1Kartą, kai minios veržėsi prie Jo klausytis Dievo žodžio, Jis stovėjo prie Genezareto ežero
1ሕዝቡም የእግዚአብሔርን ቃል እየሰሙ ሲያስጠብቡት ሳሉ፥ እርሱ ራሱ በጌንሳሬጥ ባሕር ዳር ቆሞ ነበር፤
2ir pamatė dvi valtis, stovinčias prie ežero kranto. Žvejai buvo išlipę iš jų ir plovė tinklus.
2በባሕር ዳርም ቆመው የነበሩትን ሁለት ታንኳዎች አየ፤ ዓሣ አጥማጆች ግን ከእነርሱ ውስጥ ወጥተው መረቦቻቸውን ያጥቡ ነበር።
3Įlipęs į vieną valtį, kuri buvo Simono, Jis paprašė truputį atsistumti nuo kranto ir atsisėdęs mokė minias iš valties.
3ከታንኳዎቹም የስምዖን ወደ ነበረች ወደ አንዲቱ ገብቶ ከምድር ጥቂት ፈቀቅ እንዲያደርጋት ለመነው፤ በታንኳይቱም ተቀምጦ ሕዝቡን ያስተምር ነበር።
4Baigęs kalbėti, Jis tarė Simonui: “Irkis į gilumą ir išmeskite tinklus valksmui”.
4ነገሩንም ከጨረሰ በኋላ፥ ስምዖንን። ወደ ጥልቁ ፈቀቅ በል መረቦቻችሁንም ለማጥመድ ጣሉ አለው።
5Simonas Jam atsakė: “Mokytojau, visą naktį vargę, mes nieko nesugavome, bet dėl Tavo žodžio užmesiu tinklą”.
5ስምዖንም መልሶ። አቤቱ፥ ሌሊቱን ሁሉ አድረን ስንደክም ምንም አልያዝንም፤ ነገር ግን በቃልህ መረቦቹን እጥላለሁ አለው።
6Tai padarę, jie užgriebė didelę daugybę žuvų, kad net jų tinklas pradėjo trūkinėti.
6ይህንም ባደረጉ ጊዜ እጅግ ብዙ ዓሣ ያዙ፤ መረቦቻቸውም ተቀደዱ።
7Jie pamojo savo bendrininkams, buvusiems kitoje valtyje, atplaukti į pagalbą. Tie atplaukė ir pripildė žuvų abi valtis, kad jos beveik skendo.
7በሌላ ታንኳም የነበሩትን ጓደኞቻቸውን መጥተው እንዲያግዙአቸው ጠቀሱ፤ መጥተውም ሁለቱ ታንኳዎች እስኪሰጥሙ ድረስ ሞሉአቸው።
8Tai matydamas, Simonas Petras puolė Jėzui po kojų, sakydamas: “Pasitrauk nuo manęs, Viešpatie, nes ašnusidėjėlis!”
8ስምዖን ጴጥሮስ ግን ባየ ጊዜ በኢየሱስ ጕልበት ላይ ወድቆ። ጌታ ሆይ፥ እኔ ኃጢአተኛ ነኝና ከኔ ተለይ አለው።
9Mat jį ir visus draugus apėmė nuostaba dėl to valksmo žuvų, kurias jie sugavo;
9ስላጠመዱት ዓሣ እርሱ ከእርሱ ጋርም የነበሩ ሁሉ ተደንቀዋልና፥
10taip pat Zebediejaus sūnus Jokūbą ir Joną, kurie buvo Petro bendrai. O Jėzus tarė Simonui: “Nebijok! Nuo šiol žmones žvejosi”.
10እንዲሁም ደግሞ የስምዖን ባልንጀሮች የነበሩ የዘብዴዎስ ልጆች ያዕቆብና ዮሐንስም ተደነቁ። ኢየሱስም ስምዖንን። አትፍራ፤ ከእንግዲህ ወዲህ ሰውን የምታጠምድ ትሆናለህ አለው።
11Išvilkę į krantą valtis, jie viską paliko ir nusekė paskui Jį.
11ታንኳዎችንም ወደ ምድር አድርሰው ሁሉን ትተው ተከተሉት።
12Jam esant viename mieste, atėjo vyras, visas raupsuotas. Pamatęs Jėzų, jis parpuolė ant žemės ir maldavo: “Viešpatie, jei nori, gali mane apvalyti!”
12ከከተማዎችም በአንዲቱ ሳለ፥ እነሆ፥ ለምጽ የሞላበት ሰው ነበረ፤ ኢየሱስንም አይቶ በፊቱ ወደቀና። ጌታ ሆይ፥ ብትወድስ፥ ልታነጻኝ ትችላለህ ብሎ ለመነው።
13Jėzus, ištiesęs ranką, palietė raupsuotąjį ir tarė: “Noriu, būk švarus!” Ir iškart raupsai pranyko.
13እጁንም ዘርግቶ ዳሰሰውና። እወዳለሁ፥ ንጻ አለው፤ ወዲያውም ለምጹ ለቀቀው።
14Jėzus jam liepė niekam šito nepasakoti: “Tik nueik, pasirodyk kunigui ir atiduok auką už pagijimą, kaip Mozės įsakyta, jiems paliudyti”.
14እርሱም ለማንም እንዳይናገር አዘዘው፥ ነገር ግን። ሄደህ ራስህን ለካህን አሳይ፥ ለእነርሱም ምስክር እንዲሆን ስለ መንጻትህ ሙሴ እንዳዘዘ መሥዋዕት አቅርብ አለው።
15Tačiau garsas apie Jį sklido vis plačiau, ir didelės minios rinkdavosi Jo pasiklausyti bei pagyti nuo savo ligų.
15ወሬው ግን አብዝቶ ወጣ፥ ብዙ ሕዝብም ሊሰሙትና ከደዌአቸው ሊፈወሱ ይሰበሰቡ ነበር፤
16O Jis pasitraukdavo į dykvietes melstis.
16ነገር ግን እርሱ ወደ ምድረ በዳ ፈቀቅ ብሎ ይጸልይ ነበር።
17Vieną dieną, kai Jis mokė žmones, ten sėdėjo fariziejų bei Įstatymo mokytojų, susirinkusių iš visų Galilėjos ir Judėjos kaimų bei Jeruzalės. Ir ten buvo Viešpaties jėga, kad gydytų žmones.
17አንድ ቀንም ያስተምር ነበር፤ ከገሊላና ከይሁዳ መንደሮችም ሁሉ ከኢየሩሳሌምም መጥተው የነበሩ ፈሪሳውያንና የሕግ መምህራን ይቀመጡ ነበር፤ እርሱም እንዲፈውስ የጌታ ኃይል ሆነለት።
18Štai vyrai neštuvais atnešė paralyžiuotą žmogų. Jie bandė jį įnešti į vidų ir paguldyti priešais Jėzų.
18እነሆም፥ አንድ ሽባ በአልጋ ተሸክመው አመጡ፤ አግብተውም በፊቱ ሊያኖሩት ይሹ ነበር።
19Nerasdami pro kur įnešti dėl žmonių gausybės, jie užlipo ant stogo ir, praardę jį, nuleido ligonį kartu su neštuvais žemyn ties Jėzumi.
19ስለ ሕዝቡም ብዛት እንዴት አድርገው እንዲያገቡት ሲያቅታቸው፥ ወደ ሰገነቱ ወጡ የጣራውንም ጡብ አሳልፈው በመካከል በኢየሱስ ፊት ከነአልጋው አወረዱት።
20Matydamas jų tikėjimą, Jis tarė: “Žmogau, tavo nuodėmės tau atleistos!”
20እምነታቸውንም አይቶ። አንተ ሰው፥ ኃጢአትህ ተሰረየችልህ አለው።
21Tada Rašto žinovai ir fariziejai pradėjo svarstyti: “Kas per vienas šitas piktžodžiaujantis? Kas gali atleisti nuodėmes, jei ne vienas Dievas?”
21ጻፎችና ፈሪሳውያንም። ይህ የሚሳደብ ማን ነው? ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ኃጢአት ሊያስተሰርይ ማን ይችላል? ብለው ያስቡ ጀመር።
22Jėzus, supratęs jų mintis, prabilo: “Kodėl taip svarstote savo širdyse?
22ኢየሱስም አሳባቸውን እያወቀ መልሶ። በልባችሁ ምን ታስባላችሁ?
23Kas lengviauar pasakyti: ‘Tavo nuodėmės tau atleistos’, ar pasakyti: ‘Kelkis ir vaikščiok’?
23ኃጢአትህ ተሰረየችልህ ከማለት ወይስ። ተነሣና ሂድ ከማለት ማናቸው ይቀላል?
24O kad žinotumėte Žmogaus Sūnų turint žemėje valdžią atleisti nuodėmes,čia Jis tarė paralyžiuotajam,sakau tau: kelkis, imk savo gultą ir eik namo!”
24ነገር ግን በምድር ላይ ኃጢአት ሊያስተሰርይ ለሰው ልጅ ሥልጣን እንዳለው እንድታውቁ ብሎ፥ ሽባውን። አንተን እልሃለሁ፥ ነተሣ፥ አልጋህን ተሸክመህ ወደ ቤትህ ሂድ አለው።
25Tas tuojau atsikėlė jų akivaizdoje, pasiėmė neštuvus ir, šlovindamas Dievą, nuėjo namo.
25በዚያን ጊዜም በፊታቸው ተነሣ፥ ተኝቶበትም የነበረውን ተሸክሞ እግዚአብሔርን እያመሰገነ ወደ ቤቱ ሄደ።
26Visi didžiai stebėjosi ir šlovino Dievą. Apimti baimės, jie kalbėjo: “Šiandien matėme stebinančių dalykų!”
26ሁሉንም መገረም ያዛቸው፥ እግዚአብሔርንም አመስግነው። ዛሬስ ድንቅ ነገር አየን እያሉ ፍርሃት ሞላባቸው።
27Po to išėjęs Jis pastebėjo muitininką, vardu Levį, sėdintį muitinėje, ir jam tarė: “Sek paskui mane!”
27ከዚህም በኋላ ወጥቶ ሌዊ የሚባል ቀራጭ በመቅረጫው ተቀምጦ ተመለከተና። ተከተለኝ አለው።
28Tas atsikėlė ir, viską palikęs, nusekė paskui Jį.
28ሁሉንም ተወ፤ ተነሥቶም ተከተለው።
29Levis savo namuose iškėlė Jam didelį pokylį. Prie stalo susirinko gausus būrys muitininkų ir kitų svečių.
29ሌዊም በቤቱ ታላቅ ግብዣ አደረገለት፤ ከእነርሱም ጋር በማዕድ ተቀምጠው የነበሩ ከቀራጮችና ከሌሎች ሰዎች ብዙ ሕዝብ ነበሩ።
30Rašto žinovai ir fariziejai murmėjo ir prikaišiojo Jėzaus mokiniams: “Kodėl jūs valgote ir geriate su muitininkais ir nusidėjėliais?”
30ፈሪሳውያንና ጻፎቻቸውም በደቀ መዛሙርቱ ላይ። ስለ ምን ከቀራጮችና ከኃጢአተኞች ጋር ትበላላችሁ ትጠጡማላችሁ? ብለው አንጐራጐሩ።
31Jėzus jiems atsakė: “Ne sveikiesiems reikia gydytojo, bet ligoniams.
31ኢየሱስም መልሶ። ሕመምተኞች እንጂ ባለ ጤናዎች ባለ መድኃኒት አያስፈልጋቸውም፤
32Aš atėjau šaukti ne teisiųjų, bet nusidėjėlių atgailai”.
32ኃጢአተኞችን ወደ ንስሐ እንጂ ጻድቃንን ልጠራ አልመጣሁም አላቸው።
33Tada jie sakė Jam: “Kodėl Jono mokiniai dažnai pasninkauja ir meldžiasi, taip pat ir fariziejų mokiniai, o Tavieji valgo ir geria?”
33እነርሱም። የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ስለ ምን ብዙ ይጦማሉ ጸሎትስ ስለ ምን ያደርጋሉ፥ ደግሞም የፈሪሳውያን ደቀ መዛሙርት ስለ ምን እንደዚሁ ያደርጋሉ፤ የአንተ ደቀ መዛሙርት ግን ይበላሉ ይጠጣሉም? አሉት።
34Jėzus jiems atsakė: “Argi galite versti pasninkauti vestuvininkus, kol su jais yra jaunikis?
34ኢየሱስም። ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሚዜዎችን ልታስጦሙ ትችላላችሁን?
35Ateis dienos, kai jaunikis bus iš jų atimtas, ir tada, tomis dienomis, jie pasninkaus”.
35ነገር ግን ወራት ይመጣል፥ ሙሽራውም ከእነርሱ ሲወሰድ ያንጊዜ፥ በዚያ ወራት ይጦማሉ አላቸው።
36Jėzus dar pasakė jiems palyginimą: “Niekas neplėšia lopo iš naujo drabužio ir nesiuva jo ant seno. Nes ir naująjį jis suplėšytų, ir senajam netiktų lopas iš naujojo.
36ደግሞም ምሳሌ እንዲህ ሲል ነገራቸው። የአዲስ ልብስ እራፊ ባረጀ ልብስ ላይ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግን አዲሱን ይቀደዋል ደግሞም አዲስ እራፊ ለአሮጌው አይስማማውም።
37Taip pat niekas nepila jauno vyno į senus vynmaišius. Jaunas vynas suplėšytų vynmaišius, pats ištekėtų, ir vynmaišiai niekais nueitų.
37ባረጀ አቁማዳም አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግን አዲሱ የወይን ጠጅ አቁማዳውን ያፈነዳል፥ እርሱም ይፈሳል አቁማዳውም ይጠፋል።
38Jauną vyną reikia pilti į naujus vynmaišius, ir tada abeji išsilaiko.
38አዲሱን የወይን ጠጅ ግን በአዲስ አቁማዳ ማኖር ይገባል፥ ሁለቱም ይጠባበቃሉ።
39Ir niekas, gėręs seno vyno, nenori jauno; jis sako: ‘Senasis geresnis!’ ”
39አሮጌ የወይን ጠጅ ሲጠጣ አዲሱን የሚሻ ማንም የለም፤ አሮጌው ይጣፍጣል ይላልና።