1Išėjęs iš šventyklos, Jėzus ėjo tolyn. Priėjo Jo mokiniai, rodydami Jam šventyklos pastatus.
1ኢየሱስም ከመቅደስ ወጥቶ ሄደ፥ ደቀ መዛሙርቱም የመቅደሱን ግንቦች ሊያሳዩት ቀረቡ።
2O Jis jiems tarė: “Ar matote visa tai? Iš tiesų sakau jums: čia neliks akmens ant akmens, viskas bus išgriauta!”
2እርሱ ግን መልሶ። ይህን ሁሉ ታያላችሁን? እውነት እላችኋለሁ፥ ድንጋይ በድንጋይ ላይ ሳይፈርስ በዚህ አይቀርም አላቸው።
3Kai Jis sėdėjo Alyvų kalne, priėjo vieni mokiniai ir klausė: “Pasakyk mums, kada tai įvyks? Ir koks Tavo atėjimo ir pasaulio pabaigos ženklas?”
3እርሱም በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ፥ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀርበው። ንገረን፥ ይህ መቼ ይሆናል? የመምጣትህና የዓለም መጨረሻ ምልክቱስ ምንድር ነው? አሉት።
4Jėzus jiems atsakė: “Žiūrėkite, kad niekas jūsų nesuklaidintų.
4ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው። ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ።
5Daug kas ateis mano vardu ir sakys: ‘Aš esu Kristus!’, ir daugelį suklaidins.
5ብዙዎች። እኔ ክርስቶስ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉና፤ ብዙዎችንም ያስታሉ።
6Girdėsite apie karus ir karų gandus. Žiūrėkite, kad neišsigąstumėte, nes visa tai turi įvykti. Bet tai dar ne galas.
6ጦርንም የጦርንም ወሬ ትሰሙ ዘንድ አላችሁ፤ ይህ ሊሆን ግድ ነውና ተጠበቁ፥ አትደንግጡ፤ ዳሩ ግን መጨረሻው ገና ነው።
7Tauta sukils prieš tautą ir karalystė prieš karalystę. Įvairiose vietose bus badmečių, marų ir žemės drebėjimų.
7ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፥ ራብም ቸነፈርም የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል፤
8Tačiau visa taigimdymo skausmų pradžia.
8እነዚህም ሁሉ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው።
9Tada jus atiduos kankinti ir žudyti. Jūs būsite visų tautų nekenčiami dėl mano vardo.
9በዚያን ጊዜ ለመከራ አሳልፈው ይሰጡአችኋል ይገድሉአችሁማል፥ ስለ ስሜም በአሕዛብ ሁሉ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ።
10Daugelis pasipiktins, vieni kitus išdavinės ir vieni kitų nekęs.
10በዚያን ጊዜም ብዙዎች ይሰናከላሉ እርስ በርሳቸውም አሳልፈው ይሰጣጣሉ እርስ በርሳቸውም ይጣላሉ፤
11Atsiras daug netikrų pranašų, kurie daugelį suvedžios.
11ብዙ ሐሰተኞች ነቢያትም ይነሣሉ ብዙዎችንም ያስታሉ፤
12Kadangi įsigalės neteisumas, daugelio meilė atšals.
12ከዓመፃም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች።
13Bet kas ištvers iki galo, tas bus išgelbėtas.
13እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል።
14Ir bus paskelbta ši karalystės Evangelija visame pasaulyje paliudyti visoms tautoms. Ir tada ateis galas”.
14ለአሕዛብም ሁሉ ምስክር እንዲሆን ይህ የመንግሥት ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል፥ በዚያን ጊዜም መጨረሻው ይመጣል።
15“Todėl, kai pamatysite per pranašą Danielių paskelbtą naikinimo bjaurastį, stovinčią šventoje vietoje (kas skaito, teišmano),
15እንግዲህ በነቢዩ በዳንኤል የተባለውን የጥፋትን ርኩሰት በተቀደሰችው ስፍራ ቆሞ ስታዩ፥ አንባቢው ያስተውል፥
16tada, kas bus Judėjoje, tebėga į kalnus,
16በዚያን ጊዜ በይሁዳ ያሉት ወደ ተራራዎች ይሽሹ፥
17kas ant stogo, tenelipa žemėn pasiimti ko nors iš savo namų,
17በሰገነትም ያለ በቤቱ ያለውን ሊወስድ አይውረድ፥
18o kas laukuose, tenegrįžta pasiimti apsiausto.
18በእርሻም ያለ ልብሱን ይወስድ ዘንድ ወደ ኋላው አይመለስ።
19Vargas nėščioms ir žindančioms tomis dienomis!
19በዚያችም ወራት ለርጉዞችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው።
20Bet melskitės, kad jums netektų bėgti žiemą ar per sabatą.
20ነገር ግን ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት እንዳይሆን ጸልዩ፤
21Tuomet bus didelis suspaudimas, kokio nėra buvę nuo pasaulio pradžios iki dabar ir kokio daugiau nebebus.
21በዚያን ጊዜ ከዓለም መጀመሪያ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ያልሆነ እንግዲህም ከቶ የማይሆን ታላቅ መከራ ይሆናልና።
22Ir jeigu tos dienos nebūtų sutrumpintos, neišsigelbėtų nė vienas kūnas. Bet dėl išrinktųjų tos dienos bus sutrumpintos.
22እነዚያ ቀኖችስ ባያጥሩ ሥጋ የለበሰ ሁሉ ባልዳነም ነበር፤ ነገር ግን እነዚያ ቀኖች ስለ ተመረጡት ሰዎች ያጥራሉ።
23Jei tada kas nors jums sakys: ‘Štai čia Kristus’, arba: ‘Jis tenai!’,netikėkite,
23በዚያን ጊዜ ማንም። እነሆ፥ ክርስቶስ ከዚህ አለ ወይም። ከዚያ አለ ቢላችሁ አትመኑ፤
24nes atsiras netikrų kristų ir netikrų pranašų, ir jie darys didelių ženklų bei stebuklų, kad suklaidintų, jei įmanoma, net išrinktuosius.
24ሐሰተኞች ክርስቶሶችና ሐሰተኞች ነቢያት ይነሣሉና፥ ቢቻላቸውስ የተመረጡትን እንኳ እስኪያስቱ ድረስ ታላላቅ ምልክትና ድንቅ ያሳያሉ።
25Štai Aš jums iš anksto tai pasakiau!”
25እነሆ፥ አስቀድሜ ነገርኋችሁ።
26“Todėl, jeigu jums sakytų: ‘Štai Jis dykumoje!’, neikite, ‘Štai Jis kambariuose!’, netikėkite.
26እንግዲህ። እነሆ፥ በበረሀ ነው ቢሉአችሁ፥ አትውጡ፤ እነሆ፥ በእልፍኝ ነው ቢሉአችሁ፥ አትመኑ፤
27Kaip žaibas tvyksteli iš rytų ir nušvinta iki vakarų, toks bus ir Žmogaus Sūnaus atėjimas.
27መብረቅ ከምሥራቅ ወጥቶ እስከ ምዕራብ እንደሚታይ፥ የሰው ልጅ መምጣት እንዲሁ ይሆናልና፤
28Kur tik bus lavonų, ten sulėks ir maitvanagiai.
28በድን ወዳለበት በዚያ አሞራዎች ይሰበሰባሉ።
29Tuoj pat po tų suspaudimo dienų saulė užtems, mėnulis nebeduos šviesos, žvaigždės kris iš dangaus, ir dangaus jėgos bus sudrebintos.
29ከዚያች ወራትም መከራ በኋላ ወዲያው ፀሐይ ይጨልማል፥ ጨረቃም ብርሃንዋን አትሰጥም፥ ከዋክብትም ከሰማይ ይወድቃሉ፥
30Tada danguje pasirodys Žmogaus Sūnaus ženklas, ir visos žemės giminės raudos ir pamatys Žmogaus Sūnų, ateinantį dangaus debesyse su galybe ir didžia šlove.
30የሰማያትም ኃይላት ይናወጣሉ። በዚያን ጊዜም የሰው ልጅ ምልክት በሰማይ ይታያል፥ በዚያን ጊዜም የምድር ወገኖች ሁሉ ዋይ ዋይ ይላሉ፥ የሰው ልጅንም በኃይልና በብዙ ክብር በሰማይ ደመና ሲመጣ ያዩታል፤
31Jis pasiųs savo angelus su skardžiais trimitų garsais, ir jie surinks Jo išrinktuosius iš keturių žemės pusių, nuo vieno dangaus pakraščio iki kito.
31መላእክቱንም ከታላቅ መለከት ድምፅ ጋር ይልካቸዋል፥ ከሰማያትም ዳርቻ እስከ ዳርቻው ከአራቱ ነፋሳት ለእርሱ የተመረጡትን ይሰበስባሉ።
32Pasimokykite iš palyginimo su figmedžiu: kai jo šaka suminkštėja ir sprogsta lapai, jūs žinote, jog artėja vasara.
32ምሳሌውንም ከበለስ ተማሩ፤ ጫፍዋ ሲለሰልስ ቅጠልዋም ሲያቈጠቍጥ፥ ያን ጊዜ በጋ እንደ ቀረበ ታውቃላችሁ፤
33Taip pat, visa šita išvydę, žinokite, jog tai arti, prie durų.
33እንዲሁ እናንተ ደግሞ ይህን ሁሉ ስታዩ በደጅ እንደ ቀረበ እወቁ።
34Iš tiesų sakau jums: ši karta nepraeis, iki visa tai įvyks.
34እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ሁሉ እስኪሆን ድረስ ይህ ትውልድ አያልፍም።
35Dangus ir žemė praeis, bet mano žodžiai nepraeis.
35ሰማይና ምድር ያልፋሉ፥ ቃሌ ግን አያልፍም።
36Tačiau tos dienos ir valandos niekas nežino, nė dangaus angelai, o vien tik mano Tėvas”.
36ስለዚያች ቀንና ስለዚያች ሰዓት ግን ከአባት ብቻ በቀር የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ ልጅም ቢሆን የሚያውቅ የለም።
37“Kaip buvo Nojaus dienomis, taip bus ir tada, kai ateis Žmogaus Sūnus.
37የኖኅ ዘመን እንደ ነበረ የሰው ልጅ መምጣት እንዲሁ ይሆናልና።
38Kaip dienomis prieš tvaną žmonės valgė, gėrė, tuokėsi ir tuokė iki tos dienos, kurią Nojus įžengė į laivą,
38በዚያች ወራት ከጥፋት ውኃ በፊት፥ ኖኅ ወደ መርከብ እስከገባበት ቀን ድረስ፥ ሲበሉና ሲጠጡ ሲያገቡና ሲጋቡም እንደ ነበሩ፥
39nieko nenumanydami, kol užėjo tvanas ir visus nusinešė; taip bus ir tada, kai ateis Žmogaus Sūnus.
39የጥፋት ውኃም መጥቶ ሁሉን እስከ ወሰደ ድረስ እንዳላወቁ፥ የሰው ልጅ መምጣት ደግሞ እንዲሁ ይሆናል።
40Tada du bus kartu lauke, ir vienas bus paimtas, o kitas paliktas.
40በዚያን ጊዜ ሁለት ሰዎች በእርሻ ይሆናሉ፤ አንዱ ይወሰዳል አንዱም ይቀራል፤
41Dvi mals girnomis, ir viena bus paimta, o kita palikta.
41ሁለት ሴቶች በወፍጮ ይፈጫሉ፤ አንዲቱ ትወሰዳለች አንዲቱም ትቀራለች።
42Todėl budėkite, nes nežinote, kurią valandą ateis jūsų Viešpats.
42ጌታችሁ በምን ሰዓት እንዲመጣ አታውቁምና እንግዲህ ንቁ።
43Supraskite ir tai: jeigu šeimininkas žinotų, kurią nakties valandą ateis vagis, jis budėtų ir neleistų jam įsilaužti į namus.
43ያን ግን እወቁ፤ ባለቤት ከሌሊቱ በየትኛው ክፍል ሌባ እንዲመጣ ቢያውቅ ኖሮ፥ በነቃ ቤቱም ሊቈፈር ባልተወም ነበር።
44Todėl ir jūs būkite pasiruošę, nes Žmogaus Sūnus ateis tą valandą, kurią nemanote”.
44ስለዚህ እናንተ ደግሞ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፥ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና።
45“Kas yra tas ištikimas bei protingas tarnas, kurį šeimininkas paskyrė tarnauti savo šeimynai, kad ją maitintų deramu laiku?
45እንኪያስ ምግባቸውን በጊዜው ይሰጣቸው ዘንድ ጌታው በቤተ ሰዎች ላይ የሾመው ታማኝና ልባም ባሪያ ማን ነው?
46Palaimintas tarnas, kurį sugrįžęs šeimininkas ras taip darantį.
46ጌታው መጥቶ እንዲህ ሲያደርግ የሚያገኘው ያ ባሪያ ብፁዕ ነው፤
47Iš tiesų sakau jums: jį paskirs valdyti visų savo turtų.
47እውነት እላችኋለሁ፥ ባለው ሁሉ ላይ ይሾመዋል።
48Bet jei blogas tarnas tartų savo širdyje: ‘Mano šeimininkas neskuba grįžti’,
48ያ ክፉ ባሪያ ግን። ጌታዬ እስኪመጣ ይዘገያል ብሎ በልቡ ቢያስብ፥
49ir pradėtų mušti savo tarnybos draugus, valgyti ir gerti su girtuokliais,
49ባልንጀሮቹን ባሮች ሊመታ ቢጀምር ከሰካሮችም ጋር ቢበላና ቢጠጣ፥
50to tarno šeimininkas sugrįš tą dieną, kai jis nelaukia, ir tą valandą, kurią jis nemano.
50የዚያ ባሪያ ጌታ ባልጠበቃት ቀን ባላወቃትም ሰዓት ይመጣል፥
51Jis perkirs jį pusiau ir paskirs jam dalį su veidmainiais. Ten bus verksmas ir dantų griežimas”.
51ከሁለትም ይሰነጥቀዋል፥ እድሉንም ከግብዞች ጋር ያደርግበታል፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል።