Lithuanian

Amharic: New Testament

Revelation

11

1Man buvo duotas nendrinis matas, panašus į lazdą, ir angelas pasakė: “Kelkis ir išmatuok Dievo šventyklą, aukurą ir tuos, kurie tenai garbina.
1በትር የሚመስል መለኪያ ለእኔ ተሰጠኝ፥ እንዲህም ተባለልኝ። ተነሥተህ የእግዚአብሔርን መቅደስና መሠዊያውን በዚያም የሚሰግዱትን ለካ።
2O išorinį šventyklos kiemą praleisk, palik, nematuok jo, nes jis skirtas pagonims. Jie tryps šventąjį miestą keturiasdešimt du mėnesius.
2በመቅደሱም ውጭ ያለው እድሞ ለአሕዛብ ተሰጥቶአልና ተወው አትለካውም፤ እነርሱም አርባ ሁለት ወር የተቀደሰችውን ከተማ ይረግጡአታል።
3Aš duosiu galią savo dviem liudytojams, ir jie, apsivilkę ašutinėmis, pranašaus tūkstantį du šimtus šešiasdešimt dienų”.
3ለሁለቱም ምስክሮቼ ማቅ ለብሰው ሺህ ከሁለት መቶ ስድሳ ቀን ትንቢት ሊናገሩ እሰጣለሁ።
4Jie yra du alyvmedžiai ir du žibintuvai, stovintys žemės Dievo akivaizdoje.
4እነዚህ በምድር ጌታ ፊት የሚቆሙ ሁለቱ ወይራዎችና ሁለቱ መቅረዞች ናቸው።
5Ir jei kas panorės juos skriausti, iš jų burnos išsiverš ugnis ir praris jų priešininkus. Jei kas norės jiems kenkti, tas irgi taip žus.
5ማንምም ሊጐዳቸው ቢወድ እሳት ከአፋቸው ይወጣል ጠላቶቻቸውንም ይበላል፤ ማንም ሊጐዳቸው ቢወድም እንዲሁ ሊገደል ይገባዋል።
6Jiedu turi valdžią užrakinti dangų, kad jų pranašavimo dienomis nelytų lietus, ir turi valdžią vandenis paversti krauju ir ištikti žemę bet kokia neganda, kada tik panorės.
6እነዚህ ትንቢት በሚናገሩበት ወራት ዝናብ እንዳይዘንብ ሰማይን ሊዘጉ ሥልጣን አላቸው፥ ውኃዎችንም ወደ ደም ሊለውጡ በሚፈልጉበትም ጊዜ ሁሉ በመቅሠፍት ሁሉ ምድርን ሊመቱ ሥልጣን አላቸው።
7Kai jie baigs liudyti, žvėris, išlindęs iš bedugnės, kovos su jais, nugalės ir nužudys juos.
7ምስክራቸውን ከፈጸሙ በኋላ ከጥልቁ የሚወጣው አውሬ ይዋጋቸዋል ያሸንፋቸውማል ይገድላቸውማል።
8Jų lavonai gulės gatvėje didžiojo miesto, kuris dvasine prasme vadinamas Sodoma ir Egiptu, kur ir mūsų Viešpats buvo nukryžiuotas.
8በድናቸውም በታላቂቱ ከተማ አደባባይ ይተኛል እርስዋም በመንፈሳዊ ምሳሌ ሰዶምና ግብጽ የተባለች ደግሞ ጌታቸው የተሰቀለባት ናት።
9Tada įvairių tautų, genčių, kalbų ir giminių žmonės matys jų lavonus pusketvirtos dienos ir neleis jų lavonų palaidoti kapuose.
9ከወገኖችና ከነገዶችም ከቋንቋዎችም ከአሕዛብም የሆኑ ሰዎች ሦስት ቀን ተኵል በድናቸውን ይመለከታሉ፥ በድናቸውም ወደ መቃብር ሊገባ አይፈቅዱም።
10Žemės gyventojai džiūgaus dėl jų ir linksminsis, ir siųs vieni kitiems dovanas, nes tiedu pranašai vargino žemės gyventojus.
10እነዚህም ሁለት ነቢያት በምድር የሚኖሩትን ስለ ሣቀዩ በምድር የሚኖሩት በእነርሱ ላይ ደስ ይላቸዋል በደስታም ይኖራሉ እርስ በርሳቸውም ስጦታ ይሰጣጣሉ።
11O po pusketvirtos dienos gyvybės dvasia nuo Dievo įžengė į juodu. Jie pašoko ant kojų, ir didžiulė baimė pagavo tuos, kurie į juos žiūrėjo.
11ከሦስቱ ቀን ተኵልም በኋላ ከእግዚአብሔር የወጣ የሕይወት መንፈስ ገባባቸው በእግሮቻቸውም ቆሙ፥ ታላቅም ፍርሃት በሚመለከቱት ላይ ወደቀባቸው።
12Ir jie išgirdo galingą balsą iš dangaus, kuris jiems šaukė: “Užženkite šen!” Ir juodu užžengė į dangų debesyje, o jų priešai žiūrėjo į juodu.
12በሰማይም። ወደዚህ ውጡ የሚላቸውን ታላቅ ድምፅ ሰሙ፤ ጠላቶቻቸውም እየተመለከቱአቸው ወደ ሰማይ በደመና ወጡ።
13Tą pačią valandą kilo didelis žemės drebėjimas, ir dešimta dalis miesto sugriuvo. Nuo žemės drebėjimo žuvo septyni tūkstančiai žmonių, o likusieji, baimės apimti, atidavė šlovę dangaus Dievui.
13በዚያም ሰዓት ታላቅ የምድር መናወጥ ሆነ፥ ከከተማይቱም አሥረኛው እጅ ወደቀ፥ በመናወጥም ሰባት ሺህ ሰዎች ተገደሉ፥ የቀሩትንም ፍርሃት ያዛቸው፥ ለሰማዩም አምላክ ክብር ሰጡ።
14Antroji neganda praėjo. Štai greit artinasi trečioji neganda.
14ሁለተኛው ወዮ አልፎአል፤ እነሆ፥ ሦስተኛው ወዮ በቶሎ ይመጣል።
15Sutrimitavo septintasis angelas. Danguje pasigirdo galingi balsai, kurie skelbė: “Šio pasaulio karalystės tapo mūsų Viešpaties ir Jo Kristaus karalystėmis, ir Jis valdys per amžių amžius!”
15ሰባተኛው መልአክ ነፋ፤ በሰማይም። የዓለም መንግሥት ለጌታችንና ለእርሱ ለክርስቶስ ሆነች፥ ለዘላለምም እስከ ዘላለም ይነግሣል
16O dvidešimt keturi vyresnieji, sėdintys savo sostuose Dievo akivaizdoje, parpuolė veidais žemėn ir garbino Dievą,
16የሚሉ ታላላቅ ድምፆች ሆኑ። በእግዚአብሔርም ፊት በዙፋኖቻቸው የተቀመጡ ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በግምባራቸው ተደፍተው
17sakydami: “Dėkojame Tau, o Viešpatie, visagalis Dieve, kuris esi ir kuris buvai, ir kuris ateini, kad pasiėmei savo didžiąją galią ir pradėjai viešpatauti.
17ለእግዚአብሔር እየሰገዱ እንዲህ አሉ። ያለህና የነበርህ ሁሉን የምትገዛ ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፥ ትልቁን ኃይልህን ስለ ያዝህ ስለ ነገሥህም እናመሰግንሃለን፤
18Tautos įširdo, ir atėjo Tavo rūstybė, metas teisti mirusius ir atlyginti Tavo tarnams, pranašams ir šventiesiems, ir visiems bijantiems Tavojo vardo, mažiems ir dideliems, ir metas sunaikinti tuos, kurie niokoja žemę”.
18አሕዛብም ተቈጡ፥ ቍጣህም መጣ፥ በሙታንም ትፈርድ ዘንድ ዘመን መጣ፥ ለባሪያዎችህም ለነቢያትና ለቅዱሳን ስምህንም ለሚፈሩት ለታናናሾችና ለታላላቆችም ዋጋቸውን ትሰጥ ዘንድ፥ ምድርንም የሚያጠፉትን ታጠፋ ዘንድ ዘመን መጣ።
19Ir atsidarė danguje Dievo šventykla, ir pasirodė Jo šventykloje Jo Sandoros skrynia. Ir radosi žaibai, balsai, griaustiniai, žemės drebėjimas ir didelė kruša.
19በሰማይም ያለው የእግዚአብሔር መቅደስ ተከፈተ፥ የኪዳኑም ታቦት በመቅደሱ ታየ፥ መብረቅና ድምፅም ነጐድጓድም የምድርም መናወጥ ታላቅም በረዶ ሆነ።