Lithuanian

Amharic: New Testament

Mark

8

1Anomis dienomis, susirinkus gausiai miniai ir žmonėms neturint ko valgyti, Jėzus, pasišaukęs savo mokinius, tarė:
1በዚያ ወራት ደግሞ ብዙ ሕዝብ ነበረ የሚበሉትም ስለሌላቸው ደቀ መዛሙርቱን ጠርቶ።
2“Gaila man minios! Jau trys dienos žmonės yra su manimi ir neturi ko valgyti.
2ሕዝቡ ከእኔ ጋር እስካሁን ሦስት ቀን ውለዋልና የሚበሉት ስለሌላቸው አዝንላቸዋለሁ፤
3Jei paleisiu juos namo alkanus, jie nusilps kelyje, nes kai kurie yra atėję iš toli”.
3ከእነርሱም አንዳንዶቹ ከሩቅ መጥተዋልና ጦማቸውን ወደ ቤታቸው ባሰናብታቸው በመንገድ ይዝላሉ አላቸው።
4Mokiniai Jam atsakė: “Iš kur dykumoje gauti duonos jiems pavalgydinti?”
4ደቀ መዛሙርቱም። በዚህ በምድረ በዳ እንጀራ ከየት አግኝቶ ሰው እነዚህን ማጥገብ ይችላል? ብለው መለሱለት።
5Jėzus paklausė: “Kiek kepalų turite?” Jie atsakė: “Septynis”.
5እርሱም። ስንት እንጀራ አላችሁ? ብሎ ጠየቃቸው፥ እነርሱም። ሰባት አሉት።
6Tada Jis liepė žmonėms susėsti ant žemės. Paėmęs septynis kepalus, palaimino, laužė ir davė mokiniams dalyti, ir tie padalijo miniai.
6ሕዝቡም በምድር እንዲቀመጡ አዘዘ። ሰባቱንም እንጀራ ይዞ አመሰገነ፥ ቈርሶም እንዲያቀርቡላቸው ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠ፥ ለሕዝቡም አቀረቡ።
7Jie dar turėjo kelias žuveles. Jis palaimino jas ir taip pat liepė dalyti.
7ጥቂትም ትንሽ ዓሣ ነበራቸው፤ ባረከውም ይህንም ደግሞ እንዲያቀርቡላቸው አዘዘ።
8Žmonės pavalgė iki soties, ir jie surinko dar septynias pintines likučių.
8በሉም ጠገቡም፥ የተረፈውንም ቍርስራሽ ሰባት ቅርጫት አነሡ።
9O valgytojų buvo apie keturis tūkstančius. Jėzus paleido juos
9የበሉትም አራት ሺህ ያህል ነበሩ።
10ir tuojau, įsėdęs su mokiniais į valtį, nuplaukė į Dalmanutos sritį.
10አሰናበታቸውም። ወዲያውም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደ ታንኳይቱ ገብቶ ወደ ዳልማኑታ አገር መጣ።
11Čia priėjo fariziejų ir pradėjo su Juo ginčytis. Mėgindami Jį, jie reikalavo ženklo iš dangaus.
11ፈሪሳውያንም ወጡና ሊፈትኑት ከሰማይ ምልክት ከእርሱ ፈልገው ከእርሱ ጋር ይከራከሩ ጀመር።
12Atsidusęs iš dvasios gilumos, Jis tarė: “Ir kam šita karta reikalauja ženklo? Iš tiesų sakau jums: ženklo šiai kartai nebus duota!”
12በመንፈሱም እጅግ ቃተተና። ይህ ትውልድ ስለ ምን ምልክት ይፈልጋል? እውነት እላችኋለሁ፥ ለዚህ ትውልድ ምልክት አይሰጠውም አለ።
13Ir, palikęs juos, Jis vėl sėdo į valtį ir nuplaukė į kitą krantą.
13ትቶአቸውም እንደ ገና ወደ ታንኳይቱ ገብቶ ወደ ማዶ ሄደ።
14Mokiniai buvo pamiršę pasiimti duonos. Jie teturėjo su savim valtyje vieną kepalą.
14እንጀራ መያዝም ረሱ፥ ለእነርሱም ከአንድ እንጀራ በቀር በታንኳይቱ አልነበራቸውም።
15Jėzus juos įspėjo: “Žiūrėkite, saugokitės fariziejų raugo ir Erodo raugo”.
15እርሱም። ተጠንቀቁ፤ ከፈሪሳውያንና ከሄሮድስ እርሾ ተጠበቁ ብሎ አዘዛቸው።
16Jie svarstė tarpusavy, sakydami: “Tai todėl, kad nepasiėmėme duonos”.
16እርስ በርሳቸውም። እንጀራ ስለሌለን ይሆናል ብለው ተነጋገሩ።
17Tai supratęs, Jėzus tarė: “Kam jūs tariatės neturį duonos? Argi vis dar neišmanote ir nesuprantate ir jūsų širdys vis dar užkietėjusios?
17ኢየሱስም አውቆ እንዲህ አላቸው። እንጀራ ስለሌላችሁ ስለ ምን ትነጋገራላችሁ? ገና አልተመለከታችሁምን? አላስተዋላችሁምን?
18Turite akis, ir nematote; turite ausis, ir negirdite? Argi neatsimenate,
18ልባችሁስ ደንዝዞአልን? ዓይን ሳላችሁ አታዩምን? ጆሮስ ሳላችሁ አትሰሙምን? ትዝስ አይላችሁምን?
19jog penkis kepalus Aš sulaužiau penkiems tūkstančiams? O kiek pilnų pintinių trupinių pririnkote?” Jie atsakė: “Dvylika”.
19አምስቱን እንጀራ ለአምስት ሺህ በቈረስሁ ጊዜ፥ ቍርስራሹ የሞላ ስንት መሶብ አነሣችሁ? እነርሱም። አሥራ ሁለት አሉት።
20“O kai septynis kepalus sulaužiau keturiems tūkstančiams, kiek pilnų pintinių trupinių pririnkote?” Jie atsakė: “Septynias”.
20ሰባቱን እንጀራስ ለአራት ሺህ በቈረስሁ ጊዜ፥ ቍርስራሹ የሞላ ስንት ቅርጫት አነሣችሁ? እነርሱም። ሰባት አሉት።
21Tada Jis tarė: “Tai kaipgi vis dar nesuprantate?!”
21ገና አላስተዋላችሁምን? አላቸው።
22Jie ateina į Betsaidą. Ten atveda pas Jėzų neregį ir prašo jį palytėti.
22ወደ ቤተ ሳይዳም መጡ። ዕውርም አመጡለት፥ እንዲዳስሰውም ለመኑት።
23Jis paėmė neregį už rankos ir nusivedė už kaimo. Ten spjovė jam į akis, uždėjo ant jo rankas ir paklausė: “Ar ką nors matai?”
23ዕውሩንም እጁን ይዞ ከመንደር ውጭ አወጣው፥ በዓይኑም ተፍቶበት እጁንም ጭኖበት። አንዳች ታያለህን ብሎ ጠየቀው።
24Šis apsižvalgęs tarė: “Regiu žmones. Lyg kokius medžius matau juos vaikščiojančius”.
24አሻቅቦም። ሰዎች እንደ ዛፍ ሲመላለሱ አያለሁ አለ።
25Jis vėl rankomis palietė jo akis ir liepė apsižvalgyti. Ir šis tapo sveikas ir viską aiškiai matė.
25ከዚህም በኋላ ደግሞ እጁን በዓይኑ ላይ ጫነበት አጥርቶም አየና ዳነም ከሩቅም ሳይቀር ሁሉን ተመለከተ።
26Jėzus išsiuntė jį namo, sakydamas: “Neužeik į kaimą ir niekam ten nepasakok!”
26ወደ ቤቱም ሰደደውና። ወደ መንደሩ አትግባ በመንደሩም ለማንም አንዳች አትናገር አለው።
27Jėzus su savo mokiniais išėjo į Pilypo Cezarėjos kaimus. Kelyje klausė mokinius: “Kuo mane žmonės laiko?”
27ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱም በፊልጶስ ቂሣርያ ወዳሉ መንደሮች ወጡ በመንገድም። ሰዎች እኔ ማን እንደ ሆንሁ ይላሉ? ብሎ ደቀ መዛሙርቱን ጠየቃቸው።
28Jie atsakė: “Vieni­Jonu Krikštytoju, kiti­Eliju, treti­vienu iš pranašų”.
28እነርሱም። መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ከነቢያት አንዱ ብለው ነገሩት።
29Tada Jis paklausė: “O jūs kuo mane laikote?” Petras Jam atsakė: “Tu esi Kristus”.
29እናንተስ እኔ ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? ብሎ ጠየቃቸው። ጴጥሮስም። አንተ ክርስቶስ ነህ ብሎ መለሰለት።
30Tada Jėzus griežtai įsakė niekam apie Jį nekalbėti.
30ስለ እርሱም ለማንም እንዳይናገሩ አዘዛቸው።
31Jis pradėjo juos mokyti, jog Žmogaus Sūnus turės daug iškentėti, būti vyresniųjų, aukštųjų kunigų bei Rašto žinovų atmestas, nužudytas ir po trijų dienų prisikelti.
31የሰው ልጅ ብዙ መከራ ሊቀበል፥ ከሽማግሌዎችም ከካህናት አለቆችም ከጻፎችም ሊጣል፥ ሊገደልም ከሦስት ቀንም በኋላ ሊነሣ እንዲገባው ያስተምራቸው ጀመር፤ ቃሉንም ገልጦ ይናገር ነበር።
32Jis tai kalbėjo visiškai atvirai. Tada Petras, pasivadinęs Jį į šalį, ėmė Jį drausti.
32ጴጥሮስም ወደ እርሱ ወስዶ ይገሥጸው ጀመር።
33Jėzus atsigręžęs pažiūrėjo į mokinius ir sudraudė Petrą: “Eik šalin, šėtone, nes tu mąstai ne apie tai, kas Dievo, o kas žmonių!”
33እርሱ ግን ዘወር አለ ደቀ መዛሙርቱንም አይቶ ጴጥሮስን ገሠጸውና። ወደ ኋላዬ ሂድ፥ አንተ ሰይጣን፤ የሰውን እንጂ የእግዚአብሔርን ነገር አታስብምና አለው።
34Pasišaukęs minią ir savo mokinius, Jėzus prabilo: “Jei kas nori eiti paskui mane, teišsižada pats savęs, teima savo kryžių ir teseka manimi.
34ሕዝቡንም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ጠርቶ እንዲህ አላቸው። በኋላዬ ሊመጣ የሚወድ ቢኖር፥ ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ።
35Kas nori išgelbėti savo gyvybę, tas ją praras; o kas praras savo gyvybę dėl manęs ir dėl Evangelijos, tas ją išgelbės.
35ነፍሱን ሊያድን የሚወድ ሁሉ ያጠፋታልና፥ ስለ እኔና ስለ ወንጌል ነፍሱን የሚያጠፋ ሁሉ ግን ያድናታል።
36Kokia gi žmogui nauda, jeigu jis laimėtų visą pasaulį, o pakenktų savo sielai?
36ሰው ዓለምን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል?
37Arba kuo žmogus galėtų išsipirkti savo sielą?!
37ሰውስ ስለ ነፍሱ ቤዛ ምን ይሰጣል?
38Jei kas gėdisi manęs ir mano žodžių šios svetimaujančios ir nuodėmingos kartos akivaizdoje, to gėdysis ir Žmogaus Sūnus, kai Jis ateis savo Tėvo šlovėje su šventaisiais angelais”.
38በዚህም በዘማዊና በኃጢአተኛ ትውልድ መካከል በእኔና በቃሌ የሚያፍር ሁሉ፥ የሰው ልጅ ደግሞ በአባቱ ክብር ከቅዱሳን መላእክት ጋር በመጣ ጊዜ በእርሱ ያፍርበታል።