1Baigęs visus savo pamokymus klausytojams, Jėzus sugrįžo į Kafarnaumą.
1ቃሉን ሁሉ በሕዝብ ጆሮዎች በጨረሰ ጊዜ ወደ ቅፍርናሆም ገባ።
2Vieno šimtininko branginamas tarnas sirgo ir buvo arti mirties.
2አንድ የመቶ አለቃም ነበረ፤ የሚወደውም ባሪያው ታሞ ሊሞት ቀርቦ ነበር።
3Išgirdęs apie Jėzų, šimtininkas pasiuntė pas Jį kelis žydų vyresniuosius, prašydamas Jį ateiti ir išgydyti tarną.
3ስለ ኢየሱስም በሰማ ጊዜ የአይሁድን ሽማግሎች ወደ እርሱ ላከና መጥቶ ባሪያውን እንዲያድን ለመነው።
4Atėję pas Jėzų, jie karštai prašė, sakydami: “Jis vertas, kad jam tai padarytum,
4እነርሱም ወደ ኢየሱስ መጥተው። ይህን ልታደርግለት ይገባዋል፤
5nes jis myli mūsų tautą ir mums yra pastatęs sinagogą”.
5ሕዝባችንን ይወዳልና ምኵራብም ራሱ ሠርቶልናል ብለው አጽንተው ለመኑት።
6Jėzus nuėjo su jais. Kai Jis buvo netoli namų, šimtininkas atsiuntė savo draugus, kad Jam pasakytų: “Viešpatie, nesivargink! Aš nesu vertas, kad užeitum po mano stogu.
6ኢየሱስም ከእነርሱ ጋር ሄደ። አሁንም ወደ ቤቱ በቀረበ ጊዜ የመቶው አለቃ ወዳጆቹን ወደ እርሱ ላከ፤ አለውም። ጌታ ሆይ በቤቴ ጣራ በታች ልትገባ አይገባኝምና አትድከም፤
7Taip pat savęs nelaikau vertu ateiti pas Tave. Bet tark žodį, ir mano tarnas pasveiks.
7ስለዚህም ወደ አንተ ልመጣ እንዲገባኝ ሰውነቴን አልቈጠርሁትም፤ ነገር ግን ቃል ተናገር፥ ብላቴናዬም ይፈወሳል።
8Juk ir aš, būdamas valdinys, turiu sau pavaldžių kareivių. Taigi sakau kuriam iš jų: ‘Eik’, ir jis eina; sakau kitam: ‘Ateik čia’, ir jis ateina; sakau tarnui: ‘Padaryk tai’, ir jis daro”.
8እኔ ደግሞ ከሌሎች በታች የምገዛ ሰው ነኝ፥ ከእኔም በታች ወታደሮች አሉኝ፥ አንዱንም። ሂድ ብለው ይሄዳል፥ ሌላውንም። ና ብለው ይመጣል፥ ባሪያዬንም። ይህን አድርግ ብለው ያደርጋል።
9Tai girdėdamas, Jėzus stebėjosi juo ir, atsigręžęs į Jį lydinčią minią, tarė: “Sakau jums—net Izraelyje neradau tokio didelio tikėjimo!”
9ኢየሱስም ይህን ሰምቶ በእርሱ ተደነቀ፥ ዘወርም ብሎ ለተከተሉት ሕዝብ። እላችኋለሁ፥ በእስራኤልስ እንኳ እንዲህ ያለ ትልቅ እምነት አላገኘሁም አላቸው።
10Sugrįžę į namus, pasiųstieji rado tarną pasveikusį.
10የተላኩትም ወደ ቤት ተመልሰው ባሪያውን ባለ ጤና ሆኖ አገኙት።
11Po to Jėzus ėjo į miestą, vardu Nainą. Kartu su Juo keliavo daugelis Jo mokinių ir gausi minia.
11በነገውም ናይን ወደምትባል ወደ አንዲት ከተማ ሄደ፥ ደቀ መዛሙርቱም ብዙ ሕዝብም ከእርሱ ጋር አብረው ሄዱ።
12Kai Jis prisiartino prie miesto vartų, štai nešė numirėlįvienintelį motinos sūnų, o ji buvo našlė. Kartu su ja ėjo didelė miesto minia.
12ወደ ከተማይቱም በር በቀረበ ጊዜ፥ እነሆ፥ የሞተ ሰው ተሸክመው አወጡ፤ እርሱም ለእናቱ አንድ ልጅ ነበረ፥ እርስዋም መበለት ነበረች፥ ብዙም የከተማ ሕዝብ ከእርስዋ ጋር አብረው ነበሩ።
13Pamačiusiam motiną Viešpačiui pagailo jos, ir Jis tarė: “Neverk!”
13ጌታም ባያት ጊዜ አዘነላትና። አታልቅሽ አላት።
14Priėjęs Jis palietė neštuvus. Nešėjai sustojo, ir Jis pasakė: “Jaunuoli, sakau tau: kelkis!”
14ቀርቦም ቃሬዛውን ነካ፥ የተሸከሙትም ቆሙ፤ አለውም። አንተ ጐበዝ፥ እልሃለሁ፥ ተነሣ።
15Numirėlis atsisėdo ir pradėjo kalbėti. Jėzus atidavė jį motinai.
15የሞተውም ቀና ብሎ ተቀመጠ ሊናገርም ጀመረ፥ ለእናቱም ሰጣት።
16Visus apėmė baimė, ir jie šlovino Dievą, sakydami: “Didis pranašas iškilo tarp mūsų”, ir: “Dievas aplankė savo tautą”.
16ሁሉንም ፍርሃት ያዛቸውና። ታላቅ ነቢይ በእኛ መካከል ተነሥቶአል፥ ደግሞ። እግዚአብሔር ሕዝቡን ጐበኘ እያሉ እግዚአብሔርን አመሰገኑ።
17Ta žinia apie Jį pasklido po visą Judėją ir visą apylinkę.
17ይህም ዝና ስለ እርሱ በይሁዳ ሁሉ በዙሪያውም ባለች አገር ሁሉ ወጣ።
18Visa tai pranešė Jonui jo mokiniai.
18ደቀ መዛሙርቱም ለዮሐንስ እነዚህን ሁሉ አወሩ።
19Tada Jonas, pasišaukęs du savo mokinius, siuntė juos pas Jėzų paklausti: “Ar Tu esi Tas, kuris turi ateiti, ar mums laukti kito?”
19ዮሐንስም ከደቀ መዛሙርቱ ሁለት ወደ እርሱ ጠርቶ። የሚመጣው አንተ ነህን ወይስ ሌላውን እንጠብቅ? ብሎ ወደ ኢየሱስ ላከ።
20Atėję pas Jį, tie vyrai tarė: “Jonas Krikštytojas mus siuntė pas Tave, klausdamas: ‘Ar Tu esi Tas, kuris turi ateiti, ar mums laukti kito?’ ”
20ሰዎቹም ወደ እርሱ መጥተው። መጥምቁ ዮሐንስ። የሚመጣው አንተ ነህን ወይስ ሌላውን እንጠብቅ? ብሎ ወደ አንተ ላከን አሉት።
21Kaip tik tuo metu Jis pagydė daugelį nuo ligų bei negalių ir nuo piktųjų dvasių, daugeliui aklųjų dovanojo regėjimą.
21በዚያች ሰዓት ከደዌና ከሥቃይ ከክፉዎች መናፍስትም ብዙዎችን ፈወሰ፥ ለብዙ ዕውሮችም ማየትን ሰጠ።
22Tad atsakydamas, Jis tarė jiems: “Nuėję praneškite Jonui, ką matėte ir girdėjote: aklieji regi, luošieji vaikščioja, raupsuotieji apvalomi, kurtieji girdi, mirusieji prikeliami, vargšams skelbiama Geroji naujiena.
22ኢየሱስም መልሶ። ሄዳችሁ ያያችሁትን የሰማችሁትንም ለዮሐንስ አውሩለት፤ ዕውሮች ያያሉ፥ አንካሶችም ይሄዳሉ፥ ለምጻሞችም ይነጻሉ፥ ደንቆሮዎችም ይሰማሉ፥ ሙታንም ይነሣሉ፥ ለድሆችም ወንጌል ይሰበካል፤
23Ir palaimintas, kas nepasipiktins manimi”.
23በእኔም የማይሰናከለው ሁሉ ብፁዕ ነው አላቸው።
24Jono pasiuntiniams nuėjus, Jis pradėjo kalbėti minioms apie Joną: “Ko išėjote į dykumą pažiūrėti? Ar vėjo linguojamos nendrės?
24የዮሐንስ መልክተኞችም ከሄዱ በኋላ፥ ለሕዝቡ ስለ ዮሐንስ ይናገር ጀመር እንዲህም አለ። ምን ልታዩ ወደ ምድረ በዳ ወጣችሁ? ነፋስ የሚወዘውዘውን ሸምበቆን? ወይስ ምን ልታዩ ወጣችሁ?
25Ko išėjote pamatyti? Ar švelniais drabužiais vilkinčio žmogaus? Antai tie, kurie ištaigingai vilki ir prabangiai gyvena, yra karaliaus rūmuose.
25ቀጭን ልብስ የለበሰውን ሰውን? እነሆ፥ ጌጠኛ ልብስ የሚለብሱና በቅምጥልነት የሚኖሩ በነገሥታት ቤት አሉ።
26Tai ko gi išėjote pamatyti? Ar pranašo? Taip, sakau jums, ir daug daugiau negu pranašo.
26ወይስ ምን ልታዩ ወጣችሁ? ነቢይን? አዎን እላችኋለሁ፥ ከነቢይም የሚበልጠውን።
27Jis yra tas, apie kurį parašyta: ‘Štai Aš siunčiu pirma Tavęs savo pasiuntinį, kuris nuties Tau kelią’.
27እነሆ፥ መንገድህን በፊትህ የሚጠርግ መልክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ ተብሎ የተጻፈለት ይህ ነው።
28Sakau jums: tarp gimusių iš moters nebuvo didesnio pranašo už Joną Krikštytoją, bet ir mažiausias Dievo karalystėje didesnis už jį.
28እላችኋለሁ፥ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ ማንም የለም፤ በእግዚአብሔር መንግሥት ግን ከሁሉ የሚያንሰው ይበልጠዋል።
29Jį išgirdusi, visa tauta, taip pat ir muitininkai, pripažino Dievo teisingumą, nes leidosi krikštijami Jono krikštu.
29የሰሙትም ሕዝብ ሁሉ ቀራጮች እንኳ ሳይቀሩ በዮሐንስ ጥምቀት ተጠምቀው እግዚአብሔርን አጸደቁ፤
30Tik fariziejai ir Įstatymo mokytojai atstūmė, ką Dievas jiems buvo sumanęs, nesiduodami Jono krikštijami”.
30ፈሪሳውያንና ሕግ አዋቂዎች ግን በእርሱ ስለ አልተጠመቁ የእግዚአብሔርን ምክር ከራሳቸው ጣሉ።
31“Su kuo galėčiau palyginti šios kartos žmones? Į ką jie panašūs?
31እንግዲህ የዚችን ትውልድ ሰዎች በምን አስመስላቸዋለሁ? ማንንስ ይመስላሉ?
32Jie panašūs į vaikus, kurie, susėdę turgavietėje, vieni kitiems šaukia: ‘Mes jums grojome, o jūs nešokote; mes giedojome raudas, o jūs neverkėte’.
32በገበያ የሚቀመጡትን ልጆች ይመስላሉ፥ እርስ በርሳቸውም እየተጠራሩ። እንቢልታ ነፋንላችሁ አልዘፈናችሁምም፤ ሙሾ አወጣንላችሁ አላለቀሳችሁምም ይላል።
33Buvo atėjęs Jonas Krikštytojas. Jis nevalgė duonos ir negėrė vyno, tai jūs sakėte: ‘Jis demono apsėstas’.
33መጥምቁ ዮሐንስ እንጀራ ሳይበላ የወይን ጠጅም ሳይጠጣ መጥቶ ነበርና። ጋኔን አለበት አላችሁት።
34Atėjo Žmogaus Sūnus; Jis valgo ir geria, tai jūs vėl sakote: ‘Štai rijūnas ir vyno gėrėjas, muitininkų ir nusidėjėlių bičiulis’.
34የሰው ልጅ እየበላና እየጠጣ መጥቶአልና። እነሆ፥ በላተኛና የወይን ጠጅ ጠጭ፥ የቀራጮችና የኃጢአተኞች ወዳጅ አላችሁት።
35Bet išmintį pateisina visi jos vaikai”.
35ጥበብም ለልጆችዋ ሁሉ ጸደቀች።
36Vienas fariziejus pakvietė Jėzų kartu valgyti. Atėjęs į fariziejaus namus, Jis sėdo prie stalo.
36ከፈሪሳውያንም አንድ ከእርሱ ጋር ይበላ ዘንድ ለመነው፤ በፈሪሳዊው ቤትም ገብቶ በማዕድ ተቀመጠ።
37Ir štai moteris, kuri buvo žinoma mieste nusidėjėlė, sužinojusi, kad Jis fariziejaus namuose, atsinešė alebastrinį indą kvapaus tepalo
37እነሆም በዚያች ከተማ ኃጢአተኛ የነበረች አንዲት ሴት፤ በፈሪሳዊው ቤት በማዕድ እንደ ተቀመጠ ባወቀች ጊዜ፥ ሽቱ የሞላበት የአልባስጥሮስ ቢልቃጥ አመጣች።
38ir, verkdama priėjusi iš užpakalio prie Jo kojų, ėmė laistyti jas ašaromis, šluostyti savo galvos plaukais, bučiavo Jo kojas ir tepė jas tepalu.
38በስተ ኋላውም በእግሩ አጠገብ ቆማ እያለቀሰች በእንባዋ እግሩን ታርስ ጀመረች፥ በራስ ጠጕርዋም ታብሰው እግሩንም ትስመው ሽቱም ትቀባው ነበረች።
39Tai matydamas, fariziejus, kuris Jėzų pasikvietė, samprotavo: “Jeigu šitas būtų pranašas, Jis žinotų, kas tokia ši moteris, kuri Jį liečia, nes jinusidėjėlė!”
39የጠራው ፈሪሳዊም አይቶ። ይህስ ነቢይ ቢሆን፥ ይህች የምትዳስሰው ሴት ማን እንደ ሆነች እንዴትስ እንደ ነበረች ባወቀ ነበር፥ ኃጢአተኛ ናትና ብሎ በልቡ አሰበ።
40O Jėzus tarė: “Simonai, turiu tau ką pasakyti”. Tas atsiliepė: “Sakyk, Mokytojau!”
40ኢየሱስም መልሶ። ስምዖን ሆይ፥ የምነግርህ ነገር አለኝ አለው። እርሱም። መምህር ሆይ፥ ተናገር አለ።
41“Skolintojas turėjo du skolininkus. Vienas buvo skolingas penkis šimtus denarų, o kitaspenkiasdešimt.
41ለአንድ አበዳሪ ሁለት ተበዳሪዎች ነበሩት በአንዱ አምስት መቶ ዲናር ነበረበት በሁለተኛውም አምሳ።
42Jiems neturint iš ko atiduoti, jis dovanojo abiem. Kuris labiau jį mylės?”
42የሚከፍሉትም ቢያጡ ለሁለቱም ተወላቸው። እንግዲህ ከእነርሱ አብልጦ የሚወደው ማንኛው ነው?
43Simonas atsakė: “Manau, jog tas, kuriam daugiau dovanota”. Jėzus tarė: “Teisingai nusprendei”.
43ስምዖንም መልሶ። ብዙ የተወለቱ ይመስለኛል አለ። እርሱም። በእውነት ፈረድህ አለው።
44Ir, atsisukęs į moterį, Jis tarė Simonui: “Matai šitą moterį? Aš atėjau į tavo namus, tu nedavei man vandens kojoms nusimazgoti, o ji laistė jas ašaromis ir šluostė savo plaukais.
44ወደ ሴቲቱም ዘወር ብሎ ስምዖንን እንዲህ አለው። ይህችን ሴት ታያለህን? እኔ ወደ ቤትህ ገባሁ፥ ውኃ ስንኳ ለእግሬ አላቀረብህልኝም፤ እርስዋ ግን በእንባዋ እግሬን አራሰች በጠጕርዋም አበሰች።
45Tu manęs nepabučiavai, o ji, vos man atėjus, nesiliauja bučiavusi mano kojų.
45አንተ አልሳምኸኝም፤ እርስዋ ግን ከገባሁ ጀምራ እግሬን ከመሳም አላቋረጠችም።
46Tu aliejumi man galvos nepatepei, o ji tepalu patepė man kojas.
46አንተ ራሴን ዘይት አልቀባኸኝም፤ እርስዋ ግን እግሬን ሽቱ ቀባች።
47Todėl sakau tau: jos gausios nuodėmės jai atleidžiamos, nes ji labai pamilo. Kam mažai atleista, tas menkai myli”.
47ስለዚህ እልሃለሁ፥ እጅግ ወዳለችና ብዙ ያለው ኃጢአትዋ ተሰርዮላታል፤ ጥቂት ግን የሚሰረይለት ጥቂት ይወዳል።
48Jis tarė jai: “Tavo nuodėmės atleistos”.
48እርስዋንም። ኃጢአትሽ ተሰርዮልሻል አላት።
49Esantieji kartu su Juo už stalo ėmė svarstyti: “Kas gi Jis toks, kad net ir nuodėmes atleidžia?!”
49ከእርሱም ጋር በማዕድ ተቀምጠው የነበሩት በልባቸው። ኃጢአትን እንኳ የሚያስተሰርይ ይህ ማን ነው? ይሉ ጀመር።
50O Jis tarė moteriai: “Tavo tikėjimas išgelbėjo tave. Eik rami”.
50ሴቲቱንም። እምነትሽ አድኖሻል፤ በሰላም ሂጂ አላት።