Lithuanian

Amharic: New Testament

Matthew

5

1Matydamas minias, Jėzus užkopė į kalną ir atsisėdo. Prie Jo priėjo mokiniai.
1ሕዝቡንም አይቶ ወደ ተራራ ወጣ፤ በተቀመጠም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ወደ እርሱ ቀረቡ፤
2Atvėręs lūpas, Jis ėmė mokyti:
2አፉንም ከፍቶ አስተማራቸው እንዲህም አለ።
3“Palaiminti vargšai dvasia, nes jų yra dangaus karalystė.
3በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና።
4Palaiminti, kurie liūdi, nes jie bus paguosti.
4የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው፥ መፅናናትን ያገኛሉና።
5Palaiminti romieji, nes jie paveldės žemę.
5የዋሆች ብፁዓን ናቸው፥ ምድርን ይወርሳሉና።
6Palaiminti, kurie alksta ir trokšta teisumo, nes jie bus pasotinti.
6ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፥ ይጠግባሉና።
7Palaiminti gailestingieji, nes jie susilauks gailestingumo.
7የሚምሩ ብፁዓን ናቸው፥ ይማራሉና።
8Palaiminti tyraširdžiai, nes jie regės Dievą.
8ልበ ንጹሖች ብፁዓን ናቸው፥ እግዚአብሔርን ያዩታልና።
9Palaiminti taikdariai, nes jie bus vadinami Dievo vaikais.
9የሚያስተራርቁ ብፁዓን ናቸው፥ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና።
10Palaiminti, kurie persekiojami dėl teisumo, nes jų yra dangaus karalystė.
10ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና።
11Palaiminti jūs, kai dėl manęs jus šmeižia ir persekioja bei meluodami visaip piktžodžiauja.
11ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዱአችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ።
12Būkite linksmi ir džiūgaukite, nes didelis jūsų atlygis danguje. Juk lygiai taip persekiojo ir iki jūsų buvusius pranašus”.
12ዋጋችሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ፥ ሐሴትም አድርጉ፤ ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያትን እንዲሁ አሳድደዋቸዋልና።
13“Jūs esate žemės druska. Jei druska netenka sūrumo, kuo gi ją reikėtų pasūdyti? Ji niekam netinka, ir belieka ją išberti žmonėms sumindžioti.
13እናንተ የምድር ጨው ናችሁ፤ ጨው አልጫ ቢሆን ግን በምን ይጣፍጣል? ወደ ውጭ ተጥሎ በሰው ከመረገጥ በቀር ወደ ፊት ለምንም አይጠቅምም።
14Jūs esate pasaulio šviesa. Neįmanoma nuslėpti miesto, pastatyto ant kalno.
14እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ። በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም።
15Ir niekas, uždegęs žiburį, nevožia jo indu, bet stato į žibintuvą, kad šviestų visiems, kas yra namuose.
15መብራትንም አብርተው ከዕንቅብ በታች አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ ያኖሩታል በቤት ላሉት ሁሉም ያበራል።
16Taip tešviečia ir jūsų šviesa žmonių akivaizdoje, kad jie matytų jūsų gerus darbus ir šlovintų jūsų Tėvą, kuris danguje”.
16መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።
17“Nemanykite, jog Aš atėjau panaikinti Įstatymo ar Pranašų. Ne panaikinti jų atėjau, bet įvykdyti.
17እኔ ሕግንና ነቢያትን ለመሻር የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ልፈጽም እንጂ ለመሻር አልመጣሁም።
18Iš tiesų sakau jums: kol dangus ir žemė nepraeis, nė viena raidelė ir nė vienas brūkšnelis neišnyks iš Įstatymo, kol viskas išsipildys.
18እውነት እላችኋለሁ፥ ሰማይና ምድር እስኪያልፍ ድረስ፥ ከሕግ አንዲት የውጣ ወይም አንዲት ነጥብ ከቶ አታልፍም፥ ሁሉ እስኪፈጸም ድረስ።
19Todėl, kas sulaužytų bent vieną iš mažiausių įsakymų ir taip mokytų žmones, tas bus vadinamas mažiausiu dangaus karalystėje. O kas juos vykdys ir jų mokys, bus vadinamas didžiu dangaus karalystėje.
19እንግዲህ ከነዚህ ከሁሉ ካነሱት ትእዛዛት አንዲቱን የሚሽር ለሰውም እንዲሁ የሚያስተምር ማንም ሰው በመንግሥተ ሰማያት ከሁሉ ታናሽ ይባላል፤ የሚያደርግ ግን የሚያስተምርም ማንም ቢሆን እርሱ በመንግሥተ ሰማያት ታላቅ ይባላል።
20Taigi sakau jums: jeigu jūsų teisumas nepranoks Rašto žinovų ir fariziejų teisumo,­neįeisite į dangaus karalystę”.
20እላችኋለሁና። ጽድቃችሁ ከጻፎችና ከፈሪሳውያን ጽድቅ ካልበለጠ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም።
21“Jūs girdėjote, kad protėviams buvo pasakyta: ‘Nežudyk’; o kas nužudo, turės atsakyti teisme.
21ለቀደሙት። አትግደል እንደ ተባለ ሰምታችኋል፤ የገደለም ሁሉ ፍርድ ይገባዋል።
22O Aš jums sakau: kas be reikalo pyksta ant savo brolio, turės atsakyti teisme. Kas sako savo broliui: ‘Pusgalvi’, turės stoti prieš sinedrioną. O kas sako: ‘Beproti’, tas smerktinas į pragaro ugnį.
22እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል፤ ወንድሙንም ጨርቃም የሚለው ሁሉ የሸንጎ ፍርድ ይገባዋል፤ ደንቆሮ የሚለውም ሁሉ የገሃነመ እሳት ፍርድ ይገባዋል።
23Todėl jei neši dovaną prie aukuro ir ten prisimeni, jog tavo brolis turi šį tą prieš tave,
23እንግዲህ መባህን በመሠዊያው ላይ ብታቀርብ፥ በዚያም ወንድምህ አንዳች በአንተ ላይ እንዳለው ብታስብ፥
24palik savo dovaną ten prie aukuro, eik pirmiau susitaikinti su savo broliu, ir tik tada sugrįžęs aukok savo dovaną.
24በዚያ በመሠዊያው ፊት መባህን ትተህ ሂድ፥ አስቀድመህም ከወንድምህ ጋር ታረቅ፥ በኋላም መጥተህ መባህን አቅርብ።
25Greitai susitark su savo kaltintoju, dar kelyje į teismą, kad kaltintojas neįduotų tavęs teisėjui, o teisėjas­teismo vykdytojui ir kad nepakliūtum į kalėjimą.
25አብረኸው በመንገድ ሳለህ ከባላጋራህ ጋር ፈጥነህ ተስማማ፤ ባላጋራ ለዳኛ እንዳይሰጥህ ዳኛም ለሎሌው፥ ወደ ወህኒም ትጣላለህ፤
26Iš tiesų sakau tau: neišeisi iš ten, kol neatsiteisi iki paskutinio skatiko”.
26እውነት እልሃለሁ፥ የመጨረሻዋን ሳንቲም እስክትከፍል ድረስ ከቶ ከዚያ አትወጣም።
27“Jūs girdėjote, jog protėviams buvo pasakyta: ‘Nesvetimauk!’
27አታመንዝር እንደ ተባለ ሰምታችኋል።
28O Aš jums sakau: kiekvienas, kuris geidulingai žiūri į moterį, jau svetimauja savo širdyje.
28እኔ ግን እላችኋለሁ፥ ወደ ሴት ያየ ሁሉ የተመኛትም ያን ጊዜ በልቡ ከእርስዋ ጋር አመንዝሮአል።
29Jeigu tavo dešinioji akis skatina tave nusidėti, išlupk ją ir mesk šalin. Geriau tau netekti vieno nario, negu kad visas kūnas būtų įmestas į pragarą.
29ቀኝ ዓይንህም ብታሰናክልህ አውጥተህ ከአንተ ጣላት፤ ሙሉ ሰውነትህ በገሃነም ከሚጣል ይልቅ ከአካላትህ አንድ ቢጠፋ ይሻልሃልና።
30Ir jeigu tavo dešinioji ranka skatina tave nusidėti, nukirsk ją ir mesk šalin. Geriau tau netekti vieno nario, negu kad visas kūnas būtų įmestas į pragarą”.
30ቀኝ እጅህም ብታሰናክልህ ቆርጠህ ከአንተ ጣላት፤ ሙሉ ሰውነትህ በገሃነም ከሚጣል ይልቅ ከአካላትህ አንድ ቢጠፋ ይሻላልና።
31“Taip pat buvo pasakyta: ‘Kas atleidžia savo žmoną, teišduoda jai skyrybų raštą’.
31ሚስቱን የሚፈታት ሁሉ የፍችዋን ጽሕፈት ይስጣት ተባለ።
32O Aš jums sakau: kiekvienas, kuris atleidžia savo žmoną,­jei ne ištvirkavimo atveju,­skatina ją svetimauti; ir jeigu kas atleistąją veda­svetimauja”.
32እኔ ግን እላችኋለሁ፥ ያለ ዝሙት ምክንያት ሚስቱን የሚፈታ ሁሉ አመንዝራ ያደርጋታል፥ የተፈታችውንም የሚያገባ ሁሉ ያመነዝራል።
33“Taip pat girdėjote, jog protėviams buvo pasakyta: ‘Neprisiek melagingai, bet ištesėk Viešpačiui savo priesaikas’.
33ደግሞ ለቀደሙት። በውሸት አትማል ነገር ግን መሐላዎችህን ለጌታ ስጥ እንደተባለ ሰምታችኋል።
34O Aš jums sakau: iš viso neprisiekinėkite nei dangumi, nes jis­ Dievo sostas,
34እኔ ግን እላችኋለሁ። ከቶ አትማሉ፤ በሰማይ አይሆንም የእግዚአብሔር ዙፋን ነውና፤
35nei žeme, nes ji­Jo pakojis, nei Jeruzale, nes ji­didžiojo Karaliaus miestas.
35በምድርም አይሆንም የእግሩ መረገጫ ናትና፤ በኢየሩሳሌምም አይሆንም የታላቁ ንጉሥ ከተማ ናትና፤
36Neprisiek nei savo galva, nes negali nė vieno plauko padaryti balto ar juodo.
36በራስህም አትማል፥ አንዲቱን ጠጉር ነጭ ወይም ጥቁር ልታደርግ አትችልምና።
37Verčiau jūs sakykite: ‘Taip’, jei taip, ‘Ne’, jei ne, o kas viršaus, tai iš pikto”.
37ነገር ግን ቃላችሁ አዎን አዎን ወይም አይደለም አይደለም ይሁን፤ ከነዚህም የወጣ ከክፉው ነው።
38“Jūs girdėjote, jog buvo pasakyta: ‘Akis už akį’ ir ‘dantis už dantį’.
38ዓይን ስለ ዓይን ጥርስም ስለ ጥርስ እንደ ተባለ ሰምታችኋል።
39O Aš jums sakau: nesipriešinkite piktam, bet, jei kas tave muštų per dešinį skruostą, atsuk jam ir kitą.
39እኔ ግን እላችኋለሁ፥ ክፉውን አትቃወሙ፤ ዳሩ ግን ቀኝ ጉንጭህን በጥፊ ለሚመታህ ሁሉ ሁለተኛውን ደግሞ አዙርለት፤
40Jei kas nori su tavimi bylinėtis ir paimti tavo tuniką, atiduok jam ir apsiaustą.
40እንዲከስህም እጀ ጠባብህንም እንዲወስድ ለሚወድ መጎናጸፊያህን ደግሞ ተውለት፤
41Jei kas verstų tave nueiti mylią, nueik su juo dvi.
41ማንም ሰው አንድ ምዕራፍ ትሄድ ዘንድ ቢያስገድድህ ሁለተኛውን ከእርሱ ጋር ሂድ።
42Prašančiam duok ir nuo norinčio iš tavęs pasiskolinti nenusigręžk.
42ለሚለምንህ ስጥ፥ ከአንተም ይበደር ዘንድ ከሚወደው ፈቀቅ አትበል።
43Jūs girdėjote, jog buvo pasakyta: ‘Mylėk savo artimą’ ir nekęsk savo priešo.
43ባልንጀራህን ውደድ ጠላትህንም ጥላ እንደ ተባለ ሰምታችኋል።
44O Aš jums sakau: mylėkite savo priešus, laiminkite jus keikiančius, darykite gera tiems, kurie nekenčia jūsų, ir melskitės už savo skriaudėjus ir persekiotojus,
44እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፥ ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤ እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና።
45kad būtumėte vaikai savo Tėvo, kuris danguje; Jis juk leidžia savo saulei tekėti blogiesiems ir geriesiems, siunčia lietų ant teisiųjų ir neteisiųjų.
46የሚወዱአችሁን ብትወዱ ምን ዋጋ አላችሁ? ቀራጮችስ ያንኑ ያደርጉ የለምን?
46Jei mylite tuos, kurie jus myli, kokį gi atlygį turite? Argi taip nesielgia ir muitininkai?
47ወንድሞቻችሁንም ብቻ እጅ ብትነሡ ምን ብልጫ ታደርጋላችሁ? አሕዛብስ ያንኑ ያደርጉ የለምን?
47Ir jeigu sveikinate tik savo brolius, kuo gi viršijate kitus? Argi to nedaro ir muitininkai?
48እንግዲህ የሰማዩ አባታችሁ ፍጹም እንደ ሆነ እናንተ ፍጹማን ሁኑ።
48Taigi būkite tobuli, kaip ir jūsų Tėvas, kuris danguje, yra tobulas”.