Lithuanian

Amharic: New Testament

Mark

2

1Po kelių dienų Jėzus vėl atėjo į Kafarnaumą. Žmonės, išgirdę Jį esant namuose,
1ከጥቂት ቀን በኋላ ወደ ቅፍርናሆም ደግሞ ገብቶ በቤት እንደ ሆነ ተሰማ።
2nedelsiant susirinko, ir taip gausiai, jog nė prie durų nebeliko vietos. O Jis skelbė jiems žodį.
2በደጅ ያለው ስፍራም እስኪጠባቸው ድረስ ብዙ ሰዎች ተሰበሰቡ፤ ቃሉንም ይነግራቸው ነበር።
3Tada keturi vyrai atnešė pas Jį paralyžiuotą žmogų.
3አራት ሰዎችም የተሸከሙትን ሽባ አመጡለት።
4Negalėdami dėl minios prinešti jo prie Jėzaus, jie praplėšė stogą namo, kur Jis buvo, ir, padarę skylę, nuleido žemyn neštuvus, ant kurių gulėjo paralyžiuotasis.
4ስለ ሕዝቡም ብዛት ወደ እርሱ ማቅረብ ቢያቅታቸው እርሱ ያለበትን የቤቱን ጣራ አነሡ፥ ነድለውም ሽባው የተኛበትን አልጋ አወረዱ።
5Išvydęs jų tikėjimą, Jėzus tarė paralyžiuotajam: “Sūnau, atleidžiamos tau tavo nuodėmės!”
5ኢየሱስም እምነታቸውን አይቶ ሽባውን። አንተ ልጅ፥ ኃጢአትህ ተሰረየችልህ አለው።
6Tenai sėdėjo keletas Rašto žinovų ir svarstė savo širdyse:
6ከጻፎችም አንዳንዶቹ በዚያ ተቀምጠው ነበር በልባቸውም። ይህ ሰው ስለ ምን እንደዚህ ያለ ስድብ ይናገራል?
7“Kodėl Jis taip piktžodžiauja? Kas gali atleisti nuodėmes, jei ne vienas Dievas?!”
7ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ኃጢአት ሊያስተሰርይ ማን ይችላል? ብለው አሰቡ።
8Jėzus, iš karto savo dvasia supratęs jų mintis, tarė: “Kam taip svarstote savo širdyse?
8ወዲያውም ኢየሱስ በልባቸው እንዲህ እንዳሰቡ በመንፈስ አውቆ እንዲህ አላቸው። በልባችሁ ይህን ስለ ምን ታስባላችሁ?
9Kas lengviau­ar pasakyti paralyžiuotam: ‘Tau atleidžiamos nuodėmės’, ar liepti: ‘Kelkis, imk neštuvus ir vaikščiok’?
9ሽባውን። ኃጢአትህ ተሰረየችልህ ከማለት ወይስ። ተነሣ አልጋህንም ተሸከምና ሂድ ከማለት ማናቸው ይቀላል?
10Bet, kad žinotumėte Žmogaus Sūnų turintį valdžią atleisti žemėje nuodėmes,­čia Jis tarė paralyžiuotajam,­
10ነገር ግን ለሰው ልጅ በምድር ላይ ኃጢአትን ሊያስተሰርይ ሥልጣን እንዳለው እንድታውቁ፤
11sakau tau: kelkis, imk savo neštuvus ir eik namo!”
11ሽባውን። አንተን እልሃለሁ፥ ተነሣ፥ አልጋህን ተሸከምና ወደ ቤትህ ሂድ አለው።
12Šis tuojau atsikėlė ir, visiems matant, pasiėmęs neštuvus, išėjo. Visi stebėjosi ir garbino Dievą, sakydami: “Tokių dalykų mes niekad nesame matę”.
12ተነሥቶም ወዲያው አልጋውን ተሸክሞ በሁሉ ፊት ወጣ፥ ስለዚህም ሰዎች ሁሉ ተገረሙና። እንዲህ ያለ ከቶ አላየንም ብለው እግዚአብሔርን አከበሩ።
13Jėzus vėl nuėjo į paežerę. Didelė minia rinkosi prie Jo, ir Jis juos mokė.
13ደግሞም በባሕር አጠገብ ወጣ፤ ሕዝቡም ሁሉ ወደ እርሱ መጡና አስተማራቸው።
14Praeidamas Jis pamatė Levį, Alfiejaus sūnų, sėdintį muitinėje, ir tarė jam: “Sek paskui mane!” Šis atsikėlė ir nusekė paskui Jį.
14ሲያልፍም በመቅረጫው ተቀምጦ የነበረውን የእልፍዮስን ልጅ ሌዊን አየና። ተከተለኝ አለው። ተነሥቶም ተከተለው።
15Kai Jėzus Levio namuose valgė, drauge prie stalo su Jėzumi ir mokiniais sėdėjo daug muitininkų bei nusidėjėlių, nes tokių buvo daug ir jie sekė paskui Jį.
15በቤቱም በማዕድ ተቀምጦ ሳለ፥ ብዙ ቀራጮችና ኃጢአተኞች ከኢየሱስና ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ተቀመጡ፤ ብዙ ነበሩ ይከተሉትም ነበር።
16Rašto žinovai ir fariziejai, išvydę Jį valgantį su muitininkais ir nusidėjėliais, klausė Jo mokinių: “Kodėl Jis valgo su muitininkais ir nusidėjėliais?”
16ጻፎችና ፈሪሳውያንም ከቀራጮችና ከኃጢአተኞች ጋር ሲበላ አይተው ለደቀ መዛሙርቱ። ከቀራ ጮችና ከኃጢአተኞች ጋር የሚበላና የሚጠጣ ስለ ምንድር ነው? አሉ።
17Tai išgirdęs, Jėzus atsiliepė: “Ne sveikiesiems reikia gydytojo, bet ligoniams! Aš atėjau šaukti ne teisiųjų, bet nusidėjėlių atgailai”.
17ኢየሱስም ሰምቶ። ሕመምተኞች እንጂ ብርቱዎች ባለ መድኃኒት አያስፈልጋቸውም ኃጢአተኞችን እንጂ ጻድቃንን ልጠራ አልመጣሁም አላቸው።
18Jono mokiniai ir fariziejai pasninkavo. Jie atėję klausė Jėzų: “Kodėl Jono ir fariziejų mokiniai pasninkauja, o Tavieji ne?”
18የዮሐንስ ደቀ መዛሙርትና ፈሪሳውያን ይጦሙ ነበር። መጥተውም። የዮሐንስና የፈሪሳውያን ደቀ መዛሙርት የሚጦሙት የአንተ ደቀ መዛሙርት ግን የማይጦሙት ስለ ምንድር ነው? አሉት።
19Jėzus atsakė: “Argi gali vestuvininkai pasninkauti, kol su jais yra jaunikis? Kol jie turi su savim jaunikį, jie negali pasninkauti.
19ኢየሱስም አላቸው። ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሚዜዎች ሊጦሙ ይችላሉን? ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊጦሙ አይችሉም።
20Bet ateis dienos, kai jaunikis bus iš jų atimtas, ir tada, tomis dienomis, jie pasninkaus.
20ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፥ በዚያ ወራትም ይጦማሉ።
21Niekas nesiuva lopo iš naujo audinio ant sudėvėto drabužio; antraip naujasis atplėštų nuo senojo gabalą, ir pasidarytų dar didesnė skylė.
21በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚጥፍ የለም፤ ቢደረግ ግን፥ አዲሱ መጣፊያ አሮጌውን ይቦጭቀዋል፥ መቀደዱም የባሰ ይሆናል።
22Taip pat niekas nepila jauno vyno į senus vynmaišius. Antraip vynas suplėšytų vynmaišius, ir nueitų niekais ir vynas, ir vynmaišiai. Jaunam vynui būtini nauji vynmaišiai!”
22በአረጀ አቁማዳም አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግን፥ የወይን ጠጁ አቁማዳውን ያፈነዳል የወይኑም ጠጅ ይፈሳል አቁማዳውም ይጠፋል አዲሱን የወይን ጠጅ ግን በአዲስ አቁማዳ ያኖራሉ።
23Sabato dieną Jėzus ėjo per javų lauką, ir Jo mokiniai eidami skabė varpas.
23በሰንበትም በእርሻ መካከል ሲያልፍ ደቀ መዛሙርቱ እየሄዱ እሸት ይቀጥፉ ጀመር።
24Fariziejai Jam sakė: “Žiūrėk, kodėl jie daro per sabatą tai, kas draudžiama?”
24ፈሪሳውያንም። እነሆ፥ በሰንበት ያልተፈቀደውን ስለ ምን ያደርጋሉ? አሉት።
25Jėzus atsakė: “Nejaugi niekad neskaitėte, ką prireikus padarė Dovydas, kai jis ir jo palydovai neturėjo maisto ir buvo išalkę?
25እርሱም። ዳዊት ባስፈለገውና በተራበ ጊዜ፥ እርሱ አብረውት ከነበሩት ጋር ያደረገውን፥ አብያተር ሊቀ ካህናት በነበረ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንደ ገባ፥
26Prie vyriausiojo kunigo Abjataro jis įėjo į Dievo namus ir valgė padėtinės duonos ir davė savo palydovams, nors niekam neleistina jos valgyti, tik kunigams”.
26ከካህናት በቀር መብላት ያልተፈቀደውን የመሥዋዕትን እንጀራ እንደ በላ፥ ከእርሱም ጋር ለነበሩት እንደ ሰጣቸው ከቶ አላነበባችሁምን? አላቸው።
27Ir pridūrė: “Sabatas padarytas žmogui, o ne žmogus sabatui;
27ደግሞ። ሰንበት ስለ ሰው ተፈጥሮአል እንጂ ሰው ስለ ሰንበት አልተፈጠረም፤
28taigi Žmogaus Sūnus yra ir sabato Viešpats”.
28እንዲሁም የሰው ልጅ ለሰንበት እንኳ ጌታዋ ነው አላቸው።