Lithuanian

Amharic: New Testament

Matthew

28

1Sabatui pasibaigus, auštant pirmajai savaitės dienai, Marija Magdalietė ir kita Marija atėjo pažiūrėti kapo.
1በሰንበትም መጨረሻ መጀመሪያው ቀን ሲነጋ መግደላዊት ማርያምና ሁለተኛይቱ ማርያም መቃብሩን ሊያዩ መጡ።
2Ir štai kilo smarkus žemės drebėjimas, nes Viešpaties angelas, nužengęs iš dangaus, atėjo, nurito akmenį nuo angos, ir atsisėdo ant jo.
2እነሆም፥ የጌታ መልአክ ከሰማይ ስለ ወረደ ታላቅ የምድር መናወጥ ሆነ፤ ቀርቦም ድንጋዩን አንከባሎ በላዩ ተቀመጠ።
3Jo išvaizda buvo tarsi žaibo, o drabužiai balti kaip sniegas.
3መልኩም እንደ መብረቅ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ነበረ።
4Išsigandę jo, sargybiniai ėmė drebėti ir sustingo lyg negyvi.
4ጠባቆቹም እርሱን ከመፍራት የተነሣ ተናወጡ እንደ ሞቱም ሆኑ።
5O angelas tarė moterims: “Nebijokite! Aš žinau, kad ieškote Jėzaus, kuris buvo nukryžiuotas.
5መልአኩም መልሶ ሴቶቹን አላቸው። እናንተስ አትፍሩ የተሰቀለውን ኢየሱስን እንድትሹ አውቃለሁና፤
6Jo čia nėra! Jis prisikėlė, kaip buvo sakęs. Įeikite, apžiūrėkite vietą, kur Viešpats gulėjo.
6እንደ ተናገረ ተነሥቶአልና በዚህ የለም፤ የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ።
7Ir skubiai duokite žinią Jo mokiniams: ‘Jis prisikėlė iš numirusių ir eina pirma jūsų į Galilėją; tenai Jį pamatysite’. Štai aš jums tai pasakiau”.
7ፈጥናችሁም ሂዱና። ከሙታን ተነሣ፥ እነሆም፥ ወደ ገሊላ ይቀድማችኋል በዚያም ታዩታላችሁ ብላችሁ ለደቀ መዛሙርቱ ንገሩአቸው።
8Jos skubiai paliko kapą, apimtos išgąsčio bei didelio džiaugsmo, ir bėgo pranešti mokiniams.
8እነሆም፥ ነገርኋችሁ። በፍርሃትና በታላቅ ደስታም ፈጥነው ከመቃብር ሄዱ፥ ለደቀ መዛሙርቱም ሊያወሩ ሮጡ።
9Joms beeinant pranešti Jo mokiniams, štai Jėzus sutiko jas ir tarė: “Sveikos!” Jos priėjo, apkabino Jo kojas ir pagarbino Jį.
9እነሆም፥ ኢየሱስ አገኛቸውና። ደስ ይበላችሁ አላቸው። እነርሱም ቀርበው እግሩን ይዘው ሰገዱለት።
10Jėzus joms tarė: “Nebijokite! Eikite ir pasakykite mano broliams, kad keliautų į Galilėją; ten jie mane pamatys”.
10በዚያን ጊዜ ኢየሱስ። አትፍሩ፤ ሄዳችሁ ወደ ገሊላ እንዲሄዱ ለወንድሞቼ ተናገሩ፥ በዚያም ያዩኛል አላቸው።
11Joms beeinant, keli sargybiniai atbėgo į miestą ir pranešė aukštiesiems kunigams, kas įvyko.
11ሲሄዱም ሳሉ እነሆ፥ ከጠባቆቹ አንዳንድ ወደ ከተማ መጥተው የሆነውን ሁሉ ለካህናት አለቆች አወሩ።
12Tie susitiko su vyresniaisiais, pasitarę davė kareiviams daug pinigų
12ከሽማግሎች ጋርም ተሰብስበው ተማከሩና ለጭፍሮች ብዙ ገንዘብ ሰጥተዋቸው።
13ir primokė: “Sakykite, kad, jums bemiegant, Jo mokiniai atėję naktį Jį pavogė.
13እኛ ተኝተን ሳለን ደቀ መዛሙርቱ በሌሊት መጥተው ሰረቁት በሉ።
14O jeigu apie tai išgirstų valdytojas, mes jį įtikinsime ir apsaugosime jus nuo nemalonumų”.
14ይህም በገዢው ዘንድ የተሰማ እንደ ሆነ፥ እኛ እናስረዳዋለን እናንተም ያለ ሥጋት እንድትሆኑ እናደርጋለን አሉአቸው።
15Šie, paėmę pinigus, taip ir padarė, kaip buvo pamokyti. Šis žodis yra pasklidęs tarp žydų iki šios dienos.
15እነርሱም ገንዘቡን ተቀብለው እንደ አስተማሩአቸው አደረጉ። ይህም ነገር በአይሁድ ዘንድ እስከ ዛሬ ድረስ ሲወራ ይኖራል።
16Vienuolika mokinių nuvyko į Galilėją, ant kalno, kurį jiems buvo nurodęs Jėzus.
16አሥራ አንዱ ደቀ መዛሙርት ግን ኢየሱስ ወዳዘዛቸው ተራራ ወደ ገሊላ ሄዱ፥
17Jį pamatę, jie pagarbino Jį, tačiau kai kurie abejojo.
17ባዩትም ጊዜ ሰገዱለት፤ የተጠራጠሩ ግን ነበሩ።
18Tuomet priėjęs Jėzus jiems pasakė: “Man duota visa valdžia danguje ir žemėje.
18ኢየሱስም ቀረበና እንዲህ ብሎ ተናገራቸው። ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ።
19Todėl eikite ir padarykite mano mokiniais visų tautų žmones, krikštydami juos Tėvo ir Sūnaus, ir Šventosios Dvasios vardu,
19እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።
20mokydami juos laikytis visko, ką tik esu jums įsakęs. Ir štai Aš esu su jumis per visas dienas iki pasaulio pabaigos. Amen”.