1Baigęs visa tai kalbėti, Jėzus tarė savo mokiniams:
1ኢየሱስም እነዚህን ቃሎች ሁሉ በፈጸመ ጊዜ፥
2“Jūs žinote, kad po dviejų dienų bus Pascha, ir Žmogaus Sūnus bus atiduotas nukryžiuoti”.
2ለደቀ መዛሙርቱ። ከሁለት ቀን በኋላ ፋሲካ እንዲሆን ታውቃላችሁ፥ የሰው ልጅም ሊሰቀል አልፎ ይሰጣል አለ።
3Tuomet aukštieji kunigai, Rašto žinovai bei tautos vyresnieji susirinko į vyriausiojo kunigo Kajafo rūmus
3በዚያን ጊዜ የካህናት አለቆች የሕዝብም ሽማግሎች ቀያፋ በሚባለው በሊቀ ካህናቱ ግቢ ተሰበሰቡ፥
4ir nusprendė suimti Jėzų klasta ir Jį nužudyti.
4ኢየሱስንም በተንኰል ሊያስይዙት ሊገድሉትም ተማከሩ፤
5Bet jie sakė: “Tik ne per šventes, kad žmonėse nekiltų sąmyšio”.
5ነገር ግን። በሕዝቡ ዘንድ ሁከት እንዳይነሣ በበዓል አይሁን አሉ።
6Kai Jėzus buvo Betanijoje, Simono Raupsuotojo namuose,
6ኢየሱስም በቢታንያ በለምጻሙ በስምዖን ቤት ሳለ፥
7atėjo moteris su alebastriniu labai brangaus kvapiojo aliejaus indu ir Jam sėdinčiam prie stalo išpylė ant galvos.
7አንዲት ሴት ዋጋው እጅግ የበዛ ሽቱ የሞላው የአልባስጥሮስ ብልቃጥ ይዛ ወደ እርሱ ቀረበች በማዕድም ተቀምጦ ሳለ በራሱ ላይ አፈሰሰችው።
8Tai pamatę, mokiniai pasipiktino ir kalbėjo: “Kam toks eikvojimas?
8ደቀ መዛሙርቱም ይህን አይተው ተቈጡና። ይህ ጥፋት ለምንድር ነው?
9Juk buvo galima aliejų brangiai parduoti ir išdalyti pinigus vargšams”.
9ይህ በብዙ ዋጋ ተሽጦ ለድሆች ሊሰጥ ይቻል ነበርና አሉ።
10Tai sužinojęs, Jėzus tarė: “Kam skaudinate moterį? Ji man padarė gerą darbą!
10ኢየሱስም ይህን አውቆ እንዲህ አላቸው። መልካም ሥራ ሠርታልኛለችና ሴቲቱንስ ስለ ምን ታደክሙአታላችሁ?
11Vargšų jūs visuomet turite su savimi, o mane ne visuomet turėsite.
11ድሆች ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ይኖራሉና፥ እኔ ግን ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር አልኖርም፤
12Išpildama aliejų ant mano kūno, ji tai padarė mano laidotuvėms.
12እርስዋ ይህን ሽቱ በሰውነቴ ላይ አፍስሳ ለመቃብሬ አደረገች።
13Iš tiesų sakau jums: visame pasaulyje, kur tik bus skelbiama ši Evangelija, jos atminimui bus pasakojama ir tai, ką ji padarė”.
13እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ወንጌል በዓለም ሁሉ በማናቸውም ስፍራ በሚሰበክበት እርስዋ ያደረገችው ደግሞ ለእርስዋ መታሰቢያ እንዲሆን ይነገራል።
14Tada vienas iš dvylikos, vardu Judas Iskarijotas, nuėjo pas aukštuosius kunigus
14በዚያን ጊዜ የአስቆሮቱ ይሁዳ የሚባለው ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ወደ ካህናት አለቆች ሄዶ።
15ir tarė: “Ką man duosite, jeigu Jį jums išduosiu?” Tie suderėjo su juo trisdešimt sidabrinių.
15ምን ልትሰጡኝ ትወዳላችሁ እኔም አሳልፌ እሰጣችኋለሁ? እነርሱም ሠላሳ ብር መዘኑለት።
16Ir nuo to laiko jis ieškojo progos išduoti Jį.
16ከዚያችም ሰዓት ጀምሮ አሳልፎ ሊሰጠው ምቹ ጊዜ ይሻ ነበር።
17Pirmąją Neraugintos duonos dieną mokiniai priėjo prie Jėzaus ir paklausė: “Kur nori, kad Tau paruoštume valgyti Paschą?”
17በቂጣው በዓል በመጀመሪያ ቀን ደቀ መዛሙርቱ ወደ ኢየሱስ ቀርበው። ፋሲካን ትበላ ዘንድ ወዴት ልናሰናዳልህ ትወዳለህ አሉት።
18Jis atsakė: “Eikite į miestą pas tokį žmogų ir sakykite jam: ‘Mokytojas sako: Mano metas arti. Pas tave švęsiu Paschą su savo mokiniais’ ”.
18እርሱም። ወደ ከተማ ከእገሌ ዘንድ ሄዳችሁ። መምህር። ጊዜዬ ቀርቦአል፤ ከደቀ መዛሙርቴ ጋር ከአንተ ዘንድ ፋሲካን አደርጋለሁ ይላል በሉት አለ።
19Mokiniai padarė, kaip Jėzus nurodė, ir paruošė Paschą.
19ደቀ መዛሙርቱም ኢየሱስ እንዳዘዛቸው አደረጉ ፋሲካንም አሰናዱ።
20Atėjus vakarui, Jėzus su dvylika sėdosi prie stalo.
20በመሸም ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርቱ ጋር በማዕድ ተቀመጠ።
21Jiems bevalgant, Jėzus tarė: “Iš tiesų sakau jums: vienas iš jūsų mane išduos”.
21ሲበሉም። እውነት እላችኋለሁ፥ ከእናንተ አንዱ እኔን አሳልፎ ይሰጣል አለ።
22Jie labai nuliūdo ir kiekvienas klausė Jo: “Nejaugi aš, Viešpatie?”
22እጅግም አዝነው እያንዳንዱ። ጌታ ሆይ፥ እኔ እሆንን? ይሉት ጀመር።
23Jis atsakė: “Mane išduos dažantis kartu su manim duoną dubenyje.
23እርሱም መልሶ። ከእኔ ጋር እጁን በወጭቱ ያጠለቀ፥ እኔን አሳልፎ የሚሰጥ እርሱ ነው።
24Žmogaus Sūnus, tiesa, eina, kaip apie Jį parašyta, bet vargas tam žmogui, per kurį Žmogaus Sūnus išduodamas. Geriau būtų buvę tam žmogui negimti”.
24የሰው ልጅስ ስለ እርሱ እንደ ተጻፈ ይሄዳል፥ ነገር ግን የሰው ልጅ አልፎ ለሚሰጥበት ለዚያ ሰው ወዮለት፤ ያ ሰው ባልተወለደ ይሻለው ነበር አለ።
25Jo išdavėjas Judas paklausė: “Nejaugi aš, Rabi?!” Jis atsakė: “Tu pasakei”.
25አሳልፎ የሚሰጠው ይሁዳም መልሶ። መምህር ሆይ፥ እኔ እሆንን? አለ፤ አንተ አልህ አለው።
26Kai jie valgė, Jėzus paėmė duoną, palaimino, laužė ją ir davė mokiniams, sakydamas: “Imkite ir valgykite: tai yra mano kūnas”.
26ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና። እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው አለ።
27Po to paėmė taurę, padėkojo ir davė jiems, tardamas: “Gerkite iš jos visi,
27ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው እንዲህም አለ። ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤
28nes tai yra mano kraujas, Naujosios Sandoros kraujas, kuris už daugelį išliejamas nuodėmėms atleisti.
28ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው።
29Ir sakau jums: nuo šiol nebegersiu šito vynmedžio vaisiaus iki tos dienos, kada su jumis gersiu jį naują savo Tėvo karalystėje”.
29ነገር ግን እላችኋለሁ፥ በአባቴ መንግሥት ከእናንተ ጋር ከዚህ ከወይን ፍሬ አዲሱን እስከምጠጣበት እስከዚያ ቀን ድረስ ከዛሬ ጀምሬ አልጠጣውም።
30Pagiedoję himną, jie išėjo į Alyvų kalną.
30መዝሙርም ከዘመሩ በኋላ ወደ ደብረ ዘይት ወጡ።
31Tada Jėzus jiems kalbėjo: “Šią naktį jūs visi manimi pasipiktinsite, nes parašyta: ‘Ištiksiu piemenį, ir kaimenės avys išsisklaidys’.
31በዚያን ጊዜ ኢየሱስ። በዚች ሌሊት ሁላችሁ በእኔ ትሰናከላላችሁ፤ እረኛውን እመታለሁ የመንጋውም በጎች ይበተናሉ የሚል ተጽፎአልና፤
32Bet kai prisikelsiu, Aš pirma jūsų nueisiu į Galilėją”.
32ከተነሣሁ በኋላ ግን ወደ ገሊላ እቀድማችኋለሁ አላቸው።
33Petras atsiliepė: “Jei net visi Tavimi pasipiktins, aš niekuomet nepasipiktinsiu!”
33ጴጥሮስም መልሶ። ሁሉም በአንተ ቢሰናከሉ እኔ ከቶ አልሰናከልም አለው።
34Jėzus jam tarė: “Iš tiesų sakau tau: šią naktį, dar gaidžiui nepragydus, tu tris kartus manęs išsiginsi”.
34ኢየሱስ። እውነት እልሃለሁ፥ በዚች ሌሊት ዶሮ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ አለው።
35Bet Petras tvirtino: “Jei man reikėtų net mirti kartu su Tavimi, aš vis tiek Tavęs neišsiginsiu!” Taip kalbėjo ir visi mokiniai.
35ጴጥሮስ። ከአንተ ጋር መሞት እንኳ የሚያስፈልገኝ ቢሆን፥ ከቶ አልክድህም አለው። ደቀ መዛሙርቱ ሁሉ ደግሞ እንደዚሁ አሉ።
36Tuomet Jėzus su jais atėjo į vietą, vadinamą Getsemane, ir tarė mokiniams: “Pasėdėkite čia, kol Aš ten nuėjęs melsiuos”.
36በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ከእነርሱ ጋር ጌቴሴማኒ ወደምትባል ስፍራ መጣ ደቀ መዛሙርቱንም። ወዲያ ሄጄ ስጸልይ ሳለ በዚህ ተቀመጡ አላቸው።
37Pasiėmęs Petrą ir abu Zebediejaus sūnus, pradėjo liūdėti ir sielvartauti.
37ጴጥሮስንም ሁለቱንም የዘብዴዎስን ልጆች ወስዶ ሊያዝን ሊተክዝም ጀመር።
38Tada tarė jiems: “Mano siela mirtinai nuliūdusi. Likite čia ir budėkite su manimi”.
38ነፍሴ እስከ ሞት ድረስ እጅግ አዘነች፤ በዚህ ቆዩ ከእኔም ጋር ትጉ አላቸው።
39Paėjęs kiek toliau, Jėzus parpuolė veidu į žemę ir meldėsi: “Mano Tėve, jeigu įmanoma, teaplenkia mane ši taurė. Tačiau ne kaip Aš noriu, bet kaip Tu!”
39ጥቂትም ወደ ፊት እልፍ ብሎ በፊቱ ወደቀና ሲጸልይ። አባቴ፥ ቢቻልስ፥ ይህች ጽዋ ከእኔ ትለፍ፤ ነገር ግን አንተ እንደምትወድ ይሁን እንጂ እኔ እንደምወድ አይሁን አለ።
40Jis sugrįžo pas mokinius ir, radęs juos miegančius, tarė Petrui: “Nepajėgėte nė vienos valandos pabudėti su manimi?
40ወደ ደቀ መዛሙርቱም መጣ፤ ተኝተውም አገኛቸውና ጴጥሮስን። እንዲሁም ከእኔ ጋር አንዲት ሰዓት እንኳ ልትተጉ አልቻላችሁምን?
41Budėkite ir melskitės, kad nepatektumėte į pagundymą. Dvasia ryžtinga, bet kūnas silpnas”.
41ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ፤ መንፈስስ ተዘጋጅታለች ሥጋ ግን ደካማ ነው አለው።
42Ir vėl nuėjęs antrą kartą, meldėsi: “Mano Tėve, jei ši taurė negali praeiti mano negerta, tebūnie Tavo valia!”
42ደግሞ ሁለተኛ ሄዶ ጸለየና። አባቴ፥ ይህች ጽዋ ሳልጠጣት ታልፍ ዘንድ የማይቻል እንደ ሆነ፥ ፈቃድህ ትሁን አለ።
43Sugrįžęs vėl rado juos miegančius, nes jų akys buvo apsunkusios.
43ደግሞም መጥቶ ዓይኖቻቸው በእንቅልፍ ከብደው ነበርና ተኝተው አገኛቸው።
44Tada, palikęs juos, vėl nuėjo ir trečią kartą meldėsi tais pačiais žodžiais.
44ደግሞም ትቶአቸው ሄደ፥ ሦስተኛም ያንኑ ቃል ደግሞ ጸለየ።
45Paskui grįžo pas mokinius ir tarė: “Jūs vis dar miegate ir ilsitės... Štai atėjo valanda, ir Žmogaus Sūnus išduodamas į nusidėjėlių rankas.
45ከዚያ ወዲያ ወደ ደቀ መዛሙርቱ መጥቶ። እንግዲህስ ተኙ ዕረፉም፤ እነሆ፥ ሰዓቲቱ ቀርባለች የሰው ልጅም በኃጢአተኞች እጅ አልፎ ይሰጣል።
46Kelkitės, eime! Štai mano išdavėjas čia pat”.
46ተነሡ፥ እንሂድ፤ እነሆ፥ አሳልፎ የሚሰጠኝ ቀርቦአል አላቸው።
47Dar Jam tebekalbant, štai pasirodė Judas, vienas iš dvylikos, o su juo didelė minia, ginkluota kalavijais ir vėzdais, pasiųsta aukštųjų kunigų ir tautos vyresniųjų.
47ይህንም ገና ሲናገር፥ እነሆ፥ ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ይሁዳ መጣ፥ ከእርሱም ጋር ብዙ ሕዝብ ሰይፍና ጐመድ ይዘው ከካህናት አለቆችና ከሕዝቡ ሽማግሎች ዘንድ መጡ።
48Jo išdavėjas nurodė jiems ženklą, sakydamas: “Kurį pabučiuosiu, tai Tas! Suimkite Jį!”
48አሳልፎ የሚሰጠውም። የምስመው እርሱ ነው፤ ያዙት ብሎ ምልክት ሰጥቶአቸው ነበር።
49Ir tuojau priėjęs prie Jėzaus, tarė: “Sveikas, Rabi!”, ir pabučiavo Jį.
49ወዲያውም ወደ ኢየሱስ ቀረበና። መምህር ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን ብሎ ሳመው።
50O Jėzus jam tarė: “Bičiuli, ko atėjai?” Tada jie priėjo, čiupo Jėzų rankomis ir suėmė.
50ኢየሱስም። ወዳጄ ሆይ፥ ለምን ነገር መጣህ? አለው። በዚያን ጊዜ ቀረቡ እጃቸውንም በኢየሱስ ላይ ጭነው ያዙት።
51Ir štai vienas iš buvusių su Jėzumi ištiesė ranką, išsitraukė kalaviją, puolė vyriausiojo kunigo tarną ir nukirto jam ausį.
51እነሆም፥ ከኢየሱስ ጋር ከነበሩት አንዱ እጁን ዘርግቶ ሰይፉን መዘዘና የሊቀ ካህናቱን ባሪያ መትቶ ጆሮውን ቈረጠው።
52Tuomet Jėzus jam tarė: “Kišk kalaviją atgal, kur buvo, nes visi, kurie griebiasi kalavijo, nuo kalavijo ir žus.
52በዚያን ጊዜ ኢየሱስ እንዲህ አለው። ሰይፍ የሚያነሡ ሁሉ በሰይፍ ይጠፋሉና ሰይፍህን ወደ ስፍራው መልስ።
53O gal manai, jog negaliu paprašyti savo Tėvą ir Jis bematant neatsiųstų man daugiau kaip dvylika legionų angelų?
53ወይስ አባቴን እንድለምን እርሱም አሁን ከአሥራ ሁለት ጭፍሮች የሚበዙ መላእክት እንዲሰድልኝ የማይቻል ይመስልሃልን?
54Bet kaip tada išsipildytų Raštai, kad šitaip turi įvykti?!”
54እንዲህ ከሆነስ። እንደዚህ ሊሆን ይገባል የሚሉ መጻሕፍት እንዴት ይፈጸማሉ?
55Tą valandą Jėzus tarė miniai: “Kaip prieš plėšiką išėjote su kalavijais ir vėzdais suimti mane. Aš kasdien sėdėjau šventykloje su jumis ir mokiau, ir manęs nesuėmėte.
55በዚያን ሰዓት ኢየሱስ ለሕዝቡ። ወንበዴን እንደምትይዙ ሰይፍና ጐመድ ይዛችሁ ልትይዙኝ ወጣችሁን? በመቅደስ ዕለት ዕለት እያስተማርሁ ከእናንተ ጋር ስቀመጥ ሳለሁ አልያዛችሁኝም።
56Bet viskas šitaip įvyko, kad išsipildytų pranašų Raštai”. Tada visi mokiniai paliko Jį ir pabėgo.
56ነገር ግን ይህ ሁሉ የሆነ የነቢያት መጻሕፍት ይፈጸሙ ዘንድ ነው አለ። በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ሁሉ ትተውት ሸሹ።
57Tie, kurie suėmė Jėzų, nuvedė Jį pas vyriausiąjį kunigą Kajafą, kur buvo susirinkę Rašto žinovai ir vyresnieji.
57ኢየሱስን የያዙትም ጻፎችና ሽማግሎች ወደ ተከማቹበት ወደ ሊቀ ካህናቱ ወደ ቀያፋ ወሰዱት።
58O Petras sekė Jį iš tolo iki vyriausiojo kunigo rūmų kiemo ir įėjęs atsisėdo su tarnais pasižiūrėti, kaip viskas baigsis.
58ጴጥሮስ ግን እስከ ሊቀ ካህናቱ ግቢ ድረስ ሩቅ ሆኖ ተከተለው፥ የነገሩንም ፍጻሜ ያይ ዘንድ ወደ ውስጥ ገብቶ ከሎሌዎቹ ጋር ተቀመጠ።
59Tuo tarpu aukštieji kunigai, vyresnieji ir visas sinedrionas ieškojo melagingo parodymo prieš Jėzų, kad galėtų Jį nuteisti mirti,
59የካህናት አለቆችና ሽማግሎች ሸንጐውም ሁሉ እንዲገድሉት በኢየሱስ ላይ የሐሰት ምስክር ይፈልጉ ነበር፥ አላገኙም፤
60tačiau nerado, nors buvo išėję į priekį daug melagingų liudytojų. Pagaliau išėjo priekin du
60ብዙም የሐሰት ምስክሮች ምንም ቢቀርቡ አላገኙም።
61ir tarė: “Šitas sakė: ‘Aš galiu sugriauti Dievo šventyklą ir per tris dienas ją atstatyti’ ”.
61በኋላም ሁለት ቀርበው። ይህ ሰው። የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ አፍርሼ በሦስት ቀን ልሠራው እችላለሁ ብሎአል አሉ።
62Tada atsistojo vyriausiasis kunigas ir paklausė Jėzų: “Tu nieko neatsakai į šituos kaltinimus?!”
62ሊቀ ካህናቱም ተነሥቶ። እነዚህ ለሚመሰክሩብህ አንድ ስንኳ አትመልስምን? አለው።
63Bet Jėzus tylėjo. Tuomet vyriausiasis kunigas Jam tarė: “Prisaikdinu Tave gyvuoju Dievu, kad mums pasakytum, ar Tu esi Kristus, Dievo Sūnus?!”
63ኢየሱስ ግን ዝም አለ። ሊቀ ካህናቱም። አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ የሆንህ እንደ ሆነ እንድትነግረን በሕያው እግዚአብሔር አምልሃለሁ አለው።
64Jėzus atsakė: “Taip yra, kaip sakai. Bet Aš jums sakau: nuo šiol jūs matysite Žmogaus Sūnų, sėdintį Galybės dešinėje ir ateinantį dangaus debesyse!”
64ኢየሱስም። አንተ አልህ ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ከእንግዲህ ወዲህ የሰው ልጅ በኃይል ቀኝ ሲቀመጥ በሰማይም ደመና ሲመጣ ታያላችሁ አለው።
65Tada vyriausiasis kunigas persiplėšė drabužius ir sušuko: “Jis piktžodžiauja! Kam dar mums liudytojai?! Štai girdėjote Jo piktžodžiavimą.
65በዚያን ጊዜ ሊቀ ካህናቱ ልብሱን ቀዶ። ተሳድቦአል እንግዲህ ወዲህ ምስክሮች ስለ ምን ያስፈልገናል? እነሆ፥ ስድቡን አሁን ሰምታችኋል፤ ምን ይመስላችኋል? አለ።
66Kaip jums atrodo?” Jie atsakė: “Vertas mirties!”
66እነርሱም። ሞት ይገባዋል ብለው መለሱ።
67Tada jie ėmė spjaudyti Jam į veidą ir daužyti Jį kumščiais. Kiti mušė Jį per veidą,
67በዚያን ጊዜ በፊቱ ተፉበት፤ ጐሰሙትም፥ ሌሎችም በጥፊ መትተው። ክርስቶስ ሆይ፥ በጥፊ የመታህ ማን ነው?
68sakydami: “Pranašauk mums, Kristau! Kas Tau smogė?”
68ትንቢት ተናገርልን አሉ።
69Tuo metu Petras sėdėjo kieme. Viena tarnaitė priėjo prie jo ir tarė: “Ir tu buvai su Jėzumi Galilėjiečiu”.
69ጴጥሮስም ከቤት ውጭ በአጥሩ ግቢ ተቀምጦ ነበር፤ አንዲት ገረድም ወደ እርሱ ቀርባ። አንተ ደግሞ ከገሊላው ከኢየሱስ ጋር ነበርህ አለችው።
70Bet jis išsigynė visų akivaizdoje: “Aš nežinau, ką tu sakai”.
70እርሱ ግን። የምትዪውን አላውቀውም ብሎ በሁሉ ፊት ካደ።
71Einantį vartų link, jį pastebėjo kita tarnaitė ir kalbėjo aplinkiniams: “Šitas buvo su Jėzumi Nazariečiu”.
71ወደ በሩም ሲወጣ ሌላይቱ አየችውና በዚያ ላሉት። ይህ ደግሞ ከናዝሬቱ ከኢየሱስ ጋር ነበረ አለች።
72Jis ir vėl išsigynė, prisiekdamas: “Aš nepažįstu to žmogaus!”
72ዳግመኛም ሲምል። ሰውየውን አላውቀውም ብሎ ካደ።
73Po kiek laiko priėjo ten stovėjusieji ir sakė Petrui: “Tikrai tu vienas iš jų, nes tavo tarmė tave išduoda”.
73ጥቂትም ቈይተው በዚያ ቆመው የነበሩ ቀርበው ጴጥሮስን። አነጋገርህ ይገልጥሃልና በእውነት አንተ ደግሞ ከእነርሱ ወገን ነህ አሉት።
74Tada jis ėmė keiktis ir prisiekinėti: “Aš nepažįstu to žmogaus!” Ir tuojau pragydo gaidys.
74በዚያን ጊዜ። ሰውየውን አላውቀውም ብሎ ሊራገምና ሊምል ጀመረ። ወዲያውም ዶሮ ጮኸ።
75Petras prisiminė Jėzaus žodžius: “Dar gaidžiui nepragydus, tu tris kartus manęs išsiginsi”. Jis išėjo laukan ir karčiai verkė.
75ጴጥሮስም። ዶሮ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ ያለው የኢየሱስ ቃል ትዝ አለው፤ ወደ ውጭም ወጥቶ መራራ ልቅሶ አለቀሰ።