Lithuanian

Amharic: New Testament

Matthew

23

1Tuomet Jėzus ėmė kalbėti minioms ir savo mokiniams:
1በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ለሕዝቡና ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ ብሎ ነገራቸው።
2“Į Mozės krasę atsisėdo Rašto žinovai ir fariziejai.
2ጻፎችና ፈሪሳውያን በሙሴ ወንበር ተቀምጠዋል።
3Todėl visko, ko jie liepia jums laikytis, laikykitės ir vykdykite, tačiau nesielkite, kaip jie elgiasi, nes jie kalba, bet nedaro.
3ስለዚህ ያዘዙአችሁን ሁሉ አድርጉ ጠብቁትም፥ ነገር ግን እየተናገሩ አያደርጉትምና እንደ ሥራቸው አታድርጉ።
4Jie riša sunkias, nepanešamas naštas ir krauna žmonėms ant pečių, o patys nenori jų nė pirštu pajudinti.
4ከባድና አስቸጋሪ ሸክም ተብትበው በሰው ትከሻ ይጭናሉ፥ እነርሱ ግን በጣታቸው ስንኳ ሊነኩት አይወዱም።
5Jie viską daro, kad būtų žmonių matomi. Jie pasiplatina maldos diržus ir pasididina apsiaustų kutus.
5ለሰውም እንዲታዩ ሥራቸውን ሁሉ ያደርጋሉ፤ ስለዚህ አሽንክታባቸውን ያሰፋሉ ዘርፉንም ያስረዝማሉ፥
6Jie mėgsta garbės vietas pokyliuose bei pirmuosius krėslus sinagogose,
6በምሳም የከበሬታ ስፍራ፥ በምኵራብም የከበሬታ ወንበር፥
7mėgsta sveikinimus aikštėse ir, kad žmonės juos vadintų ‘Rabi, Rabi’.
7በገበያም ሰላምታና። መምህር ሆይ መምህር ሆይ ተብለው እንዲጠሩ ይወዳሉ።
8Bet jūs nesivadinkite ‘Rabi’, nes vienas yra jūsų Mokytojas­Kristus, o jūs visi esate broliai.
8እናንተ ግን። መምህር ተብላችሁ አትጠሩ፤ መምህራችሁ አንድ ስለ ሆነ እናንተም ሁላችሁ ወንድማማች ናችሁ።
9Ir nė vieno žemėje nevadinkite tėvu, nes vienas jūsų Tėvas, kuris yra danguje.
9አባታችሁ አንዱ እርሱም የሰማዩ ነውና በምድር ላይ ማንንም። አባት ብላችሁ አትጥሩ።
10Taip pat nesivadinkite mokytojais, nes vienas jūsų Mokytojas­ Kristus.
10ሊቃችሁ አንድ እርሱም ክርስቶስ ነውና። ሊቃውንት ተብላችሁ አትጠሩ።
11Kas iš jūsų didžiausias, tebūna jums tarnas.
11ከእናንተም የሚበልጠው አገልጋያችሁ ይሆናል።
12Ir kas save aukština, bus pažemintas, o kas save žemina, bus išaukštintas.
12ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳል፥ ራሱንም የሚያዋርድ ሁሉ ከፍ ይላል።
13Bet vargas jums, veidmainiai Rašto žinovai ir fariziejai! Nes jūs užrakinate žmonėms dangaus karalystę ir nei patys neinate, nei į ją einantiems neleidžiate įeiti.
13እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ መንግሥተ ሰማያትን በሰው ፊት ስለምትዘጉ፥ ወዮላችሁ እናንተ አትገቡም የሚገቡትንም እንዳይገቡ ትከለክላላችሁ።
14Vargas jums, veidmainiai Rašto žinovai ir fariziejai! Nes jūs suryjate našlių namus ir dedatės kalbą ilgas maldas, todėl gausite dar didesnį pasmerkimą.
14እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ በጸሎት ርዝመት እያመካኛችሁ የመበለቶችን ቤት ስለምትበሉ፥ ወዮላችሁ፤ ስለዚህ የባሰ ፍርድ ትቀበላላችሁ።
15Vargas jums, veidmainiai Rašto žinovai ir fariziejai! Nes jūs keliaujate per jūrą ir sausumą, kad laimėtumėte vieną naujatikį, ir kai jis tokiu tampa, jūs padarote iš jo pragaro vaiką, dvigubai blogesnį už jus pačius.
15እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ አንድ ሰው ልታሳምኑ በባሕርና በደረቅ ስለምትዞሩ፥ በሆነም ጊዜ ከእናንተ ይልቅ ሁለት እጥፍ የባሰ የገሃነም ልጅ ስለምታደርጉት፥ ወዮላችሁ።
16Vargas jums, aklieji vadai, kurie sakote: ‘Jei kas prisiektų šventykla, tai nieko, o jei kas prisiektų šventyklos auksu, tai jis įsipareigoja’.
16እናንተ። ማንም በቤተ መቅደስ የሚምል ምንም የለበትም፤ ማንም በቤተ መቅደስ ወርቅ የሚምል ግን በመሐላው ይያዛል የምትሉ፥ ዕውሮች መሪዎች፥ ወዮላችሁ።
17Kvaili jūs ir akli! Kas gi didesnis­auksas ar šventykla, kuri pašventina auksą?
17እናንተ ደንቆሮዎችና ዕውሮች፥ ማናቸው ይበልጣል? ወርቁ ነውን? ወይስ ወርቁን የቀደሰው ቤተ መቅደስ?
18Arba vėl sakote: ‘Jei kas prisiektų aukuru, tai nieko, o jei kas prisiektų atnaša ant aukuro, tai jis įsipareigoja’.
18ደግማችሁም። ማንም በመሠዊያው የሚምል ምንም የለበትም፤ ማንም በላዩ ባለው መባ የሚምል ግን በመሐላው ይያዛል ትላላችሁ።
19Kvaili ir akli! Kas gi didesnis­ atnaša ar aukuras, kuris pašventina atnašą?
19እናንተ ደንቆሮዎችና ዕውሮች፥ ማናቸው ይበልጣል? መባው ነውን? ወይስ መባውን የሚቀድሰው መሠዊያው?
20Todėl, kas prisiekia aukuru, prisiekia juo ir viskuo, kas ant jo padėta,
20እንግዲህ በመሠዊያው የሚምለው በእርሱና በእርሱ ላይ ባለው ሁሉ ይምላል፤
21o kas prisiekia šventykla, prisiekia ja ir Tuo, kuris joje gyvena.
21በቤተ መቅደስም የሚምለው በእርሱና በእርሱ በሚኖረው ይምላል፤
22Ir kas prisiekia dangumi, prisiekia Dievo sostu ir Tuo, kuris jame sėdi.
22በሰማይም የሚምለው በእግዚአብሔር ዙፋንና በእርሱ ላይ በተቀመጠው ይምላል።
23Vargas jums, veidmainiai Rašto žinovai ir fariziejai! Nes jūs duodate dešimtinę nuo mėtų, krapų ir kmynų, o paliekate, kas Įstatyme svarbiau,­teisingumą, gailestingumą ir tikėjimą. Tai turite daryti ir ano nepalikti!
23እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ ከአዝሙድና ከእንስላል ከከሙንም አሥራት ስለምታወጡ፥ ፍርድንና ምሕረትን ታማኝነትንም፥ በሕግ ያለውን ዋና ነገር ስለምትተዉ፥ ወዮላችሁ፤ ሌላውን ሳትተዉ ይህን ልታደርጉ ይገባችሁ ነበር።
24Akli vadai, jūs iškošiate uodą, o praryjate kupranugarį.
24እናንተ ዕውሮች መሪዎች፥ ትንኝን የምታጠሩ ግመልንም የምትውጡ።
25Vargas jums, veidmainiai Rašto žinovai ir fariziejai! Nes jūs valote taurės bei dubens išorę, o viduje esate pilni gobšumo ir nesusilaikymo.
25እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ በውስጡ ቅሚያና ስስት ሞልቶ ሳለ የጽዋውንና የወጭቱን ውጭ ስለምታጠሩ፥ ወዮላችሁ።
26Aklas fariziejau! Pirmiau išvalyk taurės ir dubens vidų, kad būtų švari ir išorė!
26አንተ ዕውር ፈሪሳዊ፥ ውጭው ደግሞ ጥሩ እንዲሆን አስቀድመህ የጽዋውንና የወጭቱን ውስጡን አጥራ።
27Vargas jums, veidmainiai Rašto žinovai ir fariziejai! Nes jūs panašūs į pabaltintus kapus, kurie iš paviršiaus atrodo gražiai, o viduje pilni numirėlių kaulų ir visokių nešvarumų.
27እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ በውጭ አምረው የሚታዩ በውስጡ ግን የሙታን አጥንት ርኩሰትም ሁሉ የተሞሉ በኖራ የተለሰኑ መቃብሮችን ስለምትመስሉ፥ ወዮላችሁ።
28Taip ir jūs iš paviršiaus atrodote žmonėms teisūs, o viduje esate pilni veidmainystės ir nedorumo.
28እንዲሁ እናንተ ደግሞ በውጭ ለሰው እንደ ጻድቃን ትታያላችሁ፥ በውስጣችሁ ግን ግብዝነትና ዓመፀኝነት ሞልቶባችኋል።
29Vargas jums, veidmainiai Rašto žinovai ir fariziejai! Nes jūs statote pranašams antkapius, puošiate teisiųjų kapus
29እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ የነቢያትን መቃብር ስለምትሠሩ የጻድቃንንም መቃብር ስለምታስጌጡና።
30ir sakote: ‘Jei būtume gyvenę savo protėvių dienomis, nebūtume kartu su jais susitepę pranašų krauju’.
30በአባቶቻችን ዘመን ኖረን በሆነስ በነቢያት ደም ባልተባበርናቸውም ነበር ስለምትሉ፥ ወዮላችሁ።
31Taigi jūs patys prieš save liudijate, jog esate pranašų žudytojų vaikai.
31እንግዲያስ የነቢያት ገዳዮች ልጆች እንደሆናችሁ በራሳችሁ ላይ ትመሰክራላችሁ።
32Pripildykite tad savo tėvų saiką!
32እናንተ ደግሞ የአባቶቻችሁን መስፈሪያ ሙሉ።
33Gyvatės! Angių išperos! Kaip jūs ištrūksite nuo pasmerkimo į pragarą?!
33እናንተ እባቦች፥ የእፉኝት ልጆች፥ ከገሃነም ፍርድ እንዴት ታመልጣላችሁ?
34Todėl štai siunčiu pas jus pranašų, išminčių ir Rašto žinovų. Vienus iš jų užmušite ir nukryžiuosite, kitus plaksite savo sinagogose ir persekiosite nuo miesto iki miesto,
34ስለዚህ፥ እነሆ፥ ነቢያትንና ጥበበኞችን ጻፎችንም ወደ እናንተ እልካለሁ፤ ከእነርሱም ትገድላላችሁ ትሰቅሉማላችሁ፥ ከእነርሱም በምኵራባችሁ ትገርፋላችሁ ከከተማም ወደ ከተማ ታሳድዳላችሁ፤
35kad ant jūsų kristų visas teisus kraujas, pralietas žemėje, pradedant teisiojo Abelio krauju ir baigiant krauju Barachijo sūnaus Zacharijo, kurį nužudėte tarp šventyklos ir aukuro.
35ከጻድቁ ከአቤል ደም ጀምሮ በቤተ መቅደስና በመሠዊያው መካከል እስከ ገደላችሁት እስከ በራክዩ ልጅ እስከ ዘካርያስ ደም ድረስ በምድር ላይ የፈሰሰው የጻድቅ ደም ሁሉ ይደርስባችሁ ዘንድ።
36Iš tiesų sakau jums: visa tai ištiks šitą kartą”.
36እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ሁሉ በዚህ ትውልድ ላይ ይደርሳል።
37“Jeruzale, Jeruzale! Tu žudai pranašus ir užmėtai akmenimis tuos, kurie pas tave siųsti. Kiek kartų norėjau surinkti tavo vaikus, kaip višta surenka savo viščiukus po sparnais, o tu nenorėjai!
37ኢየሩሳሌም ኢየሩሳሌም ሆይ፥ ነቢያትን የምትገድል ወደ እርስዋ የተላኩትንም የምትወግር፥ ዶሮ ጫጩቶችዋን ከክንፎችዋ በታች እንደምትሰበስብ ልጆችሽን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ! አልወደዳችሁምም።
38Štai jūsų namai jums paliekami tušti.
38እነሆ፥ ቤታችሁ የተፈታ ሆኖ ይቀርላችኋል።
39Ir sakau jums: nuo dabar jūs manęs nebematysite, kol tarsite: ‘Palaimintas Tas, kuris ateina Viešpaties vardu!’ ”
39እላችኋለሁና፥ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው እስክትሉ ድረስ ከእንግዲህ ወዲህ አታዩኝም።