, Viešpatie!”, ir pagarbino Jį.
38እርሱም። ጌታ ሆይ፥ አምናለሁ አለ፤ ሰገደለትም።
39O Jėzus pasakė: “Aš atėjau į šį pasaulį daryti teismo,­kad neregiai praregėtų, o regintieji apaktų”.
39ኢየሱስም። የማያዩ እንዲያዩ የሚያዩም እንዲታወሩ እኔ ወደዚህ ዓለም ለፍርድ መጣሁ አለ።
40Prie Jo esantys fariziejai, tai išgirdę, paklausė: “Tai gal ir mes akli?”
40ከፈሪሳውያንም ከእርሱ ጋር የነበሩት ይህን ሰምተው። እኛ ደግሞ ዕውሮች ነንን? አሉት።
41Jėzus jiems atsakė: “Jei būtumėte akli, neturėtumėte nuodėmės, bet dabar sakote: ‘Mes regime!’­Todėl jūsų nuodėmė pasilieka”.
41ኢየሱስም አላቸው። ዕውሮችስ ብትሆኑ ኃጢአት ባልሆነባችሁም ነበር፤ አሁን ግን። እናያለን ትላላችሁ፤ ኃጢአታችሁ ይኖራል።