Lithuanian

Amharic: New Testament

Mark

3

1Jis vėl atėjo į sinagogą, o ten buvo žmogus su padžiūvusia ranka.
1ደግሞም ወደ ምኵራብ ገባ፥ በዚያም እጁ የሰለለች ሰው ነበር፤
2Jie stebėjo Jį, ar Jis gydys šį sabato dieną, kad galėtų Jėzų apkaltinti.
2ሊከሱትም፥ በሰንበት ይፈውሰው እንደ ሆነ ይጠባበቁት ነበር።
3Jėzus tarė žmogui su padžiūvusia ranka: “Stok į vidurį!”
3እጁ የሰለለችውንም ሰው። ተነሥተህ ወደ መካከል ና አለው።
4O juos paklausė: “Ar sabato dieną leistina daryti gera, ar bloga? Gelbėti gyvybę ar žudyti?” Bet anie tylėjo.
4በሰንበት በጎ ማድረግ ተፈቅዶአልን? ወይስ ክፉ? ነፍስ ማዳን ወይስ መግደል? አላቸው፤ እነርሱም ዝም አሉ።
5Tada, rūsčiai juos apžvelgęs ir nuliūdęs dėl jų širdies kietumo, tarė tam žmogui: “Ištiesk ranką!” Šis ištiesė, ir ranka tapo sveika kaip ir kita.
5ስለ ልባቸውም ድንዛዜ አዝኖ ዙሪያውን እየተመለከተ በቍጣ አያቸው፥ ሰውየውንም። እጅህን ዘርጋ አለው።
6Išėję fariziejai tuojau pradėjo tartis su erodininkais, kaip Jėzų pražudyti.
6ዘረጋትም፥ እጁም ዳነች። ፈሪሳውያንም ወጥተው ወዲያው እንዴት አድርገው እንዲያጠፉት ከሄሮድስ ወገን ጋር ተማከሩበት።
7O Jėzus su savo mokiniais pasitraukė prie ežero. Jį sekė didelė minia iš Galilėjos. Ir iš Judėjos,
7ኢየሱስም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደ ባህር ፈቀቅ አለ፤ ከገሊላ የመጡም ብዙ ሰዎች ተከተሉት፤
8Jeruzalės ir Idumėjos, iš anapus Jordano bei Tyro ir Sidono šalies atvyko daugybė žmonių, kurie buvo girdėję apie Jo didelius darbus.
8እንዴት ትልቅ ነገርም እንዳደረገው ሰምተው ብዙ ሰዎች ከይሁዳ ከኢየሩሳሌምም ከኤዶምያስም ከዮርዳኖስ ማዶም ከጢሮስና ከሲዶና ምድርም ወደ እርሱ መጡ።
9Jėzus liepė mokiniams laikyti Jam paruoštą nedidelę valtį, kad minia Jo nesuspaustų.
9ሰዎቹም እንዳያጋፉት ታንኳን ያቆዩለት ዘንድ ደቀ መዛሙርቱን አዘዛቸው፤
10Mat Jis buvo daugelį išgydęs, ir visi, kuriuos kankino ligos, veržėsi prie Jo, norėdami Jį paliesti.
10ብዙ ሰዎችን አድኖ ነበርና፥ ስለዚህም ሥቃይ ያለባቸው ሁሉ እንዲዳስሱት ይወድቁበት ነበር።
11Taip pat netyrosios dvasios, vos tik Jį pamačiusios, parpuldavo priešais Jį ir šaukdavo: “Tu esi Dievo Sūnus!”
11ርኵሳን መናፍስትም ባዩት ጊዜ በፊቱ ተደፍተው። አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ እያሉ ጮኹ።
12Bet Jėzus griežtai jas drausdavo, kad Jo negarsintų.
12እንዳይገልጡትም በጣም አዘዛቸው።
13Jėzus užkopė ant kalno ir pasišaukė, kuriuos pats norėjo, ir jie atėjo pas Jį.
13ወደ ተራራም ወጣ፥ ራሱም የወደዳቸውን ወደ እርሱ ጠራ፥ ወደ እርሱም ሄዱ።
14Jis paskyrė dvylika, kad jie būtų kartu su Juo ir kad galėtų siųsti juos pamokslauti
14ከእርሱም ጋር እንዲኖሩና ለመስበክ እንዲልካቸው፥
15ir jie turėtų valdžią gydyti ligas ir išvarinėti demonus:
15ድውዮችንም ሊፈውሱ አጋንንትንም ሊያወጡ ሥልጣን ይሆንላቸው ዘንድ አሥራ ሁለት አደረገ፤
16Simoną, pavadinęs jį Petru;
16ስምዖንንም ጴጥሮስ ብሎ ሰየመው፤
17Zebediejaus sūnų Jokūbą ir Jokūbo brolį Joną (juos pavadinęs Boanerges, tai yra “griaustinio vaikai”);
17የዘብዴዎስንም ልጅ ያዕቆብን የያዕቆብንም ወንድም ዮሐንስን ቦአኔርጌስ ብሎ ሰየማቸው፥ የነጎድጓድ ልጆች ማለት ነው፤
18Andriejų, Pilypą, Baltramiejų, Matą, Tomą, Alfiejaus sūnų Jokūbą, Tadą, Simoną Kananietį
18እንድርያስንም ፊልጶስንም በርተሎሜውስንም ማቴዎስንም ቶማስንም የእልፍዮስን ልጅ ያዕቆብንም ታዴዎስንም ቀነናዊውንም ስምዖንን፥
19ir Judą Iskarijotą, kuris Jį ir išdavė. Ir jie grįžo namo.
19አሳልፎ የሰጠውንም የአስቆሮቱን ይሁዳን።
20Vėl susirinko tiek žmonių, kad jie nebegalėjo nė pavalgyti.
20ወደ ቤትም መጡ፤ እንጀራም መብላት ስንኳ እስኪሳናቸው ድረስ እንደ ገና ብዙ ሰዎች ተሰበሰቡ።
21Saviškiai, apie tai išgirdę, ėjo sulaikyti Jo, sakydami, kad Jis išėjęs iš proto.
21ዘመዶቹም ሰምተው። አበደ ብለዋልና ሊይዙት ወጡ።
22Atvykę iš Jeruzalės Rašto žinovai sakė: “Jis turi Belzebulą”, ir: “Demonų kunigaikščio jėga Jis išvaro demonus”.
22ከኢየሩሳሌም የወረዱ ጻፎችም። ብዔል ዜቡል አለበት፤ ደግሞ። በአጋንንት አለቃ አጋንንትን ያወጣል ብለው ተናገሩ።
23O Jėzus, pasivadinęs juos, kalbėjo palyginimais: “Kaip gali šėtonas išvaryti šėtoną?
23እነርሱንም ወደ እርሱ ጠርቶ በምሳሌ አላቸው። ሰይጣን ሰይጣንን ሊያወጣው እንዴት ይችላል?
24Jei karalystė suskilusi, tokia karalystė negali išsilaikyti.
24መንግሥትም እርስ በርስዋ ከተለያየች ያች መንግሥት ልትቆም አትችልም፤
25Ir jei namai suskilę, tokie namai negali išsilaikyti.
25ቤትም እርስ በርሱ ከተለያየ ያ ቤት ሊቆም አይችልም።
26Ir jei šėtonas sukyla pats prieš save ir tampa susiskaldęs, jis negali išsilaikyti ir žlunga.
26ሰይጣንም ራሱን ተቃውሞ ከተለያየ፥ መጨረሻ ይሆንበታል እንጂ ሊቆም አይችልም።
27Niekas negali įeiti į galiūno namus ir pasigrobti jo turto, pirmiau nesurišęs galiūno. Tik tada jis apiplėš jo namus.
27ነገር ግን አስቀድሞ ኃይለኛውን ሳያስር ወደ ኃይለኛው ቤት ገብቶ ዕቃውን ሊበዘብዝ የሚችል የለም፥ ከዚያም ወዲያ ቤቱን ይበዘብዛል።
28Iš tiesų sakau jums: bus atleistos žmonių vaikams visos nuodėmės ir piktžodžiavimai, kaip jie bepiktžodžiautų;
28እውነት እላችኋለሁ፥ ለሰው ልጆች ኃጢአት ሁሉ የሚሳደቡትም ስድብ ሁሉ ይሰረይላቸዋል፤
29bet jei kas piktžodžiautų Šventajai Dvasiai, tam niekada nebus atleista, ir jis amžiams bus pasmerktas”.
29በመንፈስ ቅዱስ ላይ የሚሳደብ ሁሉ ግን የዘላለም ኃጢአት ዕዳ ይሆንበታል እንጂ ለዘላለም አይሰረይለትም።
30Mat jie sakė: “Jis turi netyrąją dvasią”.
30ርኵስ መንፈስ አለበት ይሉ ነበርና።
31Atėjo Jėzaus motina ir broliai ir, lauke sustoję, prašė Jį pakviesti.
31እናቱና ወንድሞቹም መጡ በውጭም ቆመው ወደ እርሱ ልከው አስጠሩት።
32Aplink Jį sėdėjo minia, kai Jam pranešė: “Štai Tavo motina ir broliai bei seserys lauke stovi ir ieško Tavęs”.
32ብዙ ሰዎችም በዙሪያው ተቀምጠው ነበሩና። እነሆ፥ እናትህ ወንድሞችህም በውጭ ቆመው ይፈልጉሃል አሉት።
33O Jis atsakė: “Kas yra mano motina ir mano broliai?”
33መልሶም። እናቴ ማን ናት? ወንድሞቼስ እነ ማን ናቸው? አላቸው።
34Ir, apžvelgęs aplinkui sėdinčius, tarė: “Štai mano motina ir mano broliai!
34በዙሪያው ተቀምጠው ወደ ነበሩትም ተመለከተና። እነሆ እናቴ ወንድሞቼም።
35Kas vykdo Dievo valią, tas mano brolis, ir sesuo, ir motina”.
35የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ሁሉ፥ እርሱ ወንድሜ ነው እኅቴም እናቴም አለ።