1Rytui išaušus, visi aukštieji kunigai ir tautos vyresnieji nusprendė, kad Jėzus turi būti nužudytas.
1ሲነጋም የካህናት አለቆችና የሕዝቡ ሽማግሎች ሁሉ ሊገድሉት በኢየሱስ ላይ ተማከሩ፤
2Surišę nuvedė ir atidavė Jį valdytojui Poncijui Pilotui.
2አስረውም ወሰዱት፥ ለገዢው ለጴንጤናዊው ጲላጦስም አሳልፈው ሰጡት።
3Pamatęs, jog Jėzus pasmerktas, išdavikas Judas gailėjosi ir nunešė atgal aukštiesiems kunigams ir vyresniesiems trisdešimt sidabrinių,
3በዚያን ጊዜ አሳልፎ የሰጠው ይሁዳ እንደ ተፈረደበት አይቶ ተጸጸተ፥ ሠላሳውንም ብር ለካህናት አለቆችና ለሽማግሎች መልሶ።
4sakydamas: “Nusidėjau, išduodamas nekaltą kraują”. Tie atsakė: “Kas mums darbo? Tu žinokis!”
4ንጹሕ ደም አሳልፌ በመስጠቴ በድያለሁ አለ። እነርሱ ግን። እኛስ ምን አግዶን? አንተው ተጠንቀቅ አሉ።
5Nusviedęs šventykloje pinigus, jis išbėgo ir pasikorė.
5ብሩንም በቤተ መቅደስ ጥሎ ሄደና ታንቆ ሞተ።
6Aukštieji kunigai paėmė sidabrinius ir kalbėjo: “Jų negalima dėti į šventyklos iždą, nes tai užmokestis už kraują”.
6የካህናት አለቆችም ብሩን አንሥተው። የደም ዋጋ ነውና ወደ መባ ልንጨምረው አልተፈቀደም አሉ።
7Jie pasitarė ir už juos nupirko puodžiaus dirvą ateiviams laidoti.
7ተማክረውም የሸክላ ሠሪውን መሬት ለእንግዶች መቃብር ገዙበት።
8Todėl ta dirva iki šios dienos vadinasi Kraujo dirva.
8ስለዚህ ያ መሬት እስከ ዛሬ ድረስ የደም መሬት ተባለ።
9Tuomet išsipildė, kas buvo parašyta per pranašą Jeremiją: “Ir paėmė trisdešimt sidabriniųįkainotojo kainą, už kurią buvo Jį suderėję iš Izraelio vaikų,
9በዚያን ጊዜ በነቢዩ በኤርምያስ የተባለው። ከእስራኤል ልጆችም አንዳንዶቹ የገመቱትን፥ የተገመተውን ዋጋ ሠላሳ ብር ያዙ፥
10ir atidavė juos už puodžiaus dirvą; taip man Viešpats buvo paskyręs”.
10ጌታም እንዳዘዘኝ ስለ ሸክላ ሠሪ መሬት ሰጡት። የሚል ተፈጸመ።
11O Jėzus stovėjo valdytojo akivaizdoje. Valdytojas Jį klausė: “Ar Tu esi žydų karalius?” Jėzus atsakė: “Taip yra, kaip sakai”.
11ኢየሱስም በገዢው ፊት ቆመ፤ ገዢውም። የአይሁድ ንጉሥ አንተ ነህን? ብሎ ጠየቀው፤ ኢየሱስም። አንተ አልህ አለው።
12Aukštųjų kunigų ir vyresniųjų kaltinamas, Jis nieko neatsakė.
12የካህናት አለቆችም ሽማግሎችም ሲከሱት ምንም አልመለሰም።
13Tada Pilotas klausė: “Ar negirdi, kiek daug jie prieš Tave liudija?”
13በዚያን ጊዜ ጲላጦስ። ስንት ያህል እንዲመሰክሩብህ አትሰማምን? አለው።
14Bet Jis neatsakė jam nė žodžio ir tuo labai nustebino valdytoją.
14ገዢውም እጅግ እስኪደነቅ ድረስ አንዲት ቃል ስንኳ አልመለሰለትም።
15Per šventę valdytojas buvo pratęs paleisti miniai vieną kalinį, kurio ji norėdavo.
15በዚያም በዓል ሕዝቡ የወደዱትን አንድ እስረኛ ሊፈታላቸው ለገዢው ልማድ ነበረው።
16Tuo metu jie turėjo pagarsėjusį kalinį, vardu Barabą.
16በዚያን ጊዜም በርባን የሚባል በጣም የታወቀ እስረኛ ነበራቸው።
17Todėl, žmonėms susirinkus, Pilotas klausė: “Kurį norite, kad jums paleisčiau: Barabą ar Jėzų, vadinamą Kristumi?”
17እንግዲህ እነርሱ ተሰብስበው ሳሉ ጲላጦስ። በርባንን ወይስ ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን ማንኛውን ልፈታላችሁ ትወዳላችሁ? አላቸው፤
18Nes jis žinojo, kad Jėzų jie buvo išdavę iš pavydo.
18በቅንዓት አሳልፈው እንደ ሰጡት ያውቅ ነበርና።
19Sėdinčiam teismo krėsle Pilotui žmona atsiuntė įspėjimą: “Nieko nedaryk šitam teisiajam, nes šiąnakt sapne labai dėl Jo kentėjau”.
19እርሱም በፍርድ ወንበር ተቀምጦ ሳለ ሚስቱ። ስለ እርሱ ዛሬ በሕልም እጅግ መከራ ተቀብያለሁና በዚያ ጻድቅ ሰው ምንም አታድርግ ብላ ላከችበት።
20Bet aukštieji kunigai ir vyresnieji įtikino minią, kad prašytų paleisti Barabą, o Jėzų pražudytų.
20የካህናት አለቆችና ሽማግሎች ግን በርባንን እንዲለምኑ ኢየሱስን ግን እንዲያጠፉ ሕዝቡን አባበሉ።
21Tada valdytojas jiems tarė: “Kurį iš šių dviejų norite, kad jums paleisčiau?” Jie šaukė: “Barabą!”
21ገዢውም መልሶ። ከሁለቱ ማንኛውን ልፈታላችሁ ትወዳላችሁ? አላቸው፤ እነርሱም። በርባንን አሉ።
22Pilotas paklausė: “Ką gi man daryti su Jėzumi, kuris vadinamas Kristumi?” Jie visi rėkė: “Nukryžiuok Jį!”
22ጲላጦስ። ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን እንግዲህ ምን ላድርገው? አላቸው፤ ሁሉም። ይሰቀል አሉ።
23Jis klausė: “Ką bloga Jis padarė?” Bet jie dar garsiau šaukė: “Nukryžiuok Jį!”
23ገዢውም። ምን ነው? ያደረገው ክፋት ምንድር ነው? አለ፤ እነርሱ ግን። ይሰቀል እያሉ ጩኸት አበዙ።
24Pilotas, pamatęs, kad nieko nelaimi, o sąmyšis tik didėja, paėmė vandens, nusiplovė rankas minios akivaizdoje ir tarė: “Aš nekaltas dėl šio teisiojo kraujo. Jūs žinokitės!”
24ጲላጦስም ሁከት እንዲጀመር እንጂ አንዳች እንዳይረባ ባየ ጊዜ፥ ውኃ አንሥቶ። እኔ ከዚህ ጻድቅ ሰው ደም ንጹሕ ነኝ፤ እናንተ ተጠንቀቁ ሲል በሕዝቡ ፊት እጁን ታጠበ።
25Visi žmonės šaukė: “Jo kraujas tekrinta ant mūsų ir ant mūsų vaikų!”
25ሕዝቡም ሁሉ መልሰው። ደሙ በእኛና በልጆቻችን ላይ ይሁን አሉ።
26Tada jis paleido jiems Barabą, o Jėzų nuplakdinęs atidavė nukryžiuoti.
26በዚያን ጊዜ በርባንን ፈታላቸው፥ ኢየሱስን ግን ገርፎ ሊሰቀል አሳልፎ ሰጠ።
27Valdytojo kareiviai nusivedė Jėzų į pretorijų ir surinko aplink jį visą kuopą.
27በዚያን ጊዜ የገዢው ወታደሮች ኢየሱስን ወደ ገዢው ግቢ ውስጥ ወሰዱት ጭፍራውንም ሁሉ ወደ እርሱ አከማቹ።
28Jie išrengė Jį ir apsiautė raudonu apsiaustu.
28ልብሱንም ገፈው ቀይ ልብስ አለበሱት፥
29Nupynę erškėčių vainiką, uždėjo Jam ant galvos, o į Jo dešinę įspraudė nendrę. Po to tyčiodamiesi klūpčiojo prieš Jį ir sakė: “Sveikas, žydų karaliau!”
29ከእሾህም አክሊል ጎንጉነው በራሱ ላይ፥ በቀኝ እጁም መቃ አኖሩ፥ በፊቱም ተንበርክከው። የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን እያሉ ዘበቱበት፤
30Spjaudydami Jį, stvėrė iš Jo nendrę ir čaižė per galvą.
30ተፉበትም መቃውንም ይዘው ራሱን መቱት።
31Pasityčioję iš Jo, jie nusiautė apsiaustą, apvilko Jo paties drabužiais ir išsivedė nukryžiuoti.
31ከዘበቱበትም በኋላ ቀዩን ልብስ ገፈፉት፥ ልብሱንም አለበሱት ሊሰቅሉትም ወሰዱት።
32Išeidami jie sutiko žmogų iš Kirėnės, vardu Simoną. Tą privertė nešti Jėzaus kryžių.
32ሲወጡም ስምዖን የተባለው የቀሬናን ሰው አገኙ፤ እርሱንም መስቀሉን ይሸከም ዘንድ አስገደዱት።
33Atėję į vietą, vadinamą Golgota (tai yra: “Kaukolės vieta”),
33ትርጓሜው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሆን ጎልጎታ ወደሚባለው ስፍራ በደረሱ ጊዜም፥
34davė Jam gerti rūgštaus vyno, sumaišyto su tulžimi, bet Jėzus paragavęs negėrė.
34በሐሞት የተደባለቀ የወይን ጠጅ ሊጠጣ አቀረቡለት፤ ቀምሶም ሊጠጣው አልወደደም።
35Nukryžiavę Jį, pasidalijo Jo drabužius, mesdami burtą, kad išsipildytų, kas buvo per pranašą pasakyta: “Jie dalinosi mano drabužius ir dėl mano apdaro metė burtą”.
35ከሰቀሉትም በኋላ ልብሱን ዕጣ ጥለው ተካፈሉ፥
36Ir ten pat susėdę, saugojo Jį.
36በዚያም ተቀምጠው ይጠብቁት ነበር።
37Viršum Jo galvos jie prisegė užrašytą Jo kaltinimą: “Šitas yra Jėzus, žydų karalius”.
37ይህ ኢየሱስ የአይሁድ ንጉሥ ነው የሚል የክሱን ጽሕፈት ከራሱ በላይ አኖሩ።
38Kartu su Juo buvo nukryžiuoti du plėšikai, vienas iš dešinės, kitas iš kairės.
38በዚያን ጊዜ ሁለት ወንበዶች አንዱ በቀኝ አንዱም በግራ ከእርሱ ጋር ተሰቀሉ።
39Einantys pro šalį užgauliojo Jėzų, kraipydami galvas
39የሚያልፉትም ራሳቸውን እየነቀነቁ ይሰድቡት ነበርና።
40ir sakydami: “Še Tau, kuris sugriauni šventyklą ir per tris dienas atstatai; išgelbėk save! Jei esi Dievo Sūnus, nuženk nuo kryžiaus!”
40ቤተ መቅደስን የምታፈርስ በሦስት ቀንም የምትሠራው፥ ራስህን አድን፤ የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ ከመስቀል ውረድ አሉት።
41Taip pat tyčiojosi aukštieji kunigai su Rašto žinovais ir vyresniaisiais, kalbėdami:
41እንዲሁም ደግሞ የካህናት አለቆች ከጻፎችና ከሽማግሎች ጋር እየዘበቱበት እንዲህ አሉ።
42“Kitus išgelbėdavo, o pats negali išsigelbėti. Jeigu Jis Izraelio karalius, tenužengia dabar nuo kryžiaus, ir mes Juo tikėsime.
42ሌሎችን አዳነ፥ ራሱን ሊያድን አይችልም፤ የእስራኤል ንጉሥ ከሆነ፥ አሁን ከመስቀል ይውረድ እኛም እናምንበታለን።
43Jis pasitikėjo Dievu, tad teišvaduoja Tas dabar Jį, jeigu Jam Jo reikia, nes Jis sakė: ‘Aš Dievo Sūnus’ ”.
43በእግዚአብሔር ታምኖአል፤ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ብሎአልና ከወደደውስ አሁን ያድነው።
44Taip pat Jį užgauliojo ir kartu nukryžiuoti plėšikai.
44ከእርሱ ጋር የተሰቀሉት ወንበዶች ደግሞ ያንኑ እያሉ ይነቅፉት ነበር።
45Nuo šeštos iki devintos valandos visą kraštą gaubė tamsa.
45ከስድስት ሰዓትም ጀምሮ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ በምድር ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ።
46O apie devintą valandą Jėzus sušuko garsiu balsu: “Elí, Elí, lemá sabachtáni?”, tai reiškia: “Mano Dieve, mano Dieve, kodėl mane palikai?!”
46በዘጠኝ ሰዓትም ኢየሱስ። ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ? ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህም። አምላኬ አምላኬ፥ ስለ ምን ተውኸኝ? ማለት ነው።
47Kai kurie iš ten stovėjusiųjų, tai išgirdę, sakė: “Jis šaukiasi Elijo”.
47በዚያም ከቆሙት ሰዎች ሰምተው። ይህስ ኤልያስን ይጠራል አሉ።
48Ir tuoj vienas iš jų pribėgęs paėmė kempinę, primirkė ją rūgštaus vyno, užmovė ant nendrės ir padavė Jam gerti.
48ወዲያውም ከእነርሱ አንዱ ሮጠ፤ ሰፍነግም ይዞ ሆምጣጤ ሞላበት፥ በመቃም አድርጎ አጠጣው።
49Kiti kalbėjo: “Liaukis! Pažiūrėsim, ar ateis Elijas Jo išgelbėti”.
49ሌሎቹ ግን። ተው፥ ኤልያስ መጥቶ ያድነው እንደ ሆነ እንይ አሉ።
50Tada Jėzus, dar kartą sušukęs garsiu balsu, atidavė dvasią.
50ኢየሱስም ሁለተኛ በታላቅ ድምፅ ጮኾ ነፍሱን ተወ።
51Ir štai šventyklos uždanga perplyšo pusiau nuo viršaus iki apačios, ir žemė sudrebėjo, ir uolos ėmė skeldėti.
51እነሆም፥ የቤተ መቅደስ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ከሁለት ተቀደደ፥ ምድርም ተናወጠች፥ ዓለቶችም ተሰነጠቁ፤
52Atsidarė kapai, ir daug užmigusių šventųjų kūnų prisikėlė.
52መቃብሮችም ተከፈቱ፥ ተኝተው ከነበሩትም ከቅዱሳን ብዙ ሥጋዎች ተነሡ፤
53Išėję iš kapų po Jo prisikėlimo, jie atėjo į šventąjį miestą ir daug kam pasirodė.
53ከትንሣኤውም በኋላ ከመቃብሮች ወጥተው ወደ ቅድስት ከተማ ገቡና ለብዙዎች ታዩ።
54Šimtininkas ir kiti su juo saugojantys Jėzų, pamatę žemės drebėjimą ir visa, kas dėjosi, labai išsigando ir sakė: “Tikrai šitas buvo Dievo Sūnus!”
54የመቶ አለቃም ከእርሱም ጋር ኢየሱስን የሚጠብቁ መናወጡንና የሆነውን ነገር አይተው። ይህ በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነበረ ብለው እጅግ ፈሩ።
55Tenai buvo daug moterų, kurios žiūrėjo iš tolo. Jos sekė paskui Jėzų nuo Galilėjos, Jam tarnaudamos.
55ኢየሱስን እያገለገሉ ከገሊላ የተከተሉት ብዙ ሴቶች በሩቅ ሆነው ሲመለከቱ በዚያ ነበሩ፤
56Tarp jų buvo Marija Magdalietė, Jokūbo ir Jozės motina Marija ir Zebediejaus sūnų motina.
56ከእነርሱም መግደላዊት ማርያምና የያዕቆብና የዮሳ እናት ማርያም የዘብዴዎስም የልጆቹ እናት ነበሩ።
57Vakarui atėjus, atvyko vienas turtingas žmogus iš Arimatėjos, vardu Juozapas, kuris irgi buvo tapęs Jėzaus mokiniu.
57በመሸም ጊዜ ዮሴፍ የተባለው ባለ ጠጋ ሰው ከአርማትያስ መጣ፥ እርሱም ደግሞ የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ነበረ፤
58Jis nuėjo pas Pilotą ir paprašė Jėzaus kūno. Pilotas įsakė kūną atiduoti.
58ይኸውም ወደ ጲላጦስ ቀርቦ የኢየሱስን ሥጋ ለመነው።
59Juozapas paėmė kūną, įvyniojo į švarią drobulę
59ጲላጦስም እንዲሰጡት አዘዘ። ዮሴፍም ሥጋውን ይዞ በንጹሕ በፍታ ከፈነው፥
60ir paguldė savo naujame kape, kurį buvo išsikaldinęs uoloje. Užritęs didelį akmenį ant kapo angos, nuėjo.
60ከዓለት በወቀረው በአዲሱ መቃብርም አኖረው፥ በመቃብሩም ደጃፍ ታላቅ ድንጋይ አንከባሎ ሄደ።
61Ten buvo Marija Magdalietė ir kita Marija, kurios sėdėjo priešais kapą.
61መግደላዊት ማርያምም ሁለተኛይቱም ማርያም በመቃብሩ አንጻር ተቀምጠው በዚያ ነበሩ።
62Kitą dieną, po Prisirengimo dienos, susirinko pas Pilotą aukštieji kunigai bei fariziejai
62በማግሥቱም ከመዘጋጀት በኋላ በሚሆነው ቀን፥ የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን ወደ ጲላጦስ ተሰበሰቡና።
63ir kalbėjo: “Valdove, mes prisimename, jog tas suvedžiotojas, dar gyvas būdamas, sakė: ‘Po trijų dienų prisikelsiu’.
63ጌታ ሆይ፥ ያ አሳች በሕይወቱ ገና ሳለ። ከሦስት ቀን በኋላ እነሣለሁ እንዳለ ትዝ አለን።
64Įsakyk tad saugoti kapą iki trečios dienos, kad kartais nakčia atėję Jo mokiniai nepavogtų Jo ir nepaskelbtų žmonėms: ‘Jis prisikėlė iš numirusių’. Pastaroji apgavystė būtų blogesnė už pirmąją”.
64እንግዲህ ደቀ መዛሙርቱ መጥተው በሌሊት እንዳይሰርቁት ለሕዝቡም። ከሙታን ተነሣ እንዳይሉ፥ የኋለኛይቱ ስሕተት ከፊተኛይቱ ይልቅ የከፋች ትሆናለችና መቃብሩ እስከ ሦስተኛ ቀን ድረስ እንዲጠበቅ እዘዝ አሉት።
65Pilotas jiems atsakė: “Štai jums sargybaeikite ir saugokite, kaip išmanote”.
65ጲላጦስም። ጠባቆች አሉአችሁ፤ ሄዳችሁ እንዳወቃችሁ አስጠብቁ አላቸው።
66Jie nuėjo, pastatė prie kapo sargybą ir paženklino antspaudu akmenį.
66እነርሱም ሄደው ከጠባቆች ጋር ድንጋዩን አትመው መቃብሩን አስጠበቁ።