Lithuanian

Amharic: New Testament

Mark

1

1Jėzaus Kristaus, Dievo Sūnaus, Gerosios naujienos pradžia,
1የእግዚአብሔር ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል መጀመሪያ።
2kaip pranašų parašyta: “Štai Aš siunčiu pirma Tavęs savo pasiuntinį, kuris nuties Tau kelią.
2እነሆ፥ መንገድህን የሚጠርግ መልክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ ተብሎ በነቢዩ በኢሳይያስ እንደ ተጻፈ፥
3Dykumoje šaukiančiojo balsas: ‘Paruoškite Viešpačiui kelią! Ištiesinkite Jam takus!’ ”
4ዮሐንስ በምድረ በዳ እያጠመቀ የንስሐንም ጥምቀት ለኃጢአት ስርየት እየሰበከ መጣ።
4Jonas pasirodė dykumoje, krikštijo ir skelbė atgailos krikštą nuodėmėms atleisti.
5የይሁዳም አገር ሁሉ የኢየሩሳሌምም ሰዎች ሁሉ ወደ እርሱ ይወጡ ነበር፥ ኃጢአታቸውንም እየተናዘዙ በዮርዳኖስ ወንዝ ከእርሱ ይጠመቁ ነበር።
5Pas jį traukė visa Judėjos šalis ir Jeruzalės gyventojai. Jie išpažindavo savo nuodėmes ir visi buvo krikštijami Jordano upėje.
6ዮሐንስም የግመል ጠጉር ለብሶ በወገቡ ጠፍር ይታጠቅ አንበጣና የበረሀ ማርም ይበላ ነበር።
6Jonas vilkėjo kupranugario vilnų apdaru, o strėnas buvo susijuosęs odiniu diržu. Jis maitinosi skėriais ir lauko medumi.
7ተጎንብሼ የጫማውን ጠፍር መፍታት የማይገባኝ ከእኔ የሚበረታ በኋላዬ ይመጣል።
7Jis skelbė: “Po manęs ateina galingesnis už mane­aš nevertas nusilenkęs atrišti Jo sandalų dirželio.
8እኔ በውኃ አጠመቅኋችሁ እርሱ ግን በመንፈስ ቅዱስ ያጠምቃችኋል እያለ ይሰብክ ነበር።
8Aš jus krikštijau vandeniu, o Jis krikštys jus Šventąja Dvasia”.
9በዚያ ወራትም ኢየሱስ ከገሊላ ናዝሬት መጥቶ ከዮሐንስ በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠመቀ።
9Tomis dienomis atėjo Jėzus iš Galilėjos Nazareto, ir Jonas pakrikštijo Jį Jordane.
10ወዲያውም ከውኃው በወጣ ጊዜ ሰማያት ሲቀደዱ መንፈስም እንደ ርግብ ሲወርድበት አየና። የምወድህ ልጄ አንተ ነህ፥
10Vos tik išbridęs iš vandens, Jis pamatė prasiveriantį dangų ir Dvasią tarsi balandį, nusileidžiančią ant Jo.
11በአንተ ደስ ይለኛል የሚል ድምፅ ከሰማያት መጣ።
11Ir iš dangaus pasigirdo balsas: “Tu esi mano mylimasis Sūnus, kuriuo Aš gėriuosi”.
12ወዲያውም መንፈስ ወደ ምድረ በዳ አወጣው።
12Ir tuojau Dvasia Jį nuvedė į dykumą.
13በምድረ በዳም ከሰይጣን እየተፈተነ አርባ ቀን ሰነበተ ከአራዊትም ጋር ነበረ፥ መላእክቱም አገለገሉት።
13Jis praleido dykumoje keturiasdešimt dienų šėtono gundomas, buvo kartu su žvėrimis, ir angelai Jam tarnavo.
14ዮሐንስም አልፎ ከተሰጠ በኋላ ኢየሱስ የእግዚአብሔርን መንግሥት ወንጌል እየሰበከና። ዘመኑ ተፈጸመ የእግዚአብሔርም መንግሥት ቀርባለች ንስሐ ግቡ በወንጌልም እመኑ እያለ ወደ ገሊላ መጣ።
14Kai Jonas buvo suimtas, Jėzus atėjo į Galilėją ir skelbė Dievo karalystės Evangeliją:
16በገሊላ ባሕርም አጠገብ ሲያልፍ ስምዖንን ወንድሙንም እንድርያስን መረባቸውን ወደ ባሕር ሲጥሉ አየ፥ ዓሣ አጥማጆች ነበሩና።
15“Atėjo metas, prisiartino Dievo karalystė. Atgailaukite ir tikėkite Evangelija!”
17ኢየሱስም። በኋላዬ ኑና ሰዎችን አጥማጆች እንድትሆኑ አደርጋችኋለሁ አላቸው።
16Eidamas palei Galilėjos ežerą, Jėzus pamatė Simoną ir jo brolį Andriejų, metančius tinklą į ežerą; mat jie buvo žvejai.
18ወዲያውም መረባቸውን ትተው ተከተሉት።
17Jėzus jiems tarė: “Sekite paskui mane, ir Aš jus padarysiu žmonių žvejais”.
19ከዚያም ጥቂት እልፍ ብሎ የዘብዴዎስን ልጅ ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ደግሞ በታንኳ ላይ መረባቸውን ሲያበጁ አየ።
18Ir tuojau, palikę tinklus, jie nusekė paskui Jį.
20ወዲያውም ጠራቸው አባታቸውንም ዘብዴዎስን ከሞያተኞቹ ጋር በታንኳ ላይ ትተው ተከትለውት ሄዱ።
19Paėjęs truputį toliau, Jis pamatė Zebediejaus sūnų Jokūbą ir jo brolį Joną, valtyje betaisančius tinklus.
21ወደ ቅፍርናሆምም ገቡ፤ ወዲያውም በሰንበት ወደ ምኵራብ ገብቶ አስተማረ።
20Tuoj pat Jis pašaukė ir juos. Palikę savo tėvą Zebediejų valtyje su samdiniais, jie nusekė paskui Jį.
22እንደ ባለ ሥልጣን ያስተምራቸው ነበር እንጂ እንደ ጻፎች አይደለምና በትምህርቱ ተገረሙ።
21Jie atėjo į Kafarnaumą, ir iškart, sabato dieną, Jis nuėjo į sinagogą ir ėmė mokyti.
23በዚያን ጊዜም በምኩራባቸው ርኵስ መንፈስ ያለው ሰው ነበረ፤
22Žmonės stebėjosi Jo mokymu, nes Jis mokė kaip turintis valdžią, o ne kaip Rašto žinovai.
24እርሱም። የናዝሬቱ ኢየሱስ ሆይ፥ ከአንተ ጋር ምን አለን? ልታጠፋን መጣህን? ማን እንደ ሆንህ አውቄአለሁ፥ የእግዚአብሔር ቅዱሱ ብሎ ጮኸ።
23Jų sinagogoje buvo žmogus, turintis netyrąją dvasią. Jis sušuko:
25ኢየሱስም። ዝም በል ከእርሱም ውጣ ብሎ ገሠጸው።
24“Palik mus! Ko Tau iš mūsų reikia, Jėzau Nazarieti? Gal atėjai mūsų pražudyti? Aš žinau, kas Tu esi: Dievo Šventasis!”
26ርኵሱም መንፈስ አንፈራገጠውና በታላቅ ድምፅ ጮኾ ከእርሱ ወጣ።
25Jėzus sudraudė jį: “Nutilk ir išeik iš jo!”
27ሁሉም። ይህ ምንድር ነው? በሥልጣን ርኵሳን መናፍስትን ያዝዛል፤ እነርሱም ይታዘዙለታልና ይህ አዲስ ትምህርት ምንድር ነው? ብለው እስኪጠያየቁ ድረስ አደነቁ።
26Tada netyroji dvasia pradėjo jį tąsyti ir, baisiai šaukdama, išėjo iš jo.
28ዝናውም ወዲያው በየስፍራው ወደ ገሊላ ዙሪያ ሁሉ ወጣ።
27Visi apstulbo ir klausinėjo vienas kitą: “Kas tai? Koks čia naujas mokymas? Jis įsakinėja su valdžia net netyrosioms dvasioms, ir tos Jam paklūsta!”
29ወዲያውም ከምኵራብ ወጥቶ ከያዕቆብና ከዮሐንስ ጋር ወደ ስምዖንና ወደ እንድርያስ ቤት ገባ።
28Garsas apie Jį kaipmat pasklido po visą Galilėjos kraštą.
30የስምዖንም አማት በንዳድ ታማ ተኝታ ነበር፥ ስለ እርስዋም ወዲያው ነገሩት።
29Išėję iš sinagogos, jie su Jokūbu ir Jonu atėjo į Simono ir Andriejaus namus.
31ቀርቦም እጅዋን ይዞ አስነሣት ንዳዱም ወዲያው ለቀቃትና አገለገለቻቸው።
30Simono uošvė gulėjo karščiuodama, ir jie tuojau apie tai Jam pasakė.
32ፀሐይም ገብቶ በመሸ ጊዜ፥ የታመሙትንና አጋንንት ያደረባቸውን ሁሉ ወደ እርሱ አመጡ፤
31Jis priėjęs paėmė ją už rankos ir pakėlė; karštis tučtuojau paliovė, ir ji galėjo jiems patarnauti.
33ከተማይቱም ሁላ በደጅ ተሰብስባ ነበር።
32Vakare, saulei nusileidus, pas Jėzų sugabeno visus ligonius ir demonų apsėstuosius.
34በልዩ ልዩ ደዌም የታመሙትን ብዙዎችን ፈወሰ፥ ብዙዎችንም አጋንንት አወጣ፥ አጋንንትም ክርስቶስ መሆኑን አውቀው ነበርና ሊናገሩ አልፈቀደላቸውም።
33Visas miestas buvo susirinkęs prie durų.
35ማለዳም ተነሥቶ ገና ሌሊት ሳለ ወጣ ወደ ምድረ በዳም ሄዶ በዚያ ጸለየ።
34Jis pagydė daug sergančių įvairiomis ligomis, išvarė daug demonų ir neleido demonams kalbėti, nes jie pažino Jį.
36ስምዖንና ከእርሱ ጋር የነበሩትም ገሥግሠው ተከተሉት፥
35Anksti rytą, gerokai prieš aušrą, Jėzus atsikėlęs nuėjo į nuošalią vietą ir ten meldėsi.
37ባገኙትም ጊዜ። ሁሉ ይፈልጉሃል አሉት።
36Simonas ir buvę su juo nusekė iš paskos
38እርሱም። በዚያ ደግሞ ልሰብክ ወደ ሌላ ስፍራ በቅርብ ወዳሉ መንደሮች እንሂድ ስለዚህ ወጥቻለሁና አላቸው።
37ir, suradę Jį, pasakė: “Visi Tavęs ieško”.
39በምኵራባቸውም እየሰበከ አጋንንትንም እያወጣ ወደ ገሊላ ሁሉ መጣ።
38Jis atsakė: “Eikime kitur, į gretimus miestelius, kad ir ten pamokslaučiau, nes tam esu atėjęs”.
40ለምጻምም ወደ እርሱ መጥቶ ተንበረከከና። ብትወድስ ልታነጻኝ ትችላለህ ብሎ ለመነው።
39Ir Jis pamokslavo jų sinagogose po visą Galilėją ir išvarinėjo demonus.
41ኢየሱስም አዘነለት እጁንም ዘርግቶ ዳሰሰውና። እወድዳለሁ፤ ንጻ አለው።
40Pas Jį atėjo raupsuotasis ir atsiklaupęs maldavo: “Jeigu nori, gali mane padaryti švarų”.
42በተናገረም ጊዜ ለምጹ ወዲያው ለቀቀውና ነጻ።
41Jėzus, apimtas gailesčio, ištiesė ranką, palietė jį ir tarė: “Noriu, būk švarus!”
43በብርቱም ተናግሮ ወዲያው አወጣው፤
42Jam tai ištarus, raupsai iškart pranyko, ir jis tapo švarus.
44ለማንም አንዳች እንዳትናገር ተጠንቀቅ፥ ነገር ግን ሄደህ ራስህን ለካህን አሳይ ለእነርሱም ምስክር እንዲሆን ስለ መንጻትህ ሙሴ ያዘዘውን አቅርብ አለው።
43Jėzus liepė jam tuojau pasišalinti ir griežtai įspėjo:
45እርሱ ግን ሲወጣ ብዙ ሊሰብክና ነገሩን ሊያወራ ጀመረ፥ ስለዚህም ኢየሱስ ተገልጦ ወደ ከተማ መግባት ወደ ፊት ተሳነው፥ ነገር ግን በውጭ በምድረ በዳ ይኖር ነበር፤ ከየስፍራውም ወደ እርሱ ይመጡ ነበር።
44“Žiūrėk, kad niekam nieko nepasakotum! Eik, pasirodyk kunigui ir aukok už apvalymą Mozės įsakytą atnašą jiems paliudyti”.
45Bet šis išėjęs pradėjo taip plačiai skelbti ir skleisti tą įvykį, jog Jėzus nebegalėjo viešai pasirodyti mieste. Jis laikėsi už miesto, negyvenamose vietose, bet žmonės iš visur rinkosi pas Jį.