1“Tada su dangaus karalyste bus panašiai kaip su dešimtimi mergaičių, kurios, pasiėmusios savo žibintus, išėjo pasitikti jaunikio.
1በዚያን ጊዜ መንግሥተ ሰማያት መብራታቸውን ይዘው ሙሽራውን ሊቀበሉ የወጡ አሥር ቆነጃጅትን ትመስላለች።
2Penkios iš jų buvo protingos ir penkios kvailos.
2ከእነርሱም አምስቱ ሰነፎች አምስቱም ልባሞች ነበሩ።
3Kvailosios pasiėmė žibintus, bet nepasiėmė aliejaus.
3ሰነፎቹ መብራታቸውን ይዘው ከእነርሱ ጋር ዘይት አልያዙምና፤
4Protingosios kartu su žibintais pasiėmė induose ir aliejaus.
4ልባሞቹ ግን ከመብራታቸው ጋር በማሰሮአቸው ዘይት ያዙ።
5Jaunikiui vėluojant, visos pradėjo snausti ir užmigo.
5ሙሽራውም በዘገየ ጊዜ ሁሉ እንቅልፍ እንቅልፍ አላቸውና ተኙ።
6Vidurnaktį pasigirdo šauksmas: ‘Štai jaunikis ateina! Išeikite jo pasitikti!’
6እኩል ሌሊትም ሲሆን። እነሆ፥ ሙሽራው ይመጣል፥ ትቀበሉት ዘንድ ውጡ የሚል ውካታ ሆነ።
7Tada visos mergaitės atsikėlė ir taisėsi žibintus.
7በዚያን ጊዜ እነዚያ ቆነጃጅት ሁሉ ተነሡና መብራታቸውን አዘጋጁ።
8Kvailosios prašė protingųjų: ‘Duokite mums savo aliejaus, nes mūsų žibintai gęsta!’
8ሰነፎቹም ልባሞቹን። መብራታችን ሊጠፋብን ነው፤ ከዘይታችሁ ስጡን አሉአቸው።
9Protingosios atsakė: ‘Kad kartais nepristigtų ir mums, ir jums, verčiau eikite pas pardavėjus ir nusipirkite’.
9ልባሞቹ ግን መልሰው። ምናልባት ለእኛና ለእናንተ ባይበቃስ፤ ይልቅስ ወደሚሸጡት ሄዳችሁ ለራሳችሁ ግዙ አሉአቸው።
10Joms beeinant pirkti, atėjo jaunikis. Kurios buvo pasiruošusios, įėjo kartu su juo į vestuves, ir durys buvo uždarytos.
10ሊገዙም በሄዱ ጊዜ ሙሽራው መጣ፥ ተዘጋጅተው የነበሩትም ከእርሱ ጋር ወደ ሰርግ ገቡ፥ ደጁም ተዘጋ።
11Vėliau atėjo ir anos mergaitės ir ėmė prašyti: ‘Viešpatie, viešpatie, atidaryk mums!’
11በኋላም ደግሞ የቀሩቱ ቈነጃጅት መጡና። ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ፥ ክፈትልን አሉ።
12O jis atsakė: ‘Iš tiesų sakau jums: aš jūsų nepažįstu!’
12እርሱ ግን መልሶ። እውነት እላችኋለሁ፥ አላውቃችሁም አለ።
13Taigi budėkite, nes nežinote nei dienos, nei valandos, kurią Žmogaus Sūnus ateis”.
13ቀኒቱንና ሰዓቲቱን አታውቁምና እንግዲህ ንቁ።
14“Bus taip, kaip atsitiko žmogui, kuris, iškeliaudamas į tolimą šalį, pasišaukė savo tarnus ir patikėjo jiems savo turtą.
14ወደ ሌላ አገር የሚሄድ ሰው ባሮቹን ጠርቶ ያለውን ገንዘብ እንደ ሰጣቸው እንዲሁ ይሆናልና፤
15Vienam jis davė penkis talentus, kitam du, trečiam vienąkiekvienam pagal jo gabumusir tuojau iškeliavo.
15ለእያንዳንዱ እንደ ዓቅሙ፥ ለአንዱ አምስት መክሊት ለአንዱ ሁለት ለአንዱም አንድ ሰጠና ወደ ሌላ አገር ወዲያው ሄደ።
16Tas, kuris gavo penkis talentus, nuėjęs ėmė su jais verstis ir pelnė kitus penkis.
16አምስት መክሊትም የተቀበለው ሄዶ ነገደበት ሌላም አምስት አተረፈ፤
17Taip pat tas, kuris gavo du talentus, pelnė kitus du.
17እንዲሁም ሁለት የተቀበለው ሌላ ሁለት አተረፈ።
18O kuris gavo vieną, nuėjo, iškasė duobę ir paslėpė šeimininko pinigus.
18አንድ የተቀበለው ግን ሄዶ ምድርን ቈፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ።
19Praėjus nemaža laiko, tų tarnų šeimininkas grįžo ir pradėjo daryti su jais apyskaitą.
19ከብዙ ዘመንም በኋላ የእነዚያ ባሮች ጌታ መጣና ተቆጣጠራቸው።
20Atėjo tas, kuris buvo gavęs penkis talentus; jis atnešė kitus penkis ir tarė: ‘Šeimininke, davei man penkis talentus, štai aš pelniau kitus penkis’.
20አምስት መክሊት የተቀበለውም ቀረበና ሌላ አምስት መክሊት አስረክቦ። ጌታ ሆይ፥ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ፥ ሌላ አምስት መክሊት አተረፍሁበት አለ።
21Jo šeimininkas atsakė: ‘Gerai, šaunusis ir ištikimasis tarne! Kadangi buvai ištikimas mažuose dalykuose, pavesiu tau didelius. Eikš į savo šeimininko džiaugsmą!’
21ጌታውም። መልካም፥ አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው።
22Taip pat tas, kuris buvo gavęs du talentus, atėjęs pasakė: ‘Šeimininke, davei man du talentus, štai aš pelniau kitus du’.
22ሁለት መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ። ጌታ ሆይ፥ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ፥ ሌላ ሁለት መክሊት አተረፍሁበት አለ።
23Jo šeimininkas tarė: ‘Gerai, šaunusis ir ištikimasis tarne! Kadangi buvai ištikimas mažuose dalykuose, pavesiu tau didelius. Eikš į savo šeimininko džiaugsmą!’
23ጌታውም። መልካም፥ አንተ በጎ፥ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፥ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው።
24Priėjęs tas, kuris buvo gavęs vieną talentą, sakė: ‘Šeimininke, aš žinojau, kad tužmogus kietas: pjauni, kur nesėjai, ir renki, kur nebarstei.
24አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ። ጌታ ሆይ፥ ካልዘራህባት የምታጭድ ካልበተንህባትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤
25Pabijojęs nuėjau ir paslėpiau tavo talentą žemėje. Še, turėk, kas tavo’.
25ፈራሁም ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት፤ እነሆ፥ መክሊትህ አለህ አለ።
26Jo šeimininkas jam atsakė: ‘Blogasis tarne, tinginy! Tu žinojai, kad aš pjaunu, kur nesėjau, ir renku, kur nebarsčiau.
26ጌታውም መልሶ እንዲህ አለው። አንተ ክፉና ሃኬተኛ ባሪያ፥ ካልዘራሁባት እንዳጭድ ካልበተንሁባትም እንድሰበስብ ታውቃለህን?
27Taigi privalėjai duoti mano pinigus pinigų keitėjams, o sugrįžęs būčiau atsiėmęs, kas mano, su palūkanomis.
27ስለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር፥ እኔም መጥቼ ያለኝን ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር።
28Todėl atimkite iš jo talentą ir atiduokite tam, kuris turi dešimt talentų.
28ስለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት አሥር መክሊትም ላለው ስጡት፤
29Nes kiekvienam, kas turi, bus duota, ir jis turės su perteklium, o iš neturinčio bus atimta ir tai, ką jis turi.
29ላለው ሁሉ ይሰጠዋልና ይበዛለትማል፤ ከሌለው ግን ያው ያለው እንኳ ይወሰድበታል።
30Šitą niekam tikusį tarną išmeskite laukan į tamsybes. Ten bus verksmas ir dantų griežimas’ ”.
30የማይጠቅመውንም ባሪያ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል።
31“Kai ateis Žmogaus Sūnus savo šlovėje ir kartu su Juo visi šventi angelai, tada Jis atsisės savo šlovės soste.
31የሰው ልጅ በክብሩ በሚመጣበት ጊዜ ከእርሱም ጋር ቅዱሳን መላእክቱ ሁሉ፥ በዚያን ጊዜ በክብሩ ዙፋን ይቀመጣል፤
32Jo akivaizdoje bus surinkti visų tautų žmonės, ir Jis atskirs juos vienus nuo kitų, kaip piemuo atskiria avis nuo ožių.
32አሕዛብም ሁሉ በፊቱ ይሰበሰባሉ፤ እረኛም በጎቹን ከፍየሎች እንደሚለይ እርስ በርሳቸው ይለያቸዋል፥
33Avis Jis pastatys dešinėje, o ožiuskairėje.
33በጎችን በቀኙ ፍየሎችንም በግራው ያቆማቸዋል።
34Tuomet Karalius tars stovintiems dešinėje: ‘Ateikite, mano Tėvo palaimintieji, paveldėkite nuo pasaulio sukūrimo jums paruoštą karalystę!
34ንጉሡም በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላቸዋል። እናንተ የአባቴ ቡሩካን፥ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ።
35Nes Aš buvau išalkęs, ir jūs mane pavalgydinote, buvau ištroškęs, ir mane pagirdėte, buvau keleivis, ir mane priėmėte,
35ተርቤ አብልታችሁኛልና፥ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛልና፥ እንግዳ ሆኜ ተቀብላችሁኛልና፥ ታርዤ አልብሳችሁኛልና፥
36buvau nuogas, ir mane aprengėte, buvau ligonis, ir mane aplankėte, buvau kalinys, ir atėjote pas mane’.
36ታምሜ ጠይቃችሁኛልና፥ ታስሬ ወደ እኔ መጥታችኋልና።
37Tada teisieji klaus: ‘Viešpatie, kada gi matėme Tave alkaną ir pavalgydinome, ištroškusį ir pagirdėme?
37ጻድቃንም መልሰው ይሉታል። ጌታ ሆይ፥ ተርበህ አይተን መቼ አበላንህስ? ወይስ ተጠምተህ አይተን መቼ አጠጣንህ?
38Kada gi matėme Tave keliaujantį ir priėmėme ar nuogą ir aprengėme?
38እንግዳ ሆነህስ አይተን መቼ ተቀበልንህ? ወይስ ታርዘህ አይተን መቼ አለበስንህ?
39Kada gi matėme Tave sergantį ar kalinį ir aplankėme?’
39ወይስ ታመህ ወይስ ታስረህ አይተን መቼ ወደ አንተ መጣን?
40Ir atsakys jiems Karalius: ‘Iš tiesų sakau jums, kiek kartų tai padarėte vienam iš šitų mažiausiųjų mano brolių, man padarėte’.
40ንጉሡም መልሶ። እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ እንኳ ስላደረጋችሁት ለእኔ አደረጋችሁት ይላቸዋል።
41Tada Jis prabils ir į stovinčius kairėje: ‘Eikite šalin nuo manęs, prakeiktieji, į amžinąją ugnį, kuri paruošta velniui ir jo angelams!
41በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል። እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ።
42Nes Aš buvau išalkęs, ir jūs manęs nepavalgydinote, buvau ištroškęs, ir manęs nepagirdėte,
42ተርቤ አላበላችሁኝምና፥ ተጠምቼ አላጠጣችሁኝምና፥ እንግዳ ሆኜ አልተቀበላችሁኝምና፥
43buvau keleivis, ir manęs nepriėmėte, nuogas, ir manęs neaprengėte, ligonis ir kalinys, ir manęs neaplankėte’.
43ታርዤ አላለበሳችሁኝምና፥ ታምሜ ታስሬም አልጠየቃችሁኝምና።
44Tada jie atsakys: ‘Viešpatie, kada gi matėme Tave alkaną ar ištroškusį, ar keleivį, ar nuogą, ar ligonį, ar kalinį ir Tau nepatarnavome?’
44እነርሱ ደግሞ ይመልሱና። ጌታ ሆይ፥ ተርበህ ወይስ ተጠምተህ ወይስ እንግዳ ሆነህ ወይስ ታርዘህ ወይስ ታመህ ወይስ ታስረህ መቼ አይተን አላገለገልንህም? ይሉታል።
45Tada Jis atsakys jiems: ‘Iš tiesų sakau jums: kiek kartų taip nepadarėte vienam šitų mažiausiųjų, man nepadarėte’.
45ያን ጊዜ። እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ለአንዱ ስላላደረጋችሁት ለእኔ ደግሞ አላደረጋችሁትም ብሎ ይመልስላቸዋል።
46Ir šitie eis į amžinąjį kentėjimą, o teisieji į amžinąjį gyvenimą”.
46እነዚያም ወደ ዘላለም ቅጣት፥ ጻድቃን ግን ወደ ዘላለም ሕይወት ይሄዳሉ።