1Taigi, jeigu esama Kristuje kokio padrąsinimo, meilės paguodos, jei esama kokio Dvasios bendravimo, nuoširdumo ir gailestingumo,
1በክርስቶስም አንዳች ምክር ቢሆን፥ የፍቅር መጽናናት ቢሆን፥ የመንፈስ ኅብረት ቢሆን፥ ምሕረትና ርኅራኄ ቢሆኑ፥ ደስታዬን ፈጽሙልኝ፤
2tai padarykite mano džiaugsmą tobulą, laikydamiesi vienos minties, turėdami vienokią meilę, būdami vieningi ir to paties nusistatymo.
2በአንድ አሳብ ተስማሙ፥ አንድ ፍቅር አንድም ልብ አንድም አሳብ ይሁንላችሁ፤
3Nedarykite nieko varžydamiesi ar iš tuščios puikybės, bet nuolankiai vienas kitą laikykite aukštesniu už save
3ለወገኔ ይጠቅማል በማለት ወይም በከንቱ ውዳሴ ምክንያት አንድ እንኳ አታድርጉ፥ ነገር ግን እያንዳንዱ ባልንጀራው ከራሱ ይልቅ እንዲሻል በትሕትና ይቍጠር፤
4ir žiūrėkite kiekvienas ne savo naudos, bet kitų.
4እያንዳንዱ ለራሱ የሚጠቅመውን አይመልከት፥ ለባልንጀራው ደግሞ እንጂ።
5Būkite tokio nusistatymo kaip Kristus Jėzus,
5በክርስቶስ ኢየሱስ የነበረ ይህ አሳብ በእናንተ ዘንድ ደግሞ ይሁን።
6kuris, esybe būdamas Dievas, nesilaikė pasiglemžęs savo lygybės su Dievu,
6እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቈጠረውም፥
7bet apiplėšė save ir esybe tapo tarnu ir panašus į žmones.
7ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥
8Ir išore tapęs kaip žmogus, Jis nusižemino, tapdamas paklusnus iki mirties, iki kryžiaus mirties.
8በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፥ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ።
9Todėl Dievas Jį labai išaukštino ir suteikė Jam vardą aukščiau visų kitų vardų,
9በዚህ ምክንያት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው፥ ከስምም ሁሉ በላይ ያለውን ስም ሰጠው፤
10kad Jėzaus vardui priklauptų kiekvienas kelis danguje, žemėje ir po žeme
10ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ፥
11ir kiekvienos lūpos Dievo Tėvo šlovei išpažintų, kad Jėzus Kristus yra Viešpats.
11መላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደ ሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው።
12Taigi, mano mylimieji, kaip visada paklusdavote, kai būdavau tarp jūsų, tai juo labiau dabar, man nesant tarp jūsų,—atbaikite savo išgelbėjimą su baime ir drebėdami,
12ስለዚህ፥ ወዳጆቼ ሆይ፥ ሁልጊዜ እንደ ታዘዛችሁ፥ በእናንተ ዘንድ በመኖሬ ብቻ ሳይሆን ይልቁን አሁን ስርቅ፥ በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ የራሳችሁን መዳን ፈጽሙ፤
13nes tai Dievas, veikiantis jumyse, suteikia ir troškimą, ir darbą iš savo palankumo.
13ስለ በጎ ፈቃዱ መፈለግንም ማድረግንም በእናንተ የሚሠራ እግዚአብሔር ነውና።
14Visa darykite be murmėjimų ir svyravimų,
14በመጥፎና በጠማማ ትውልድ መካከል ያለ ነቀፋ የዋሆችም ነውርም የሌለባቸው የእግዚአብሔር ልጆች እንድትሆኑ ሳታንጐራጉሩ ክፉም ሳታስቡ ሁሉን አድርጉ፤
15kad būtumėte nepeiktini, nekalti ir nesutepti Dievo vaikai sugedusioje ir iškrypusioje žmonių kartoje, kur jūs spindite tarsi žiburiai pasaulyje.
16በእነርሱም መካከል የሕይወትን ቃል እያቀረባችሁ በዓለም እንደ ብርሃን ትታያላችሁ፥ ስለዚህም በከንቱ እንዳልሮጥሁ በከንቱም እንዳልደከምሁ በክርስቶስ ቀን የምመካበት ይሆንልኛል።
16Tvirtai laikykitės gyvenimo žodžio, kad Kristaus dieną galėčiau pasigirti ne veltui bėgęs ir ne veltui dirbęs.
17ነገር ግን በእምነታችሁ መሥዋዕትና አገልግሎት ተጨምሬ ሕይወቴ እንኳ ቢፈስ፥ ደስ ብሎኛል፤ ከሁላችሁም ጋር አብሬ ደስ ብሎኛል፤
17O jei aš atnašaujamas ant jūsų tikėjimo aukos ir tarnavimo, esu linksmas ir džiaugiuosi kartu su jumis visais.
18እናንተም ደግሞ እንዲሁ ደስ ይበላችሁ ከእኔም ጋር አብራችሁ ደስ ይበላችሁ።
18Taip pat ir jūs būkite linksmi ir džiaukitės kartu su manimi.
19ነገር ግን ኑሮአችሁን ሳውቅ እኔ ደግሞ ደስ እንዲለኝ ፈጥኜ ጢሞቴዎስን ልልክላችሁ በጌታ በኢየሱስ ተስፋ አደርጋለሁ።
19Aš turiu Viešpatyje Jėzuje viltį netrukus pasiųsti pas jus Timotiejų, kad būčiau paguostas, sužinojęs, kaip jums sekasi.
20እንደ እርሱ ያለ፥ ስለ ኑሮአችሁ በቅንነት የሚጨነቅ፥ ማንም የለኝምና፤
20Mat aš neturiu nė vieno kito tokio, kuris taip nuoširdžiai jumis rūpintųsi.
21ሁሉ የራሳቸውን ይፈልጋሉና፥ የክርስቶስ ኢየሱስን አይደለም።
21Visi kiti ieško ne Jėzaus Kristaus, bet savo naudos.
22ነገር ግን ልጅ ለአባቱ እንደ ሚያገለግል ከእኔ ጋር ሆኖ ለወንጌል እንደ አገለገለ መፈተኑን ታውቃላችሁ።
22O apie jo ištikimybę jūs žinote, nes skelbiant Evangeliją jis man tarnavo kaip sūnus tėvui.
23እንግዲህ እንዴት እንደምሆን ባየሁ ጊዜ፥ እርሱን ቶሎ እንድልክ ተስፋ አደርጋለሁ፤
23Taigi, kai tik paaiškės mano byla, viliuosi tučtuojau jį pasiųsti.
24ራሴ ደግሞ ግን ፈጥኜ እንድመጣ በጌታ ታምኜአለሁ።
24Be to, turiu Viešpatyje viltį ir pats netrukus atvykti pas jus.
25ነገር ግን ወንድሜንና ከእኔ ጋር አብሮ ሠራተኛ ወታደርም የሚሆነውን፥ የእናንተ ግን መልእክተኛ የሆነውና የሚያስፈልገኝን የሚያገለግለውን አፍሮዲጡን እንድልክላችሁ በግድ አስባለሁ፤
25Aš dar nusprendžiau siųsti pas jus Epafroditą, mano brolį, bendradarbį ir kovų draugą, o jūsų pasiuntinį ir pagalbininką mano reikmėse.
26ሁላችሁን ይናፍቃልና፥ እንደ ታመመም ስለ ሰማችሁ ይተክዛል።
26Jis labai jūsų išsiilgo ir sielojosi, kad jūs išgirdote apie jo ligą.
27በእውነት ታሞ ለሞት እንኳ ቀርቦ ነበርና፤ ነገር ግን እግዚአብሔር ማረው፥ ኀዘን በኀዘን ላይ እንዳይጨመርብኝ ለእኔ ደግሞ እንጂ ለእርሱ ብቻ አይደለም።
27Tikrai jis sirgo ir buvo arti mirties, tačiau Dievas jo pasigailėjo, ir ne vien tik jo, bet ir manęs, kad manęs neužgriūtų sielvartas po sielvarto.
28እንግዲህ እንደ ገና ስታዩት ደስ እንዲላችሁ ለእኔም ኀዘኔ እንዲቃለል በብዙ ፍጥነት እልከዋለሁ።
28Taigi aš jį skubiai siunčiu, kad, jį pamatę, pradžiugtumėte ir aš taip pat neliūdėčiau.
29እንግዲህ በሙሉ ደስታ በጌታ ተቀበሉት፥ እርሱን የሚመስሉትንም አክብሩአቸው፤
29Tad priimkite jį Viešpatyje su tikru džiaugsmu ir gerbkite tokius žmones,
30በእኔ ዘንድ ካላችሁ አገልግሎት እናንተ ስለሌላችሁ የጎደለኝን እንዲፈጽም፥ በነፍሱ ተወራርዶ ከጌታ ሥራ የተነሣ እስከ ሞት ቀርቦአልና።
30nes dėl Kristaus darbo jis buvo atsidūręs prie mirties, nebrangindamas savo gyvybės, kad užpildytų spragą jūsų patarnavime man.