1Vieną sabatą, Jam einant per javų lauką, mokiniai skabė varpas ir, ištrynę tarp delnų, valgė.
1በሰንበትም በእርሻ መካከል ያልፍ ነበር ደቀ መዛሙርቱም እሸት ይቀጥፉ በእጃቸውም እያሹ ይበሉ ነበር።
2Kai kurie iš fariziejų jiems tarė: “Kodėl darote, kas per sabatą draudžiama?!”
2ከፈሪሳውያን ግን አንዳንዶቹ። በሰንበት ሊያደርግ ያልተፈቀደውን ስለ ምን ታደርጋላችሁ? አሉአቸው።
3Jėzus jiems atsakė: “Nejaugi neskaitėte, ką darė Dovydas, kai buvo alkanas pats ir jo palydovai?
3ኢየሱስም ለእነርሱ መልሶ። ዳዊት በተራበ ጊዜ እርሱ አብረውት ከነበሩ ጋር ያደረገውን፥ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንደ ገባ ከካህናት ብቻ በቀር መብላቱ ያልተፈቀደውን የመሥዋዕትን እንጀራ ይዞ እንደ በላ፥ ከእርሱም ጋር ለነበሩት ደግሞ እንደ ሰጣቸው ይህን አላነበባችሁምን? አለ።
4Kaip jis įėjo į Dievo namus, ėmė padėtinės duonos, valgė ir davė savo palydai, nors jos niekam neleistina valgyti, tik kunigams!”
5የሰው ልጅ የሰንበት ጌታ ነው አላቸውም።
5Ir Jis pridūrė: “Žmogaus Sūnus yra ir sabato Viešpats”.
6በሌላው ሰንበትም ወደ ምኵራብ ገብቶ አስተማረ፤ በዚያም ቀኝ እጁ የሰለለች ሰው ነበረ፤
6Kitą sabatą Jis nuėjo į sinagogą ir mokė. Ten buvo žmogus, kurio dešinė ranka buvo padžiūvusi.
7ጻፎችና ፈሪሳውያንም መክሰሻ ሊያገኙበት በሰንበት ይፈውስ እንደ ሆነ ይጠባበቁት ነበር።
7Rašto žinovai ir fariziejai stebėjo, ar Jis gydys per sabatą, kad rastų kuo Jį apkaltinti.
8እርሱ ግን አሳባቸውን አውቆ እጁ የሰለለችውን ሰው። ተነሣና በመካከል ቁም አለው፤ ተነሥቶም ቆመ።
8Bet Jis, žinodamas jų mintis, tarė vyrui su padžiūvusia ranka: “Kelkis ir stok į vidurį”. Tas atsistojo.
9ኢየሱስም። እጠይቃችኋለሁ፤ በሰንበት በጎ ማድረግ ተፈቅዶአልን ወይስ ክፉ? ነፍስ ማዳንን ወይስ መግደል? አላቸው።
9Tada Jėzus jiems pasakė: “Aš klausiu jūsų: ar per sabatą leistina gera daryti ar bloga? Gelbėti gyvybę ar pražudyti?”
10ሁላቸውንም ዙሪያውን አየና ሰውዬውን። እጅህን ዘርጋ አለው። እርሱም እንዲህ አደረገ፥ እጁም እንደ ሁለተኛይቱ ዳነች።
10Ir, apžvelgęs visus aplinkui, tarė tam žmogui: “Ištiesk savo ranką!” Tas taip padarė, ir jo ranka tapo sveika kaip ir kita.
11እነርሱም ቍጣ ሞላባቸው፥ በኢየሱስም ምን እንዲያደርጉበት እርስ በርሳቸው ተባባሉ።
11O jie baisiai įniršo ir tarėsi, ką galėtų Jėzui padaryti.
12በነዚህም ወራት ይጸልይ ዘንድ ወደ ተራራ ወጣ፥ ሌሊቱንም ሁሉ ወደ እግዚአብሔር ሲጸልይ አደረ።
12Tomis dienomis Jis užkopė į kalną melstis ir ten praleido visą naktį, melsdamasis Dievui.
13በነጋም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን ጠራ፥ ከእነርሱም አሥራ ሁለት መረጠ ደግሞም ሐዋርያት ብሎ ሰየማቸው፤
13Išaušus rytui, Jis pasišaukė savo mokinius ir iš jų išsirinko dvylika, kuriuos ir pavadino apaštalais:
14እነርሱም፥ ጴጥሮስ ብሎ እንደ ገና የሰየመው ስምዖን፥ ወንድሙም እንድርያስ፥ ያዕቆብም ዮሐንስም፥ ፊልጶስም በርተሎሜዎስም፥
14Simoną, kurį praminė Petru, jo brolį Andriejų, Jokūbą, Joną, Pilypą ir Baltramiejų,
15ማቴዎስም ቶማስም፥ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብም ቀናተኛ የሚባለው ስምዖንም፥
15Matą ir Tomą, Alfiejaus sūnų Jokūbą ir Simoną, vadinamą Uoliuoju,
16የያዕቆብ ይሁዳም፥ አሳልፎ የሰጠውም የአስቆሮቱ ይሁዳ ናቸው።
16Jokūbo sūnų Judą ir Judą Iskarijotą, kuris tapo išdaviku.
17ከእነርሱም ጋር ወርዶ በተካከለ ስፍራ ቆመ፥ ከደቀ መዛሙርቱም ወገን ብዙ ሕዝብ ነበረ፥ ደግሞም ሊሰሙትና ከደዌአቸው ሊፈወሱ ከይሁዳ ሁሉ ከኢየሩሳሌምም ከጢሮስና ከሲዶና ባሕር ዳርም የመጡ ብዙ ሰዎች ነበሩ፤
17Nusileidęs su jais žemyn, sustojo lygumoje. Ten buvo daugybė Jo mokinių ir didelės minios žmonių iš visos Judėjos ir Jeruzalės, iš Tyro ir Sidono pajūrio. Jie susirinko Jo pasiklausyti ir pagyti nuo savo ligų.
18ከርኵሳንም መናፍስት ይሠቃዩ የነበሩት ተፈወሱ፤
18Buvo pagydomi kankinamieji netyrųjų dvasių.
19ከእርሱም ኃይል ወጥቶ ሁሉን ይፈውስ ነበርና ሕዝቡ ሁሉ ሊዳስሱት ይሹ ነበር።
19Visa minia stengėsi Jį paliesti, nes iš Jo ėjo jėga ir visus gydė.
20እርሱም ወደ ደቀ መዛሙርቱ ዓይኑን አነሣ እንዲህም አላቸው። እናንተ ድሆች ብፁዓን ናችሁ፥ የእግዚአብሔር መንግሥት የእናንተ ነውና።
20Tada, pakėlęs akis į savo mokinius, Jis prabilo: “Palaiminti jūs, vargšai, nes jūsų yra Dievo karalystė.
21እናንተ አሁን የምትራቡ ብፁዓን ናችሁ፥ ትጠግባላችሁና። እናንተ አሁን የምታለቅሱ ብፁዓን ናችሁ፥ ትስቃላችሁና።
21Palaiminti, kurie dabar alkstate, nes būsite pasotinti. Palaiminti, kurie dabar verkiate, nes juoksitės.
22ሰዎች ስለ ሰው ልጅ ሲጠሉአችሁ ሲለዩአችሁም ሲነቅፉአችሁም ስማችሁንም እንደ ክፉ ሲያወጡ፥ ብፁዓን ናችሁ።
22Palaiminti jūs, kai žmonės jūsų nekęs, kai jus atskirs, šmeiš ir atmes jūsų vardą kaip blogą dėl Žmogaus Sūnaus.
23እነሆ፥ ዋጋችሁ በሰማይ ታላቅ ነውና በዚያን ቀን ደስ ይበላችሁ ዝለሉም፤ አባቶቻቸው ነቢያትን እንዲህ ያደርጉባቸው ነበርና።
23Džiaukitės tą dieną ir linksminkitės, nes štai jūsų atlygis didelis danguje. Taip jų protėviai darė pranašams.
24ነገር ግን እናንተ ባለ ጠጎች ወዮላችሁ፥ መጽናናታችሁን ተቀብላችኋልና።
24Bet vargas jums, turtingieji, nes jūs jau atsiėmėte savo paguodą!
25እናንተ አሁን የጠገባችሁ ወዮላችሁ፥ ትራባላችሁና። እናንተ አሁን የምትስቁ ወዮላችሁ፥ ታዝናላችሁና ታለቅሱማላችሁ።
25Vargas jums, kurie dabar sotūs, nes būsite alkani! Vargas jums, kurie dabar juokiatės, nes jūs liūdėsite ir verksite!
26ሰዎች ሁሉ መልካም ሲናገሩላችሁ፥ ወዮላችሁ፤ አባቶቻቸው ለሐሰተኞች ነቢያት እንዲሁ ያደርጉላቸው ነበርና።
26Vargas jums, kai visi žmonės jus giria, nes ir jų protėviai taip gyrė netikrus pranašus!”
27ነገር ግን ለእናንተ ለምትሰሙ እላችኋለሁ፥ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ ለሚጠሉአችሁ መልካም አድርጉ፥
27“Bet jums, kurie klausotės, sakau: mylėkite savo priešus, darykite gera tiems, kurie jūsų nekenčia.
28የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ስለሚበድሉአችሁም ጸልዩ።
28Laiminkite tuos, kurie jus keikia, ir melskitės už savo skriaudėjus.
29ጕንጭህን ለሚመታህ ደግሞ ሁለተኛውን ስጠው፥ መጐናጸፊያህንም ለሚወስድ እጀ ጠባብህን ደግሞ አትከልክለው።
29Kas trenkia tau per vieną skruostą, atsuk ir antrąjį; kas atima iš tavęs apsiaustą, atiduok jam ir tuniką.
30ለሚለምንህ ሁሉ ስጥ፥ ገንዘብህንም የሚወስድ እንዲመልስ አትጠይቀው።
30Duok kiekvienam, kuris prašo, ir nereikalauk atgal iš to, kuris tavo atėmė.
31ሰዎችም ሊያደርጉላችሁ እንደምትወዱ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉላቸው።
31Kaip norite, kad jums žmonės darytų, taip ir jūs darykite jiems.
32የሚወዱአችሁንማ ብትወዱ፥ ምን ምስጋና አላችሁ? ኃጢአተኞች ደግሞ የሚወዱአቸውን ይወዳሉና።
32Jei mylite tuos, kurie jus myli, tai koks čia jūsų nuopelnas? Juk ir nusidėjėliai myli juos mylinčius.
33መልካምም ለሚያደርጉላችሁ መልካም ብታደርጉ፥ ምን ምስጋና አላችሁ? ኃጢአተኞች ደግሞ ያን ያደርጋሉና።
33Jei darote gera tiems, kurie jums gera daro, tai koks jūsų nuopelnas? Juk ir nusidėjėliai taip daro.
34እንድትወስዱባቸው ተስፋ ለምታደርጉአቸው ብታበድሩ፥ ምን ምስጋና አላችሁ? ኃጢአተኞች ደግሞ በትክክል እንዲቀበሉ ለኃጢአተኞች ያበድራሉ።
34Jei skolinate tik tiems, iš kurių tikitės atgausią, koks jūsų nuopelnas? Juk ir nusidėjėliai skolina nusidėjėliams, kad atgautų paskolą.
35ነገር ግን ጠላቶቻችሁን ውደዱ፤ መልካም አድርጉ፤ ምንም ተስፋ ሳታደርጉም አበድሩ፥ ዋጋችሁም ታላቅ ይሆናል፥ የልዑልም ልጆች ትሆናላችሁ፥ እርሱ ለማያመሰግኑ ለክፉዎችም ቸር ነውና።
35Bet mylėkite savo priešus, darykite gera ir skolinkite, nieko nesitikėdami. Tuomet jūsų atlygis bus didelis, ir jūs būsite Aukščiausiojo vaikai; nes Jis maloningas ir nedėkingiesiems, ir piktiesiems.
36አባታችሁ ርኅሩኅ እንደ ሆነ ርኅሩኆች ሁኑ።
36Būkite gailestingi, kaip ir jūsų Tėvas yra gailestingas.
37አትፍረዱ አይፈረድባችሁምም፤ አትኰንኑ አትኰነኑምም። ይቅር በሉ ይቅርም ትባላላችሁ።
37Neteiskite ir nebūsite teisiami; nesmerkite ir nebūsite pasmerkti; atleiskite, ir jums bus atleista.
38ስጡ ይሰጣችሁማል፤ በምትሰፍሩበት መስፈሪያ ተመልሶ ይሰፈርላችኋልና፥ የተጨቈነና የተነቀነቀ የተትረፈረፈም መልካም መስፈሪያ በእቅፋችሁ ይሰጣችኋል።
38Duokite, ir jums bus duota; saiką gerą, prikimštą, sukratytą ir su kaupu duos jums į užantį. Kokiu saiku seikite, tokiu jums bus atseikėta”.
39ምሳሌም አላቸው። ዕውር ዕውርን ሊመራ ይችላልን? ሁለቱ በጕድጓድ አይወድቁምን?
39Jis pasakė jiems palyginimą: “Ar gali aklas vesti aklą? Argi ne abu įkris į duobę?!
40ደቀ መዝሙር ከመምህሩ አይበልጥም፤ ፈጽሞ የተማረ ሁሉ ግን እንደ መምህሩ ይሆናል።
40Mokinys nėra viršesnis už savo mokytoją: kiekvienas mokinys, jei gerai išlavintas, bus kaip jo mokytojas.
41በወንድምህም ዓይን ያለውን ጉድፍ ስለ ምን ታያለህ፥ በራስህ ዓይን ግን ያለውን ምሰሶ ስለ ምን አትመለከትም?
41Kodėl matai krislą brolio akyje, o nepastebi rąsto savojoje?
42በዓይንህ ያለውን ምሰሶ ራስህ ሳታይ፥ እንዴት ወንድምህን። ወንድሜ ሆይ፥ በዓይንህ ያለውን ጉድፍ ላውጣ ፍቀድልኝ ልትል ትችላለህ? አንተ ግብዝ፥ አስቀድመህ ከዓይንህ ምሰሶውን አውጣ ከዚያም በኋላ በወንድምህ ዓይን ያለውን ጉድፍ ታወጣ ዘንድ አጥርተህ ታያለህ።
42Ir kaip gali sakyti broliui: ‘Broli, leisk, išimsiu krislą iš tavo akies’,pats nematydamas savo akyje rąsto?! Veidmainy, pirmiau išritink rąstą iš savo akies, o tada matysi, kaip iš brolio akies išimti krislelį.
43ክፉ ፍሬ የሚያደርግ መልካም ዛፍ የለምና፥ እንዲሁም መልካም ፍሬ የሚያደርግ ክፉ ዛፍ የለም።
43Nėra gero medžio, kuris duotų blogus vaisius, ir nėra blogo, kuris duotų gerus vaisius.
44ዛፍ ሁሉ ከፍሬው ይታወቃልና፤ ከእሾህ በለስ አይለቅሙም፥ ከአጣጥ ቍጥቋጦም ወይን አይቈርጡም።
44Kiekvienas medis pažįstamas iš jo vaisių. Nuo erškėčių niekas nerenka figų, o nuo gervuogių krūmo neskina vynuogių.
45በልብ ሞልቶ ከተረፈው አፉ ይናገራልና መልካም ሰው ከልብ መልካም መዝገብ መልካሙን ያወጣል፥ ክፉ ሰውም ከልብ ክፉ መዝገብ ክፉውን ያወጣል።
45Geras žmogus iš gero savo širdies lobyno iškelia gera, o blogas iš blogo savo širdies lobyno iškelia bloga. Jo lūpos kalba tai, ko pertekusi širdis”.
46ስለ ምን። ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ ትሉኛላችሁ፥ የምለውንም አታደርጉም?
46“Kodėl vadinate mane: ‘Viešpatie, Viešpatie’, o nedarote, ką sakau?
47ወደ እኔ የሚመጣ ሁሉ ቃሌንም ሰምቶ የሚያደርገው፥ ማንን እንዲመስል አሳያችኋለሁ።
47Kiekvienas, kuris ateina pas mane, klausosi mano žodžių ir juos vykdo,Aš parodysiu jums, į ką jis panašus.
48ቤት ሲሠራ አጥልቆ የቆፈረ በዓለት ላይም የመሠረተ ሰውን ይመስላል፤ ጐርፍም በመጣ ጊዜ ወንዙ ያን ቤት ገፋው፥ በዓለት ላይም ስለ ተመሠረተ ሊያናውጠው አልቻለም።
48Jis panašus į namą statantį žmogų, kuris giliai iškasė žemę ir padėjo pamatus ant uolos. Užėjus potvyniui, srovė atsimušė į tą namą, bet neįstengė jo pajudinti, nes buvo pastatytas ant uolos.
49ሰምቶ የማያደርገው ግን ያለ መሠረት በምድር ላይ ቤቱን የሠራ ሰውን ይመስላል፤ ወንዙም ገፋው ወዲያውም ወደቀ የዚያ ቤት አወዳደቅም ታላቅ ሆነ።
49O kas klausosi, bet nevykdo, panašus į žmogų, pasistačiusį namą be pamato, ant žemės. Vos tik srovė į jį atsimušė, jis kaipmat sugriuvo, ir to namo griuvimas buvo smarkus”.