Lithuanian

Amharic: New Testament

Mark

7

1Pas Jį susirinko fariziejų ir keli Rašto žinovai, atvykę iš Jeruzalės.
1ፈሪሳውያንና ከጻፎች ወገን ከኢየሩሳሌም የመጡትም ወደ እርሱ ተሰበሰቡ።
2Jie, pamatę kai kuriuos Jo mokinius valgant duoną suterštomis (tai yra neplautomis) rankomis, pradėjo priekaištauti.
2ከደቀ መዛሙርቱም አንዳንድ በርኵስ ማለት ባልታጠበ እጅ እንጀራ ሲበሉ አዩ።
3Mat fariziejai ir visi žydai, laikydamiesi prosenių tradicijos, valgo tik nusiplovę rankas.
3ፈሪሳውያንና አይሁድም ሁሉ የሽማግሎችን ወግ ሲጠብቁ እጃቸውን ደኅና አድርገው ሳይታጠቡ አይበሉምና፥
4Taip pat sugrįžę iš turgaus, jie nevalgo neapsiplovę. Be to, yra daug kitų nuostatų, kurių jie laikosi, sekdami tradicija, pavyzdžiui, taurių, puodelių bei varinių indų plovimo.
4ከገበያም ተመልሰው ካልታጠቡ አይበሉም፥ ጽዋንም ማድጋንም የናስ ዕቃንም አልጋንም እንደ ማጠብ ሌላ ነገር ሊጠብቁት የተቀበሉት ብዙ አለ።
5Taigi fariziejai ir Rašto žinovai Jį klausė: “Kodėl Tavo mokiniai nesilaiko prosenių tradicijos ir valgo duoną neplautomis rankomis?”
5ፈሪሳውያንም ጻፎችም። ደቀ መዛሙርትህ እንደ ሽማግሌዎች ወግ ስለ ምን አይሄዱም? ነገር ግን እጃቸውን ሳይታጠቡ እንጀራ ይበላሉ ብለው ጠየቁት።
6Jis jiems atsakė: “Gerai apie jus, veidmainius, pranašavo Izaijas, kaip parašyta: ‘Ši tauta gerbia mane lūpomis, bet jų širdis toli nuo manęs.
6እርሱ ግን እንዲህ አላቸው። ኢሳይያስ ስለ እናንተ ስለ ግብዞች። ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል ልቡ ግን ከእኔ በጣም የራቀ ነው፤
7Veltui jie mane garbina, žmogiškus priesakus paversdami mokymu’.
7የሰውም ሥርዓት የሆነ ትምህርት እያስተማሩ በከንቱ ያመልኩኛል ተብሎ እንደ ተጻፈ በእውነት ትንቢት ተናገረ።
8Palikdami Dievo įsakymą, jūs įsikibę laikotės žmonių tradicijų­ puodelių ir taurių plovimo, ir daug kitų panašių dalykų darote”.
8የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ትታችሁ ጽዋን ማድጋንም እንደ ማጠብ የሰውን ወግ ትጠብቃላችሁ፥ ይህንም የመሰለ ብዙ ሌላ ነገር ታደርጋላችሁ።
9Ir Jis pridūrė: “Puikiai jūs paverčiate niekais Dievo įsakymą, kad tik išsaugotumėte savo tradicijas!
9እንዲህም አላቸው። ወጋችሁን ትጠብቁ ዘንድ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ እጅግ ንቃችኋል።
10Antai Mozė įsakė: ‘Gerbk savo tėvą ir motiną’, ir: ‘Kas keiktų tėvą ar motiną, mirtimi temiršta’.
10ሙሴ። አባትህንና እናትህን አክብር፤ ደግሞ። አባቱን ወይም እናቱን የሰደበ ፈጽሞ ይሙት ብሎአልና።
11O jūs sakote: ‘Jei žmogus pasako savo tėvui ar motinai: Viskas, kas tau būtų naudinga iš manęs, tebūnie Korbįn (tai yra: dovana Dievui),­
11እናንተ ግን ትላላችሁ። ሰው አባቱን ወይም እናቱን። ከእኔ የምትጠቀምበት ነገር ሁሉ ቍርባን ማለት መባ ነው ቢል፥
12tada jūs nebeleidžiate jam padėti tėvui ar motinai,
12ለአባቱና ለእናቱ ምንም እንኳ ሊያደርግ ወደ ፊት አትፈቅዱለትም፤
13savo perduodama tradicija Dievo žodį darydami negaliojantį. Ir daug panašių dalykų darote”.
13ባስተላለፋችሁትም ወግ የእግዚአብሔርን ቃል ትሽራላችሁ፤ እንደዚሁም ይህን የሚመስል ብዙ ነገር ታደርጋላችሁ።
14Sušaukęs visus žmones, Jėzus kalbėjo: “Paklausykite manęs visi ir supraskite:
14ደግሞም ሕዝቡን ጠርቶ። ሁላችሁ እኔን ስሙ አስተውሉም።
15nėra nieko, kas, iš išorės patekęs į žmogų, galėtų jį suteršti. Žmogų suteršia vien tai, kas iš žmogaus išeina.
15ከሰው የሚወጡት ሰውን የሚያረክሱ ናቸው እንጂ ከሰው ውጭ የሚገባውስ ሊያረክሰው የሚችል ምንም የለም።
16Kas turi ausis klausyti­teklauso”.
16የሚሰማ ጆሮ ያለው ቢኖር ይስማ አላቸው።
17Kai sugrįžo nuo minios į namus, Jo mokiniai paklausė apie palyginimą.
17ከሕዝቡ ዘንድ ወደ ቤት ከገባ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ምሳሌውን ጠየቁት።
18Jis jiems sako: “Nejaugi ir jūs nesuprantate? Argi neaišku jums, kad visa, kas patenka į žmogų iš lauko, negali jo suteršti,
18እርሱም። እናንተ ደግሞ እንደዚህ የማታስተውሉ ናችሁን? ከውጭ ወደ ሰው የሚገባ ሊያረክሰው ምንም እንዳይችል አትመለከቱምን?
19nes nepatenka į jo širdį, bet į vidurius ir išeina laukan, ir taip išvalomas visas maistas?”
19ወደ ሆድ ገብቶ ወደ እዳሪ ይወጣል እንጂ ወደ ልብ አይገባምና፤ መብልን ሁሉ እያጠራ አላቸው።
20Ir Jis pasakė: “Žmogų suteršia tai, kas iš jo išeina.
20እርሱም አለ። ከሰው የሚወጣው ሰውን የሚያረክስ ያ ነው።
21Iš vidaus, iš žmonių širdies, išeina pikti sumanymai, svetimavimai, paleistuvystės, vagystės, žmogžudystės,
21ከውስጥ ከሰው ልብ የሚወጣ ክፉ አሳብ፥
22godumas, piktumas, klasta, nesusilaikymas, pavydas, piktžodžiavimai, išdidumas, kvailystė.
22ዝሙት፥ መስረቅ፥ መግደል፥ ምንዝርነት፥ መጐምጀት፥ ክፋት፥ ተንኰል፥ መዳራት፥ ምቀኝነት፥ ስድብ፥ ትዕቢት፥ ስንፍና ናቸውና፤
23Visos tos blogybės išeina iš vidaus ir suteršia žmogų”.
23ይህ ክፉው ሁሉ ከውስጥ ይወጣል ሰውን ያረክሰዋል።
24Išvykęs iš ten, Jis nukeliavo į Tyro ir Sidono sritis. Užėjęs į vienus namus, Jis norėjo, kad niekas apie tai nežinotų, bet Jam nepavyko to nuslėpti.
24ከዚያም ተነሥቶ ወደ ጢሮስና ወደ ሲዶና አገር ሄደ። ወደ ቤትም ገብቶ ማንም እንዳያውቅበት ወደደ ሊሰወርም አልተቻለውም፤
25Išgirdus apie Jį, moteris, kurios duktė turėjo netyrąją dvasią, atėjo ir puolė Jam po kojų.
25ወዲያው ግን ታናሺቱ ልጅዋ ርኵስ መንፈስ ያደረባት አንዲት ሴት ስለ እርሱ ሰምታ መጣችና በእግሩ ላይ ተደፋች
26Moteris buvo graikė, kilimo sirofinikietė. Ji maldavo, kad Jis išvarytų iš jos dukrelės demoną.
26ሴቲቱም ግሪክ፥ ትውልድዋም ሲሮፊኒቃዊት ነበረች፤ ከልጅዋ ጋኔን ያወጣላት ዘንድ ለመነችው።
27Jėzus jai tarė: “Leisk pirmiau pasisotinti vaikams. Juk nedera imti vaikų duoną ir mesti šunyčiams”.
27ኢየሱስ ግን። ልጆቹ በፊት ይጠግቡ ዘንድ ተዪ የልጆቹን እንጀራ ይዞ ለቡችሎች መጣል አይገባምናአላት።
28Moteris tarė: “Taip, Viešpatie! Bet ir šunyčiai po stalu ėda vaikų trupinius”.
28እርስዋም መልሳ። አዎን፥ ጌታ ሆይ፥ ቡችሎች እንኳ ከማዕድ በታች ሆነው የልጆችን ፍርፋሪ ይበላሉ አለችው።
29Tada Jis tarė: “Dėl šitų žodžių eik namo,­demonas jau išėjęs iš tavo dukters”.
29እርሱም። ስለዚህ ቃልሽ ሂጂ ጋኔኑ ከልጅሽ ወጥቶአል አላት።
30Parėjusi namo, ji rado dukrelę gulinčią patale ir demoną išėjusį.
30ወደ ቤትዋም ሄዳ ጋኔኑ ወጥቶ ልጅዋም በአልጋ ላይ ተኝታ አገኘች።
31Palikęs Tyro ir Sidono sritis, Jis vėl atėjo prie Galilėjos ežero, į Dekapolio krašto vidurį.
31ደግሞም ከጢሮስ አገር ወጥቶ በሲዶና አልፎ አሥር ከተማ በሚባል አገር መካከል ወደ ገሊላ ባሕር መጣ።
32Ten atvedė Jam kurčią nebylį ir prašė uždėti ant jo ranką.
32ደንቆሮና ኰልታፋም የሆነ ሰው ወደ እርሱ አመጡ፥
33Jis pasivedė jį nuošaliau nuo minios, įkišo savo pirštus į jo ausis, palietė seilėmis jo liežuvį,
33እጁንም ይጭንበት ዘንድ ለመኑት። ከሕዝቡም ለይቶ ለብቻው ወሰደው፥ ጣቶቹንም በጆሮቹ አገባ እንትፍም ብሎ መላሱን ዳሰሰ፤
34pažvelgė į dangų, atsiduso ir tarė jam: “Efatį!”, tai yra: “Atsiverk!”
34ወደ ሰማይም አሻቅቦ አይቶ ቃተተና። ኤፍታህ አለው፥ እርሱም ተከፈት ማለት ነው።
35Ir tuojau atsivėrė jo klausa, atsipalaidavo liežuvio ryšys, ir jis kalbėjo kaip reikia.
35ወዲያውም ጆሮቹ ተከፈቱ የመላሱም እስራት ተፈታ አጥርቶም ተናገረ።
36Jėzus jiems įsakė niekam šito nepasakoti. Bet kuo labiau Jis draudė, tuo jie plačiau Jį garsino.
36ለማንም አትንገሩ ብሎ አዘዛቸው እነርሱ ግን ባዘዛቸውም መጠን ይልቅ እጅግ አወሩት።
37Žmonės labai stebėjosi ir kalbėjo: “Jis visa gerai padarė! Jis daro, kad kurtieji girdi ir nebyliai kalba!”
37ያለ መጠንም ተገረሙና። ሁሉን ደኅና አድርጎአል፤ ደንቆሮችም እንዲሰሙ ዲዳዎችም እንዲናገሩ ያደርጋል አሉ።